Quantcast
Channel: Ethio Andinet ኢትዮ አንድነት
Viewing all 931 articles
Browse latest View live

የአፍሪካ ህብረት የአምባገነኖች መሰባሰቢያ መሆኑ ይብቃ

$
0
0

ይህ ወቅት የአፍሪካ አንድነት ድርጅትና የአፍሪካ ህብረት 50ኛ አመት የሚያከብርበት ነው፡፡ የዛሬ 50 አመት ኢትዮጵያን ጨምሮ በጊዜው ነፃነታቸውን ያረጋገጡ የአፍሪካ ሀገሮች በመዲናችን አዲስ አበባ በመሰባሰብ የመሰረቱት የአፍሪካ አንድነት ድርጅት ከ11 አመት በፊት ወደ አፍሪካ ህብረት ተሸጋግሯል… በፓን አፍሪካዊ አስተሳሰብ የተፀነሰው ይኸው ተቋም አፍሪካውያንን ከቅኝ ግዛትና ከባርነት አላቆ የበለፀገች አፍሪካን የመፍጠር አላማ ነበረው፡፡ ተቋሙ የተመሰረተበትን 50ኛ አመት ሲያከብር ሁሉም የአፍሪካ ሃገራት ከቅኝ ግዛት ነፃ ቢሆኑም እንደተቀሩት የአለም ክፍሎች በዴሞክራሲና በኢኮኖሚያዊ እድገት ረገድ አብዛኞቹ ሀገራት ወደኋላ መቅረታቸው ሊያሳስብ ይገባል፡፡

African Union meeting (May 25 2013)

 

የኋላቀርነቱ ምንጭ የሆነው ለዘመናትበአፍሪካ ህዝቦችላይ ተጭኖ የቆየው አምባገነናዊ አገዛዝ ስለመሆኑ ነጋሪ አያሻውም፡፡ የአፍሪካ ህብረት ከአህጉሪቱ አንባገነናዊ አገዛዝ እንዲወገድና አፍሪካውያን ከባርነት ነፃ እንዲወጡ ባለፉት ዘመናት ምንም አለማድረጉ
በታሪክ ተወቃሽያ ደርገዋል፡፡ህብረቱ የአባል ሀገራት መንግስታት ዴሞክራሲያዊ ምርጫ እንዲያደርጉ ማበረታታት ይጠበቅበታል፡፡ በመፈንቅለመንግስት ስልጣን የሚይዙ መንግስታትን እንደሚያግደው ሁሉ፣ በተጭበረበረ ምርጫ ስልጣን የሚይዙ መንግስታትን ከህብረቱ በማገድም አህጉሪቱን የተረጋጋችና ከፖለቲካዊ ቀውስ የፀዳች እንድትሆን የበኩሉን በወጣት አለበት፡፡ ቢሞላውም ሊያሳካ ያለመውንየአፍሪካ አንድነት ድርጅት ሲመሰረት ኢትዮጵያ የነፃነት ምሳሌ ነበረች፡፡

አሁን ግን እንደአብዛኞቹ አፍሪካውያን ኢትዮጵያውያንም በአምባገነናዊ ባርነት ስር ሆነን የአፍሪካ ህብረትን 50ኛ አመት ማክበራችን ሊያስቆጨን ይገባል፡፡ ከሀምሳ አመት በፊት በነጭ ወራሪዎች ግዛት ስር ሆነው በባርነት ይኖሩ የነበሩት አፍሪካውያን ዛሬም በአምባገነን መንግስታት ባርነት ስር መሆናቸው መላውን አፍሪካውያን ሊያሳስብ ይገባል፡፡ ሁሉንም ወገን ሊያስማማ የሚችለው የባርነት ፍቺ‹‹የራስ ፈቃድ ሳይኖር ያለፍላጎት የገዢን ፍላጎት እየፈፀሙ መኖር›› የሚል ነው፡፡ በዚህ ፍቺ መሰረት በባዕዳንም ሆነ በሀገሬው ገዢዎች ባርነት ስር መውደቅ የቅርፅ እንጂ የይዘት ለውጥ የለውም፡፡ በመሆኑም አፍሪካውያን አሁንም ከባርነት በመውጣት ዴሞክራሲያዊ ነፃነታቸውን አግኝተው በራሳቸውና በሀገራቸው ጉዳይና ጥቅም ላይ ቀጥተኛ ወሳኝነት እንዲኖራቸው በጥንካሬ መታገል አለባቸው፡፡ የአፍሪካ ህብረትም ይህን ትግል የመደገፍ ኃላፊነቱን ሊወጣ ይገባል፡፡ይህ ካልሆነ ግን የአፍሪካ አንድነት ድርጅት ሲቋቋም የሰነቀው አፍሪካውያንን ሁሉ የነፃነት ተቋዳሽ የማድረግ አላማ ተሳክቷል ብሎ ለመናገር ድፍረት ያሳጣል፡፡ ምክንያቱም አፍሪካውያን በቅኝ ግዛት ወቅት ይደርስባቸው የነበረው ብሔራዊ ጭቆና፣ አፈና እንዲሁም የሀብት ዝርፊያ አሁንም በሚገዙዋቸው አምባገነን መሪዎች እየተፈፀመባቸው ነው፡፡ አብዛኞቹ የአፍሪካ ሀገራት በጦር መሳሪያ እና በተጭበረበረ ምርጫ ስልጣን ላይ በወጡ አምባገነን ገዢዎች ስር ናቸው፡፡

አፍሪካውያን የሀገራቸውን ሀብት በውጭ ወራሪዎች ከመበዝበዝ ቢድኑም አምባገነን ገዢዎቻቸው በከፍተኛ መጠን እየዘረፏቸው ነው፡፡ ለምሳሌ ኢትዮጵያ በጥቂት አመታት ውስጥ ብቻ አስራ አንድ ነጥብ ሰባት ቢሊዮን ዶላር በላይ በኢህአዴግ ባለስልጣናት ተዘፍፎ በህገወጥ መንገድ ከሀገር እንደወጣ በአለም አቀፍ ተቋማት ተረጋግጧል፡፡ ይህ አይነቱ
ዝርፊያ በሌሎቹ የአፍሪካ ሀገራትም እንዳለ መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡ የነፃነት ጥያቄ ባነሱ አፍሪካውያን ላይ ቅኝ ገዢዎች ያደርሱ ከነበረው ግድያ ባልተናነሰ ሁኔታ የአሁኖቹ የአፍሪካ አምባገነን መሪዎች የጅምላ ግድያ ይፈፅማሉ፡፡የአፍሪካ ህብረት የአምባገነኖች መሰባሰቢያ መሆኑን የአፍሪካውያንን ሁሉ የሚያሳስብ በመሆኑ እኛንም ያሳስበናል፡፡ የዛሬው መልዕክታችንም ‹‹የአፍሪካውያን የነፃነት ጥያቄ ይሰማ! የአፍሪካ ህብረት የአምባገነኖች መሰባሰቢያ መሆኑ ይብቃ!›› የሚል ነው፡፡



የኢህአዴግና የሻዕቢያ ድርድር ተበጠሰ

$
0
0

ኳታር በተናጠል የጀመረችው ኢትዮጵያንና ኤርትራን የማሸማገል ሂደት መበጠሱ ተሰምቷል። ከሽምግልናው ዙሪያ የግብጽ ሚና ስለመኖሩ አመላካች ጉዳዮች አሉ እየተባለ ኳታር በተናጠል የጀመረችው ኢትዮጵያንና ኤርትራን የማሸማገል ሂደት መበጠሱ ተሰምቷል። ከሽምግልናው ዙሪያ የግብጽ ሚና ስለመኖሩ አመላካች ጉዳዮች አሉ እየተባለ ነው። በድርድሩ ኢህአዴግ በዋናነት እንደ ቅድመ ሁኔታ ያስቀመጠው የትግራይ ህዝባዊ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ /ደሚት/ ጉዳይ እንደሆነም ለማወቅ ተችሏል…

አቶ መለስ የኢትዮጵያን ወደብ እንደተራ ጉዳይ አሳልፈው በመስጠት ኤርትራን እንደ አገር እውቅና በሰጡበት ወቅት ድጋፍ ለማሰማት ቀዳሚ የነረችው ኳታር ከበረሃው ትግል ጀምሮ የሻዕቢያ ወዳጅ አገር እንደሆነች ይታወቃል

haile and esayas

 ከዚሁ የከረመ ወዳጅነት በመነሳት ኳታር በ2008 ከኢህአዴግ ጋር ተፈጥሮ የነበረውን የጸብ ግድግዳ አፍርሳ ወደ ኢትዮጵያ የመጣችው በዋናነት ሁለቱን አገሮች መልሶ ለማስታረቅ በተያዘ እቅድ ስለመሆኑ ለጉዳዩ ቅርብ የሆኑ ይናገራሉ። በተለይም አሁን ያለው የኤርትራ አስተዳደር እጣ ፈንታ አብዝቶ ያስጨነቃት ኳታር በኤርትራ ወደብ ሊዝ በማድረግ፣ ኢንቨስትመንት ላይ በመሳተፍና ልዩ ድጎማ በማድረግ ቀዳሚውን ስፍራ ስለምትይዝ ችግር ከመፈጠሩ በፊት ላይ ታች ማለቷ እንደማይደንቅ ስምምነት አለ።

ጎልጉል ምንጭ የሆኑ ዲፕሎማት እንዳሉት ኳታር አሁን እርቁን የፈለገችው በኤርትራ መረጋጋት እንዲፈጠርና የኤርትራ ኢኮኖሚ አንዲያገግም ለማድረግ በሚል ነው። በሌላ በኩል ህወሃት የዘወትር ስጋቱ የሆነውን ሻዕቢያን ለማስወገድ ሌት ከቀን እንደሚሰራና ይህም በድርጅት ደረጃ አቋም የተያዘበት ጉዳይ በመሆኑ የኤርትራ መንግስት መሰረታዊ የአቋም ለውጥ ሳያደርግ ከኢህአዴግ ጋር የድርድር ስምምነት ላይ መድረስ አስቸጋሪ እንደሚሆን ሁሉም ወገኖች የሚረዱት ጉዳይ ነው።

ከውስጥም ከውጪም ፖለቲከኞች ትኩረት ሰጥተው እየተከታተሉት ያለው የሁለቱ አገሮች  የሰላም ድርድር ዲፕሎማቱ እንዳሉት ሁለት አብይ ጉዳዮች አሉበት። ሁለቱ አብይ ጉዳዮች ደግሞ ሊነጣጠሉ አይችሉም። በኤርትራ እለት እለት እየሰለለ የሄደው የአገሪቱ ኢኮኖሚና የኑሮ ውድነቱ የኢሳያስን አስተዳደር አናግቶታል። በተጨማሪ ሆን ተብሎ ይሁን በሌላ ምክንያት ከሃያላኑ አገራት ጋር የገጠሙት የረዥም ጊዜ ፍትጊያ የኢሣያስን ትከሻ አዝሎታል። ከዚህም በላይ እድሜ ለመለስ የፍቅር ጊዜያቸው ሲሻግት “አሸባሪ” አድርገዋቸው።

ከዓለምና ከአህጉር መድረኮች ሙሉ በሙሉ ተገልሎ የከረመው የኢሳያስ አስተዳደር በተለያዩ ደረጃዎች የደረሰበትን እግድና ቅጣት ለመቋቋም የዲፕሎማሲ ዘመቻ የጀመረው ከውጪ ያለውን ችግር ተከትሎ በአገር ውስጥ የገጠመውን ፈተና ለመቋቋም እንደሆነ ተንታኞች ያስታውሳሉ። በውስጥ የፖለቲካና የኢኮኖሚ አጣብቂኝ ውስጥ ያለው ሻዕቢያ ወንበሩ እየወላለቀ ስለሆነ ከቀድሞው ወዳጁ ህወሓት ጋር ለመወዳጀት ይፈልጋል።

ኤርትራ ኢኮኖሚዋ እንዲነቃቃ ኢትዮጵያን የንግድ ሸሪኳ ማድረግ የመጀመሪያው ስራ ነው።  ያለ ስራ “ሙት” ሆኖ የተቀመጠውን የአሰብን ወደብ ኢትዮጵያ ከጅቡቲ ባነሰ ዋጋ እንድትጠቀምበት ማድረግና ወደቡ ላይ ህይወት መዝራት ዛሬ ላይ ግድ እየሆነ የመጣ ጉዳይ ነው። በተለይም ኢትዮጵያ ጅቡቲ ላይ የራስዋን ወደብ ለመገንባት የጀመረችው እንቅስቃሴና ለጅቡቲ የወደብ ኪራይ የምትገፈግፈው እጅግ ከፍተኛ ወጪ ግማሹ እንኳን ኤርትራ ቋት ውስጥ ቢገባ አሁን የተፈጠረውን የኑሮ ግለት ጋብ እንደሚያደርገው በርካቶች ይስማሙበታል።

በዚሁ መነሻ የኢሳያስ መንግሰት ከገባበት የመኖርና አለመኖር ስጋት ለመገላገል እቅድ ተነድፎለት የተጀመረውን ድርድር ኢህአዴግ የህልውና ጥያቄ በመጠየቁ ሳቢያ ብዙም ሳይራመድ በእንጭጩ ተኮላሽቷል። ኢህአዴግ በድርድሩ መሰረታዊ ሃሳብም ሆነ በሌሎች ዝርዝር የኢኮኖሚ ነጥቦች የተፈለገው ርቀት ድረስ ለመጓዝ ፈቃደኝነቱን ለመግለጽ ጊዜ አልወሰደም ነበር። የለበጣም ቢመስልም አቶ ሃይለማርያም አስመራ ድረስ ለመሄድ ዝግጁ መሆኑንን ማስታወቃቸው አይዘነጋም።

የሆነ ሆኖ ኢሳያስ አሁን ባላቸው የፖለቲካ አቋም ከሳቸው ጋር መነገድ የዛለውን ክንዳቸውን ማፈርጠም በመሆኑ ኢህአዴግ እንዳልተዋጠለት የሚጠቁሙት ዲፕሎማቱ “ፖለቲካዊ ይዘቱ ኢኮኖሚያዊ ሽርክናውን ዋጋ ቢስ አድርጎታል” በማለት ስለማይነጣጠሉት ሁለት ተያያዥ ጉዳዮች አስረድተዋል።

ኳታር ሶማሊያ ላይ በነበራት አቋምና የገንዘብ ተሳትፎ ከኢትዮጵያ ጋር የነበራት የዲፕሎማሲ መስመር ከመቋረጡም በላይ “ለሶማሊያ ጉዳይ አባቱ ነኝ” ይሉ በነበሩት አቶ መለስ ክፉኛ ተዘልዝላ ነበር። ያ ሁሉ አልፎ ዛሬ በኢንቨስትመንት ስም እርቅ አውርዳ የገባቸው ኳታር በጀመረችው ድርድር ኢህአዴግ ያነሳው መሰረታዊ የህልውና ጥያቄ አላላውስ ብሏታል።

ተቀማጭነታቸው ሎንደን የሆነ የጎልጉል ምንጭ እንዳሉት የኢህአዴግ ለመደራደሪያ ቅድመ ሁኔታ ያስቀመጠው አጀንዳ ኤርትራ ውስጥ የሚንቀሳቀሰውን የትግራይ ህዝባዊ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ /ደሚት/ ታጣቂ ሃይሎች ተላልፈው እንዲሰጡት ወይም ወደ ትግራይ ድንበር እንዲገፉለት ነው።

ቀደም ሲል የትግራይ ነጻ አውጪ ድርጅት ህወሃት አካል የነበሩት እነዚህ ክፍሎች “ኤርትራ ውስጥ ታግተው የተቀመጡ”  ሃይሎች ስለመሆናቸውና ከ30 እስከ 40 ሺህ የሚደርስ ወታደር እንዳላቸው ለህወሃት ቅርበት ባላቸው የተለያዩ መገናኛዎች መዘገቡ ይታወሳል። በገለልተኛነታቸው የሚታወቁ መገኛዎችም ቢሆኑ የደሚት ሃይል ከአርበኞች፣ ከቤንሻንጉል፣ ከጋምቤላ፣ ከአማራ፣ ወዘተ ብረት አንጋቢዎች ጋር በጥምረት ለመሥራት መዘጋጀቱንና ይህም ሁኔታ ለህወሃት ስጋት እንደሚሆን አመልከተው ነበር።

ከኢህአዴግ የሚወጡ የምርመራ መረጃዎች እንደሚያሳዩት ህወሃት ደሚትን እየፈራ ነው። ደሚት “በኤርትራ የታገተ ሃይል ነው” በማለት የድርጅቱን ሃይል ለማጣጣል ቢሞከርም፣ የደሚት ሃይል እንደሚባለው አለመሆኑንን የሚያረጋግጡ መረጃዎች አቶ መለስ በህይወት እያሉ ቀርቦላቸዋል። ከዚያ በኋላ ነበር ደሚት ጥንካሬው እንዳይጎለብት ህወሃቶች መስራት የጀመሩት።

በወቅቱ ከኢህአዴግ ጓዳ ያፈተለኩ መረጃዎች እንደሚጠቁሙት ኢትዮጵያ አሰብን ለመጠቀም የሚያስችላት ድርድር ተጀምሮ ነበር። በስዊድን የሚኖሩ የጎልጉል ምንጭ የሆኑ የኤርትራ ተወላጅ ከዓመት ከስድስት ወር በፊት የአሰብ ወደብ እንዲታደስና ስራ እንዲጀምር ተወስኖ እንደነበርና ስራው ሲጀመር ስራ አቁመው የነበሩ ሰራተኞችና አገልግሎት አቋርጠው የነበሩ ድርጅቶች ስራቸውን እንዲጀምሩ መመሪያ ተሰጥቶ እንደነበር ያስታውሳሉ። ስራው አሁን በምን ደረጃ እንደሚገኝ ለጊዜው መረጃ እንደሌላቸው ተናግረዋል።

በተለያየ ወቅት አቶ መለስን ከቀድሞው ወዳጃቸው አቶ ኢሳያስ ጋር መልሶ ለማሻረክ ግብጽን ጨምሮ የተለያዩ አገሮች እንደተሳተፉ የሚገልጹ አሉ። የግብጽን የሸምጋይነት ሚና ጥርጥር ውስጥ በማስገባት አስተያየት የሚሰጡት ዲፕሎማት አሁን ኳታር ከጀመረችው ድርድር ጋርም ግብጽን ያያይዛሉ። ከኳታር ካዝና በሚወጣ ገንዘብ ሻዕቢያ የኢትዮጵያን ተቃዋሚዎች እንዲያደራጅ አጥብቃ የምትሰራውና የምትደጉመው ግብጽ አሁንም ቢሆን ኢትዮጵያና ኤርትራ አስተማማኝ ሰላም አውርደው በሰላም በጉርብትና እንዲኖሩ አትመኝም።

ኳታር ግን በቀድሞው አቋም መቀጠሉ አግባብ እንዳልሆነና በ2008 ከኢትዮጵያ ላይ እጇን እንድታነሳ ተጠይቃ ባለመቀበሏ የተሰበረው የዲፕሎማሲ ግንኙነት ለማቃናት መስራት የጀመረችው ከሊቢያው መሪ ጋዳፊ ሞት በኋላ እንደሆነ የሚገልጹ ክፍሎች ኳታር አሁን በጀመረችው “የትልቅ አገር ነኝ” ስሜትና በአፍሪካ ቀንድ ጂኦ ፖለቲካ ላይ ያላት ሚና መጎልበት ኢትዮጵያን መወዳጀት ብቸኛው አማራጯ እንደሆነ ይናገራሉ።

ሻዕቢያ እየከሰመ ሲሄድ ኢህአዴግ በሌላ በኩል በአፍሪካም ሆነ በዓለም ደረጃ ማደጉ ለንግድና ለፖለቲካ ዝናዋ ኢህአዴግን መወዳጀት አማራጭ የሌለው ጉዳይ የሆነባት ኳታር ሩጫዋ በጊዜ የተኮላሸው ከኢህአዴግ ወገን በተነሳ “የማይታሰብ” በተባለ ጥያቄ ነው። የደሚት የጦር ሃይል ተላልፎ እንዲሰጠው ወይም ወደ ኢትዮጵያ ድንበር እንዲገፋለት የተየቀው ኢህአዴግ ይህ እስካልሆነ ድረስ ከሻዕቢያ ጋር አንድ መቀመጫ ላይ ተቀምጦ ለመነጋገር አለመቻሉ ለኳታር ሽምግልና የመጀመሪያውና ሊመለስ ያልቻለ ፈተና ሆኗል።

ከድሮ ጀምሮ አድብታ የኢትዮጵያን ተቃዋሚዎች በመርዳት የምትታወቀው ግብጽ ኢህአዴግ በፈለገው መልኩ ድርድሩ ሊካሄድ እንደማይችል አቋም ይዛ እየሰራች እንደሆነ፣ ለዚህም ሲባል ከአንዳንድ የተቃዋሚ ሃይሎች ጋር ለመነጋገርና በሻዕቢያ አማካይነት ድጋፍ ለመስጠት ፍላጎት ማሳየቷን የጎልጉል ምንጭ የሆኑት ዲፕሎማት አስረድተዋል። ዲፕሎማቱ በደፈናው ከመናገር ውጪ ግብጽን ያነጋገረቻቸውን የተቃዋሚ ሃይሎች አልዘረዘሩም።

ኳታር የምጽዋን ወደብ በሊዝ ከመያዟ በተጨማሪ ለአሰብ ወደብ የነዳጅ ማጣሪያ ማደሻና ለወደቡ ስራ ማስቀጠያ ድጋፍ ማድረጓ አይዘነጋም። ያለ ስራ ተቀምጦ የነበረው ወደብ ለስራ እንዲዘጋጅ የታሰበው ለማን ተብሎና ማን እንዲጠቀምበት ታስቦ ነው ሚለው ጉዳይ ፖለቲካዊ ውሳኔ የሚጠይቅ አብይ ጉዳይ ከሆነ ዓመት ከስድስት ወር አስቆጥሯል። ኢህአዴግ የሚደጉመው የኤርትራ የሽግግር መንግስት አዲስ አበባ መቋቃሙም የሚታወስ ነው።


Injustice in Afar Region of Ethiopia is injustice in Germany

$
0
0

Afar Human Rights Statement

We learned from reliable sources that the dictator and President of Afar Regional State in Ethiopia, Mr Ismail Ali Sirro is currently… The Core of Human Rights violation Areas in Afar Region of Ethiopiavisiting Berlin, the capital of Germany.

The Afar people in Ethiopia have suffered a gross human rights violation during Mr Ismail Ali Sirros leadership. The number of people detained without fair trial has dramatically increased the latest years; people have been displaced from their homes and many were killed coldblooded. As highest leader of the Regional State, all crimes and corruption is taking place under President Isamails leadership, hence he is accountable for atrocities and human rights violation committed in Afar Region.

The Afar people whose majority are pastoralists, have been displaced from their land without any alternative for subsistence; they have lost their livestock and are exposed for starvation as a result of land grabbing policy of Mr Ismails leadership. There are documented testimonies that confirm the Mr Ismail personally threatened people to leave their home to facilitate sugar cane commercial farming, where those who refused were shot to death at spot. The order was given by the president of the region. Hence the crime committed by Mr Ismail Ali Sirro and the EPRDF Regime in Ethiopia is defined as crimes against humanity which is in line with the mission of the International Criminal Court.

The rampant corruption taking place in Afar Region has made Mr Ismail and his wife Mrs Fatuma Abdalla from having nothing to multimillionaires in ten years period. Moreover, there is information that the stolen many from starving population has been placed in foreign banks in Europe, North America and Asia.

Afar Human Right Organisation has been systematically following and voicing about the suffering, killings and detention of the voiceless Afar pastoralist. We believe that it’s unacceptable that dictators and murders are allowed to live in luxury in democratic countries like Germany. Therefore injustice in Afar Region should be considered as injustice in Germany and elsewhere. Hence, we appeal to German authorities and justice system to facilitate the handover of the criminals like Mr Ismail to the International Criminal Court.

Copy to:

  • Madame Sabine Leutheusser-Schnarrenberger, German Federal minster of Justice
  • Mrs. Mireille Ballestrazzi, President of INTERPOL
  • Deutsche Welle, Amharic program
  • Voice of America, Amharic program

For further information contact: ahro2006@hotmail.com


በጄ/ል ከማል ገልቹ የሚመራው ኦነግ በሚኒሶታ ሕዝባዊ ስብሰባ ጠራ

$
0
0

small_alaabaa(ዘ-ሐበሻ) በብርጋዲየር ጄነራል ከማል ገልቹ የሚመራው ኦነግ ዓመታዊ ስብሰባውን በሚኒሶታ ጁላይ 7 ቀን 2013 እንደሚያደርግ ለዘ-ሐበሻ በላከው ጋዜጣዊ መግለጫ አስታወቀ። ድርጅቱ ጁላይ 7 በሚያደርገው ሕዝባዊ ስብሰባ ላይ ዘርና ጾታ ሳይለይ ማንኛውም ኢትዮጵያውያን እንዲታደሙ ጋብዟል..

ድርጅቱ በላከው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ የዘንድሮውን ስብሰባ ልዩ የሚያደገውን ምክንያት ሲገልጽ “ይህንን ስብሰባ ካለፉት ልዩ የሚያደርገው ማንኛውንም ኢትዮጵያዊ ወይም ብሔር እና ብሔረሰቦች እንዲሁም ሕጋዊ ከሆኑ ተቃዋሚዎች ጋር በመተባባር የወደፊት የኢትዮጵያን ህልውና እውነተኛ የዲሞክራሲ የሕግ በላይነት የማንኛውም ግለሰብና ድርጅት መብት የሚከበርባት አገር ለመመስረት እንደሆነ ከኦነግ የፖለቲካ ለውጥ መረዳት ይቻላል” ብሏል።
“በዚህ ስብሰባ ላይ የሚገኙ ፡ የሐይማኖት አባቶች ፡ የፖለትካ ድርጅቶች ፡ መካሪ አዛውንቶችና ፡ ታዋቂ ግለሰቦች በወቅታዊ ኢትዮጵያ ጉዳዮች ላይ ለመመካካር በዚሁ ታሪካዊ ጥሪ ላይ ይገኛሉ፡፡” ያለው ኦነግ “ስለዚህ ፡ ማንኛውም ኢትዮጵያዊ ፡ ይህ ጉዳይ ይመለከተኛል የሚል ሁሉ ጁላይ 7 2013 ከቀኑ 1፡00 ፒኤም እንድገኙልን በትህትና እንጋብዛለን። ብሏል።
በብርጋዲየር ጀነራል ከማል ገልቹ የሚመራው ኦነግ ሕዝባዊውን ስብሰባ የሚያደርግበት አድራሻ የሚከተለው ነው።
አድራሻ : Best Western / Kelly Inn
161 St. Anthony Ave.
St. Paul , MN , 55103

July 7 , 2013 @ 1:00 Pm
አዘጋጅ ኮሚቴ
ጁላይ 7 የኦሮሞ ሰሜን አሜሪካ የስፖርትና የባህል ፌስቲቫል በሚኒሶታ የሚደረግበት ሰሞን በመሆኑ ከሌሎች ስቴቶች እና ሃገራት የሚመጡ እንግዶች በዚህ ስብሰባ ላይ እንዲታደሙ እድሉን ይፈጥርላቸዋል ተብሎ ይጠበቃል።


ጥሩነሽ ዲባባ የጎዳና ላይ ሩጫዎችን በፍጹም የበላይነት እየተቆጣጠረች ነው

$
0
0

ኢትዮጵያዊያኖቹ የረጅም ርቀት ሩጫ ሀያሎች ሀይሌ ገብረስላሴ እና ጥሩነሽ ዲባባ ጥሩነሽ ዲባባን ለውድድር ከመግባቷ በፊት አግኝታችሁ “የዛሬውን ውድድር ታሸንፊያለሽ ወይ?” …ብላችሁ ብትጠይቋት መልሷ ሁልጊዜም ተመሳሳይ ነው – “እግዚአብሄር ያውቃል” የሚል።

በየአመቱ ማንቼስተር ከተማ ውስጥ የሚካሄደው እና የዘንድሮው (26-05-2013) የ10 ኪሎ ሜትር የሩጫ ውድድር ከመጀመሩ በፊት ያገኟት ጋዜጠኞችም ለዛ ጥያቄያቸው “እግዚአብሄር ያውቃል” የሚለውን መልስ ነበር ያገኙት።

ኢትዮጵያዊያኖቹ የረጅም ርቀት ሩጫ ሀያሎች ሀይሌ ገብረስላሴ እና ጥሩነሽ ዲባባ

 

ጋዜጠኞች የሴቶቹ ውድድር ሲጀመር ለመገናኛ ብዙሀን በተዘጋጀው ቦታ ላይ ቁጭ ብለው ውድድሩን በተለያዩ መንገዶች እየተከታተሉ እንዳለ ጥሩነሽ ዲባባ አብረዋት ከሚወዳደሩት እና ውድድሩን እየመሩ ከነበሩት ሌሎች ተፎካካሪዎቿ ጋር ጥቂት አንድ ኪሎ ሜትር ያህል አብራ ከሮጠች በኋላ ለብቻዋ ተገንጥላ ወደፊት ስትወጣ ያየ አንድ ጋዜጠኛ ከመቀመጫው ብድግ ካለ በኋላ ጮክ ብሎ “[ጥሩነሽ] ዲባባ እግዚአብሄር ያውቃል ብትልም እሷም ምን እንደሚሆን እና ውድድሩንም እንደምታሸንፍ ታውቃለች” አለ።

በአለፈው ሚያዚያ ወር በተካሄደው የለንደን ማራቶን ላይ የመጀምሪያዋ የሚሆነውን የማራቶን ውድድሯን ታደርጋለች ተብሎ ሲጠበቅ በሚያስቆጭ ሁኔታ በጉዳት ምክንያት ሳትሳተፍ የቀረችው ጥሩነሽ በጎዳና ላይ ውድድሮችም ልክ እንደትራክ ውድድሮች ሁሉ ትኩረቷን ከሰጠች ማንም ሊያቆማት እንደማይችል በማንቼስተሩ የታላቁ 10 ኪሎ ሜትር ሩጫ ውድድር ላይ አሳይታለች።

“ወደዚህ [ማንቼስተር] የመጣሁት የቦታውን ሪከርድ ለመስበር አስቤ ነበር” ያለችው ጥሩነሽ ውድድሩ ተጀምሮ አንድ ኪሎ ሜትር ያህል ከመሪዎቹ አትሌቶች ጋር አብራ ከሮጠች በኋላ ከመሀል ድንገት ውልቅ ብላ በመውጣት ከፊት ሆና ሩጫውን በራሷ ሂደት መምራት ስትጀምር በርግጥም በቀጥታ ለአንድ አላማ ብቻ ወደላንክሻዬሯ ከተማ እንደመጣች መረዳት ይቻላል።

የእርሷ መውጣት አብረዋት ሲሮጡ የነበሩትን ሯጮች በሙሉ ከመረበሹ የተነሳ ለመከተል ሲሞክሩ በተፈጠረ መተራመስ አንድ አትሌት ስትወድቅ ጥቂቶች ደግሞ የአሯሯጥ ዘይቤያቸውን በተወሰነ መልኩ አጥተው ነበር። ከጀርባዋ ምን እንደተፈጠረ የማታውቀው እና ወደፊት ብቻ ትገሰግስ የነበረችው ጥሩነሽ የእግር አጣጣሎቿ እና ፊቷ ላይ ይታይ የነበረው መረጋጋት የልምምድ እንጂ የፉክክር ሩጫ ላይ ያለች አትመስልም ነበር።

የርቀቱን ግምሽ ያህል ማለትም አምስት ኪሎ ሜትሮች ያህል እንደሮጠች በሁለተኛነት በጋራ ይከተላት ከነበረው ቡድን በ38 ሰከንዶች ያህል ወደፊት ርቃ የነበረ በመሆኑ ውድድሩን በስፍራው ተገኝተው እና በቴሌቪዥን መስኮቶች ሲከታተሉ የነበሩ የአለም እንኳን ባይሆን የስፍራውን ክብረወሰን እንደምትስበር በርግጠኛነት መናገር ጀመሩ።

በርግጥ በቶሎ አፈትልካ መውጣቷንም ትክክለኛ ውሳኔ እንዳልሆነ የተናገሩም ነበሩ – ምንም እንኳን ቁጥራቸው እጅግ በጣም ጥቂት ቢሆንም። ጥሩነሽ ግን ያንን ያደረገችበት ምክንያት ነበራት።

የመጀምሪያው ኪሎ ሜትር ያዘገመ በመሆኑ “ከመጀመሪያው ካልሄድኩ የቦታውን ሰአት ለመስበር አይቻልም። አሯሯጭም (pace maker) ስለሌለ የግድ ራሴ ለመሄድ ወሰንኩ” ያለችው ጥሩነሽ በርግጥም ያ በቶሎ መውጣቷ የሩጫውን ፍጥነት በፈለገችው መንገድ እንድታስኬድ ያደረጋት ከመሆኑ በተጨማሪ የተፎካካሪዎቿ በጣም ወደኋላ መቅረት ትኩረቷን ሰአት እና የሯሷ አሯሯጥ ላይ ብቻ እንድታደርግ አስችሏታል።

የመጀመሪያውን አምስት ኪሎ ሜትር በ15 ደቂቃ ከ40 ሰከንድ የሮጠችው ጥሩነሽ በሀገሯ ልጅ ብርሀኔ አደሬ ከሰባት አመት በፊት የተመዘገበውን 31 ደቂቃ ከ07 ሰከንድ የሆነ የታላቁ ማንቼስተር ሩጫ ውድድር ክብረወሰንን ለማሻሻል ፍጥነቷን በሁለተኛው ግማሽ መጨመር እንዳለባት በመገንዘቧ ሁለተኛውን አምስት ኪሎ ሜትር በአስደናቂ ፍጥነት መሮጧን ተያያዘችው።

ያ ጥረቷም እንዳሰበችው በመሄዱ ሁለተኛውን ግማሽ አምስት ኪሎ ሜትር በሚያስደንቅ ሁኔታ በ15 ደቂቃ ከ 09 ሰከንድ በሆነ ጊዜ በመሮጥ የብርሀኔ አደሬን የስፍራውን ክብረወሰን አሻሽላ በ30 ደቂቃ ከ49 ሰከንድ በሆነ ጊዜ በማጠናቀቅ አሸነፈች።

በ10 ኪሎ ሜትር የሩጫ ውድድር በታሪክ 11ኛውን ፈጣን ሰአት ያስመዘገበችው እና በአለፈው መስከረም ወር ለመጀመሪያ ጊዜ በግማሽ ማራቶን ተወዳድራ ያሸነፈችው የሶስት ኦሎምፒክ ወርቅ ሜዳሊያዎች ባለቤቷ ጥሩነሽ ዲባባ ምንም እንኳን ሙሉ ለሙሉ ባይሆንም ወደጎዳና ውድድሮችም እየገባች እንደሆነ በቅርቡ ያደረገቻቸው ውድድሮች እና ውጤቶቿ ይመሰክራሉ።

“ሙሉ ለሙሉ ወደ አስፋልት ውድድር ባልገባም በሚቀጥለው አመት የለንደን ማራቶንን ለመሮጥ አስቤያለሁ” የምትለው ጥሩነሽ አሁን ቀዳሚው ትኩረቷ የፊታችን ነሀሴ ወር በሩሲያዋ ዋና ከተማ ሞስኮ አስተናጋጅነት የሚካሄደው 14ኛው የአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና እንደሆነ ነው የምትናገረው።

ከስድስት አመት በፊት በጃፓኗ ኦሳካ ከተማ አስተናጋጅነት በተካሄደ የአለም ሻምፒዮና ላይ ከተሳተፈች እና በ10 ሺህ ሜትር የወርቅ ሜዳሊያ ባለቤት ከሆነች በኋላ በርሊን እና ዴጉ ላይ በተካሄዱት የአለም ሻምፒዮናዎች ላይ በጉዳት ምክንያት በሚያስቆጭ ሁኔታ ያልተሳተፈችው ጥሩነሽ፣ በሞስኮው የአለም ሻምፒዮና በእርግጠኛነት 10 ሺህ ሜትር እንደምትሮጥ ብትናገርም፣ በ5 ሺህ ሜትር ስለመወዳደሯ ግን እርግጠኛ እንዳልሆነች ገልጻለች። ጥሩነሽ ዲባባ ከፍስሀ ተገኝ ጋር ያደረገችውን ቃለ-ምልልስ ይሄንን ጽሁፍ በመጫን ያድምጡ።

ሀይሌ ገና ይሮጣል

በበርካቶች የምንጊዜም ታላቁ የረጅም ርቀት ሩጭ ተደርጎ የሚወሰደው ሀይሌ ገብረስላሴ በማንቼስተር ጎዳናዎች ላይ አምስት ጊዜ በአሸናፊነት ቢነግስም ዘንድሮ ግን ያሰበው አልተሳካለትም።

የወንዶቹ 10 ኪሎ ሜትሩ ሊጠናቀቅ አንድ ኪሎ ሜትር እስከሚቀረው ድረስ ከመሪዎቹ ጋር አብሮ ሲሮጥ የነበረው ሀይሌ ገብረስላሴ ከዛ በኋላ ግን አጨራረሱ ላይ ፍጥነቱን ሊቀይር ባለመቻሉ ውድድሩን ባሸነፈው ዩጋንዳዊው ኪፕሲሮ እና ሁለተኛ በወጣው ኬኒያዊው ዊልሰን ኪፕሳንግ ተቀድሞ ሶስተኛ ለመጨረስ ተገዷል።

ለምን ፍጥነቱን መቀየር እንዳልቻለ ሀይሌ ሲናገር “የፍጥነት ልምምድ አለመስራቴ ነው ምክንያቱ። እኔ የፍጥነት ልምምድ ብሰራ እግሬን ስለምታመም የምሰራው ኢንዱራንስ ብቻ ነው። ኢንዱራንስ ደግሞ ፍጥነትን ለመቀየር በቂ አይደለም” ነበር ያለው።

የታላቁ ማንቼስተር 10 ኪሎ ሜትር ሩጫ ውድድር ክብሩን እንደገና ለማስመለስ በቀጣዩ አመት ተመልሶ ሊወዳደር እንደሚችል ፍንጭ የሰጠው እና የቀድሞው የአለም የማራቶን ክብረወሰን ባለቤት፣ የሁለት ኦሎምፒክ ወርቅ ሜዳሊያዎች ባለቤት እና አራት ጊዜ በ10 ሺህ ሜትር የአለም ሻምፒዮን በመሆን ወርቅ ሜዳሊያዎችን ያጠለቀው ሀይሌ ገብረስላሴ፣ ሶስተኛ የወጣበትን የማንቼስተሩን ውድድር ለመጨረስ 28 ደቂቃ ሲወስድበት፣ ቀጣዩ እቅዱ የፊታችን መስከረም ወር የሚካሄዱት የበርሊን ማራቶን ወይም የታላቁ የሰሜን ሩጫ ውድድሮች ላይ መሳተፍ ነው።

ከአንዳንድ ጥቃቅን ጉድለቶች በስተቀር የመሮጥ አቅሙ አሁንም አብሮት እንዳለ የሚናገረው ሀይሌ ገብረስላሴ ሩጫን መሮጡን እንደሚቀጥል ነው በአጽኖት የገለጸው።

ሀይሌ ገብረስላሴ በስፖርቱ አለም ያለውን ተከባሪነት ለማየት የሚወዳደርባቸው ቦታዎች ሄዶ ከተመልካቾች ብቻ ሳይሆን አብረውት የሚፎካከሩት አትሌቶች እንኳን የሚሰጡትን ክብር እና አድናቆት ማየት ይበቃል።

እሁድ እለት ማንቼስተር ውስጥ የተካሄደውን የ10 ኪሎ ሜትር የሩጫ ውድድር ያሸነፈው እና በሩጫ ህይወቱ ለመጀመሪያ ጊዜ በአንድ የውድድር ቦታ ላይ ከሀይሌ ጋር መወዳደር መቻሉ ያስደሰተው ዩጋንዳዊው ሞሰስ ኪፕሲሮ ለሀይሌ ገብረስላሴ ያለውን ክብር እንዲህ ነበር የገለጸው፦

“ልጅ እያለሁ በ1992 እና 1993 ዓ.ም ስለሀይሌ እሰማ ነበር። እናም ከዛ ጊዜ ጀምሮ ከሀይሌ ጋር መሮጥ ምኞቴ እና ህልሜ  የነበረ ሲሆን እናም ዛሬ ያንን ህልም በማሳካቴ እጅግ በጣም ነው የተደሰትኩት። ሀይሌ ታላቅ አትሌት ነው” አለ ኪፕሲሮ። ሀይሌ ገብረስላሴ ከፍስሀ ተገኝ ጋር ያደረገውን ቃለ-ምልልስ ይሄንን ጽሁፍ በመጫን ያድምጡ።


ብአዴን ‹‹ሰለሞናዊ›› ስርወ መንግስት!? – (ሊያነቡት የሚገባ የአደባባይ ምስጢር)

$
0
0

በአንድ ወቅት ዜጋ መጽሔት ላይ ታትሞ የነበረና ለግንዛቤዎ ይጠቅምዎታል ብለን እንደገና ለዘ-ሐበሻ አንባቢዎች አቅርበናል።  በአንዳንድ የአገዛዝ ሥርዓቶች በሀብት፣ በመደብ፣ ወይም ዴሞክራሲያዊ ምርጫ፣ አልያም በዘር የተዋቀረ ሥርዓት ይኖራል… ለምሳሌ በአፄ ኃይለ ስላሴ ጊዜ የነበረው የስልጣን ፍልስፍና ከሰለሞን ስርዎ መንግስት የሚመዘዝ የዘር ሀረግ ባለቤት መሆንን ይጠይቅ እንደነበረ ሁላችንም የምናስታውሰው ነው፡፡ ከሰለሞን ስርዎ (Solomon Daynasty) መንግስት ውጭ ላሉና በዚያ የስልጣን ዘር ሀረግ ውስጥ ያሉ ሆነው በጉልበትም ይሁን በብልሃት ስልጣን ላጡት ስልጣን የሚሰጣቸው በጋብቻ ትስስር እንደነበረ ለማስታወስ የአፄ ኃይለስላሴ ልጆች ከማንና የት ተጋብተው እንደነበረ ማስታወሱ በቂ ምሳሌ ነው፡፡

 የብርሐኔ አበራ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ቤተሰብ አባላት አቶ በረከት እና አዲሱ

የብርሐኔ አበራ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ቤተሰብ አባላት አቶ በረከት እና አዲሱ ከፍ ብዬ የጠቀስኩትን የታሪክና የንድፈ ሀሳብ ማነፃፀሪያ ይዘን የኢህአዴግ አባል ድርጅት ስለሆነው ብአዴን የስልጣን ድልድልና ከሕወሓት በሚሰጣቸው መመሪያ ድርጅቱን በሞኖፖል አንቀው የያዙትን ግለሰቦች የጋብቻ ትስስር፣ በትጥቅ ትግል ዘመን ጊዜ የነበራቸው ተሳትፎን እንዲሁም ዛሬ ያሉበትን ሁኔታ እንደሚከተለው ላቀርብ ተከታተሉ፡–

በክልል ሶስት በዋግ ህምራ ዞን ብርሃኔ አበራ ስለሚባሉ ባልቴት ታጋይ ነው የማወጋችሁ፡፡ ለስሙ የዋግህምራ ዞን ኃላፊ (ሊቀመንበር) ልጃለም ወልዴ ሆኑ እንጅ የዞኑ ህቡዕ መሪ ብርሃኔ አበራ ናቸው፡፡ ይታሰር ያሉት ይታሰራል፤ ይፈታ ያሉት ይፈታል፤ ይባረር ያሉት ሁሉ ከስልጣን ላይ ይባረራል፡፡

ወይዘሮ ብርሃኔ አበራ ለመሆኑ ይኀን ሁሉ ገበሬ ኩሉ ስልጣን ከየት አገኙት? የስልጣን ምንጫቸውን የጨበጡት ከዚህ ቀጥሎ ዝርዝራቸውን በማቀርባቸው ‹‹ታጋይ›› ልጆቻቸው፣ እህቶቻቸውና አማቾቻቸው ወዘተ ነው፡፡ የብርሃኔ አበራ ልጆች1. መዝሙር ፈንቴ የብአዴን ማ/ኮ አባል የነበረ አሁን የተባረረ፤

2. አሰፋ ፈንቴ፡- የበረከት ስምኦን ሚስት/ሲቭል ሰርቪስ ኮሌጅ የምትማር፤

3. ገነት ፈንቴ፡- አንድ የሕወሓት የደህንነት ባለስልጣን ያገባች፤

4. የሺሀረግ ፈንቴ

5. አሸናፊ ፈንቴ

6. መላኩ ፈንቴ

7. አበባ ፈንቴ፡- የሟቹ ሙሉአለም አበበ ሚስት የነበረች፤ በአገር ውስጥ ጉዳይ የኢሚግሬሽን ቪዛ ኃላፊ የነበረች፤ (የብርሃኔ አበራ እንጀራ ልጅ)

8. አለሚቱ ፈንቴ፡- በክልል ሶስት የምክር ቤት አባል የነበረች፤ አሁን እንግሊዝ አገር ያለች (የብርሃኔ አበራ የእንጀራ ልጅ)

9. ኃይሉ ፈንቴ፡- የጢጣ ት/ቤት አስተዳደር

10. አድና ፈንቴ (የተሰዋች) የወይዘሮ ብርሃኔ አበራ ታጋይ እህቶች1. የሺ አበራ የጄኔራል ኃይሌ ጥላሁን ሚስት፣ ጦር ኃይሎች ሆስፒታል በኃላፊነት ቦታ የምትሰራ፤

2. ነጻነት አበራ፡- የታደሰ ጥንቅሹ (ካሳ) ሚስት ክልል ሶስት በፕሮፖጋንዳ ክፍል ውስጥ የምትሰራ፤

የብራሃኔ አበራ ታጋይ የልጅ ልጆች

1. ውዲቱ አጋዡ፤- መከላከያ ውስጥ የነበረች፤

2. ፍሬህይወት አጋዡ፡- የኢህአዴግ ቢሮ ውስጥ ያለች፣ የውዲቱ አጋዡና የፍሬህይወት አጋዡ እናት የብርሃኔ አበራ ታላቋ ልጃቸው ዋርቃ ናት፡፡ የብርሃኔ አበራ የእህት ልጆች1. እንወይ ገብረመድህን የጸረ ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር (የአዲሱ ለገሰ ሚስት የነበረች)

2. ቢያድጎ፤

3. የዋግህምራ አቃቢ ህግ ሹም-ወይዘሮ እንወይ ገ/መድህን የአንድ ወንድ ልጅና የሁለት ሴት ልጆች እናት ናቸው፡፡ የወ/ሮ እንወይ ልጆች አባት አቶ ብርሃኑ ነጋሽ ዛሬ ነዋሪነታቸውን አሜሪካ አገር ያደረጉ ሲሆን፣ ከባለቤታቸው ጋር የተለያዩት ወ/ሮ እንወይ ገና ወደትግል ሜዳ ከመግባታቸው በፊት ነበር፡፡ ወ/ሮ እንወይ

የብርሃኔ አበራ ቤተሰብን በጋብቻ የተዛመደው ታደሰ ካሳ (ጥንቅሹ)

የብርሃኔ አበራ ቤተሰብን በጋብቻ የተዛመደው ታደሰ ካሳ (ጥንቅሹ)

ወደ ትግል ከገቡ በኋላ ከአቶ አዲሱ ለገሰ ጋር አንድ ወር ላልበለጠ ጊዜ ጋብቻ መስርተው ነበር፡፡ የአሁኗ የአዲሱ ለገሰ ሚስት የሰቆጣዋ ታምር ተሻለ ነች፡፡ ወ/ሮ እንወይ በአሁን ሰዓት ትዳር የላቸውም፡፡ ወ/ሮ እንወይ ትግሉን ሙሉ በሙሉ የተቀላቀሉት ከ1978 ዓ.ም ወዲህ ነው፡፡ የማዕከላዊ ኮሚቴ አባል የሆኑት ኢህዴን ወደ ብአዴን ከተለወጠ በኋላ ነው፡፡ ምንም እንኳ በበረሃው ዘመን የነበራቸው የፖለቲካ ንቃት የኢህዴን ማእከላዊ ኮሚቴ አባል ሊያደርጋቸው የሚችል የነበረ ቢሆንም፣ ኢህዴን ከሕወሓት የፖለቲካ ፕሮግራም የገለበጠውን ‹‹ፊውዳሊዝም አስፈጊ ጠላታችን በመሆኑ (Threa-tening enemy) በፕሮግራማችን ውስጥ መስፈር አለበት›› የሚለውን አመለካከት ወ/ሮ እንወይ ሙሉ በሙሉ የኢትዮጵያ አብዮትና ደርግ ጠራርገው የጣሉት ስርዓት የሌለ ስለሆነ፣ ስለሌለ ፊውዳሊዝም መሰረታዊ የኢትዮጵያ ህዝቦች ጠላት ነው ብሎ ፕሮግራማችን ውስጥ ማስፈር የለብንም›› የሚል አቋም ነበራቸው፡፡ ይህ አቋማቸው እንዲያውም የኢህአፓን ፕሮግራም ተከታይ አስብሏቸው ስለነበረ ነው በጣባው ኮንፍረንስ የኢህዴን ማ/ኮ አባል ሆነው ሳይመረጡ የቀሩት፡፡

4. ሌላኛዋ የብርሃኔ አበራ የአክስት ልጅ፡- የአቶ ታምራት ባለቤት ሁለት ልጆቿን አሜሪካ ይዛ የገባችው ወ/ሮ ሙሉ ግርማይ ናት፡፡

የዚህ ቤተሰብ የእርስ በእርስ ግንኙነት ሁኔታ

በትጥቅ ትግሉ ዘመን ይህ ቤተሰብ እርስ በራሱ በጣም ይደጋገፍ ነበር፡፡ ከእንወይ ገ/መድህን በስተቀር እስከ 1983 እንወይ ገ/መድህን ከዚህ ቤተሰብ እንዲገለሉ ያደረጋት ታደሰ ጥንቅሹ ነበር፡፡ በ1975 ዓ.ም የኢህዴን የህቡዕ አባላት ተጋልጠው የህይወትና የአካል አደጋ ደርሶባቸው ነበር፡፡ ይህን የህቡዕ አባላት እንቅስቃሴ በጊዜው ይከታተለው የነበረው ታደሰ ጥንቅሹ ነበር፡፡ የእቡዕ አባሎቻችንን ያጋለጠችው እንወይ ነች ብሎ ስላስወራባት ነው እስከ 1983 በመጠኑም ቢሆን ከዚህ ቤተሰብ የተገለሉት፡፡

ሌላኛዋ የዚህ ቤተሰብ አባል ሆና ይኸን ያህል የጎላና እፍ እፍ የቤተሰብ ፍቅር ያልነበራት ወ/ሮ ሙሉ ግርማይ ነች፡፡ እንዲያውም ወደመጨረሻው አካባቢ የአንድ ቤተሰብ አባል ሆነው በባሎቻቸው የስልጣን ከፍና ዝቅ ማለት፣ በአኗኗርና በአለባበስ በወ/ሮ ሙሉ ግርማይና በሌላው ቤተሰብ አባላት ከፍተኛ አለመግባባት ተከስቷል፡፡

አቶ ታምራት ላይኔም ከብርሃኔ አበራ ቤተሰብ ጋር ይዛመዳሉ

አቶ ታምራት ላይኔም ከብርሃኔ አበራ ቤተሰብ ጋር ይዛመዳሉ

ከዚህም በላይ አቶ ታምራት የግንቦት 20 ትምህርት ቤት ይማሩ በነበሩ የዚህ ቤተሰብ አባላት ዘንድ ከፍተኛ ፈንጠዝያ ተፈጥሮ ነበር፡፡

ዘ-ሐበሻ ድረገጽን ሁልጊዜ ያንብቡ። በየሰዓቱ አዲስ ነገር አያጡም። በትጥቅ ትግሉ ወቅት የዚህ ቤተሰብ ተሳትፎና መስእዋትነትበመግቢያዬ የዘረዘርኳቸው የዚህን ቤተሰብ አባላት ዋና ዋናዎቹን ነው፤ እንጂ ጠቅላላ በብአዴን ውስጥ ያሉትን ኢህዴን ውስጥ የታገሉት በቁጥር 60 ናቸው፡፡ በትጥቅ ትግሉ ውስጥ የነበራቸውን ተሳትፎ በትክክል ማየት እንድንችል ከዚህ ቀጥዬ ስም ዝርዝራቸውን የማቀርብላችሁ በኢህአዴን ውስጥ እንደታጋይ ታቅፈው ጊዜው ይጠይቅ የነበረውን የትጥቅ ትግል ምላሽ ለመስጠት እንዲችሉ የወታደራዊ ስልጠና (ተአለም) ያልወሰዱትን ነው፡፡

1. እንወይ ገ/መድህን

2. ኃይሉ ፈንቴ

3. የሺሀረግ ፈንቴ

4. ገነት ፈንቴ

5. አሸናፊ ፈንቴ

6. አለሚቱ ፈንቴ

7. ብርሃኔ አበራ ከማስታውሳቸው የዚህ ቤተሰብ አባላት ከፊሎቹ ናቸው፡፡

ሁሉም ሰው መገንዘብ እንደሚችለው በአንድ የሽምቅ ውጊያ ስልታዊ ንቅናቄ ውስጥ የሚገኙ የድርጅት አባላት በሙሉ ትግሉ የሚጠይቀውን የወታደራዊ ስልጠና ወስደው ቢያንስ ራሳቸውን መከላከል በሚችሉበት ሁኔታ ላይ መገኘት አለባቸው፡፡ ሙያና ምንም አይነት የመጀመሪያ ደረጃ የውጊያ እውቀት የሌለው ታጋይ ጠላት ኃይሉን አጠናክሮ ወደ ድርጅቱ ቤዝ አምባ ሊገባ በሚዘጋጅበት ጊዜ ከእቃ ጋር አብሮ መሸሽ ነበር የመጨረሻ እጣ ፈንታው፡፡ ይህ በደፈናው የሚቀርብ የንድፈ ሀሳብ ትንተና ሳይሆን ኢህዴን ውስጥ በተግባር የታየ ሀቅ ነው፡፡ ይህ ቤተሰብ በትጥቅ ትግሉ ዘመን መሽጎ የኖረው ጠላት ይደርስበታል ተብሎ በማይገመተው የኢህዴን ቤዝ አምባ ውስጥ ነው፡፡ የትጥቅ ትግሉ የሚጠይቀውን የውዴታ ግዴታ ይህ ቤተሰብ ሊፈፅም ባለመቻሉ በተለይ በ1978 አካባቢ በሌላው የድርጅቱ አባላትና ይኸን ቤተሰብ ጉያው ውስጥ በሸጎጠው የኢህዴን ማ/ኮ አባል መካከል ከፍተኛ አለመግባባት ተፈጥሮ ነበር፡፡

በወቅቱ ይነሱ የነበሩ ጥያቄዎች ይህ ቤተሰብ ለመስእዋትነት ዝግጁ አይደለም፤ የሌላውን የድሀ ገበሬ ልጅ ላብና ደም እየጋጠ መኖር የሚፈልግ ነው፤ የኢህዴን ማ/ኮ ለዚህ ቤተሰብ (የነማዘር ቤተሰብ) አባላት ልዩ እንክብካቤ ያደርጋል የሚሉ የሰላ ሂሶች ነበሩ፡፡

ከላይ ስለዚህ ቤተሰብ የገለፅኳቸውና ያነታርኩ የነበሩ ጥያቄዎች ምን ያክል ትክክል መሆናቸውን ለማየት ከ60 የቤተሰብ አባላት ውስጥ ስንቶቹ የህይወት፣ ስንቶቹ የአካል መስእዋትነት ከፈሉ የሚለው ጥያቄው በትክክል ይመልሰዋል፡፡ ከዚህ ቤተሰብ ውስጥ የህይወት መስእዋትነት የከፈለችው አድና (ታሪክ) ፈንቴ ብቻ ነች፡፡

በጥይት የቆሰሉ

1.ነፃነት (አምራየ) አበራ በ1977 ዓ.ም ቀስታ ውስጥ ልዩ ስሙ አቡነይ ጋራ በተባለ ቦታ በተካሄደ ውጊያ ዳሌዋ ላይ መጠነኛ የመቁሰል አደጋ የገጠማት ሲሆን በሌላ ውጊያ በጌምድር ክፍለ ሀገር ደጎማ ከተማ በተካሄደ ውጊያ ቀኝ እጇን በብርቱ ቆስላለች፡፡

2.መዝሙር ፈንቴ በ1977 ዓ.ም ዋግ አውራጃ ልዩ ስሙ ተላቁዝቁዛ ይገኝ ከነበረው የኢህዴን ቤዝ አምባ ከራሱ ከመዝሙር ፈንቴ ቤተሰብ ጥይት እግሩ ላይ የመቁሰል አደጋ ገጥሞታል፡፡ ሲጠቃለል ከስድስት ግለሰቦች ውጪ በዚህ ቤተሰብ ላይ የደረሰበት የአካልም ይሁን የህይወት መስእዋትነት የለም፡፡ ስለዚህ የኢህዴን አባላት ለዚህ ቤተሰብ መስእዋትነት ከፈሉ እንጂ ይህ ቤተሰብ ለኢህዴን የከፈለው መስእዋትነት ኢምነት ነው፡፡ እንዲያውም በደም ጎጆ በተገነባ ቤት ውስጥ ተንደላቀው ኖሩ እንጂ ስለነ ‹‹ማዘር›› (ብርሃኔ አበራ) ቤተሰብ ሲነሳ እኔም ጆሮ ዳባ ልበስ ብዬ የማሳልፈው ሀቅ አለ፡፡ የዚህ ቤተሰብ አንድ የእህል ወፍጮ ከቤተሰቡ በላይ እንዳገለገለ መርሳት እኔም የበላሁትን ቂጣ መካድ ይሆንብኛል፡፡

(ዘ-ሐበሻን ያንብቡ0


አባይ ሊያለማን ወይስ ሊያጠፋን?

$
0
0

ዘጋጅ ለኢትዮጵያ ፍቅር ከቃሊቲ  የዐባይ ሥረ_መሠረትና የሕዳሴው ግድብ ማነጣጠሪያ እነሆ!  . ጥናቱ የተፈጸመው ሚያዚያ 2003 (2011 እ ኤ አ) ነው። . አቅርቦት የፀሐፊው ትክክለኛ ቅጂ (በአቀራረባዊ ጥንቅር)    መነሻ  .የጊዜው የኢትዮጵያ ጉዳይ ሆኖ የቀጠለውና ሕዝቡም የጠየቁትን እያደረገ ያለበት የሚሌኒየሙ ታላቅ የዐባይ ግድብ እንደተነገረው፤… የሚገደበው ከሱዳን ድንበር 17 (አሥራ ሰባት) ኪሎሜትር ባለ ቀረቤታ በዐባይ ወንዝ ላይ ነው።

Blue Nile Falls 02.jpg

የሕዳሴው ግድብና ዐባይ፣ የሚሊኒየሙ ዐባይ ተጋቦት

 

  • ግድቡ ወደ 62 ቢሊዮን ሜትር ኩብ ውኃ የመያዝ አቅም አለው።
  • የውኃው መጠን የጣና ሐይቅ ከሚይዘው ውኃ እጥፍ ይሆናል።
  • በሚቋረው ውኃ 5250 (አምስት ሺ ሁለት መቶ ሃምሳ) ሜጋ ዋት የኤሌትሪክ ኃይል ሊመረት ታቅዷል። የሚመረተው የኤሌክትሪክ ኃይል ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ለሱዳንና ለግብፅም ሊሸጥ ታስቧል። ይህ ግንባት 80 ቢሊዮን ብር ይፈልጋል።
  • ገንዘቡ በግብፅ ተፅዕኖ ሳቢያ የውጭ ብድር ወይም ዕርዳታ እንዳያገኝ ሰለሚጠናወት፤ በኢትዮጵያ ሕዝብ የመዋጮና ቦንድ ሺያጭ ሊሸፈን ነው ተብሏል።
  • ለሕዝቡም ታሪካዊ ተዐምር ሊሠራ እንደሆነና የልማት ሁሉ አንጋፋ እንደሆነ ተነግሮት የቻለውንና ያልቻለውንም ከማድረጉ በላይ ለሃገር የሚበጅ ልማታዊ ድንቅ እንደተፈጠረ ተበስሮለታል።
  • ባለፈው ሚያዚያ (April) 2013 እ ኤ አ ወር ማብቃያ አካባቢ በወጣው ዜና ደግሞ (ይህ ጥንቅር ከቀረበ ከሁለት ዓመት በኋላ መሆኑ ነው። ቻይና ለሚሌኒየሙ ግድብ ግንባታ 1.5 ቢሊዮን ዶላር ልታበድር ነው ተብሏል።

ታዲያ ግብፅና ሱዳን ምነው ዝም አሉ?

እኮ ቢጠቅማቸውማ ነው ዝምታቸው፤ የዐባይ ልጅ ይህ እንዴት ያየዋል?

ዝርዝሩን ምድር ላይ ያለውን እንየው፤

አባይ (ናይል)እየተባለ የሚጠራው በዓለም ረዥሙ ወንዝ፣6671 ኪሎ ሜትር እርዝማት ሲኖረው፣ከዘጠኝ አገሮች ይመነጫል።ግብፅ ምንም የምታመነጨው  የውኃ አስተዋፆ የላትም። ሆኖም በናይል ውኃ በከፍተኛ ደረጃ ተጠቃሚ አገር ናት። ግብፅ 100% የሰሐራ በረሃ አካል በመሆኗ በሜዲቴሪንያን አካባቢ ጥቂት ዝናብ ጠብ ከማለቱ ሌላ ከዓመት ዓመት ዝናብ አይጥልም።

በሌላ በኩል ደግሞ ከሁሉም የናይል ተፋሰስ አገሮች ይበልጥ የ80% በመቶ ከአባይና ከሌሎች የኢትዮጵያ ወንዞች የሚገኘው ውኃ አባይን ይገልጸዋል። በጠቅላላው የናይል ወንዝ 74 ቢሊዮን ሜትር ኩብ ውኃ በዓመት ሲሰጥ ከዚህ ውስጥ ከኢትዮጵያ የሚገኘው የውኃ ድርሻ መጠን 54 ቢሊዮን ሜትር ኩብ ውኃ ነው። የዚህ ሁሉ ውኃ ምንጭ ኢትዮጵያ ስትሆን፤እንደ ሱዳንና ግብፅ እምነት ጥቂት ውኃ እንኳን ለመጠቀም መብት የላትም።ሌሎቹንም የናይል ውኃ አመንጪና ባለቤት የራስጌ አገሮችን በማግለል መብታቸውን ገፍፈው ሱዳንና ግብፅ ተከፋፍለውታል።

እ ኤ አ 1959 ዓ ም በተፈራረሙት ስምምነት መሠረት ግብፅ 55.5 ቢሊዮን ሜትር ኩብ ፤ሱዳን ደግሞ 18.5 ቢሊዮን ሜትር ኩብ ውኃ ይወስዳሉ።በተለይ ግብፅ የውኃው ዋና ባለቤት እራሷን አድርጋ በመቁጠር አመንጪዎቹን የራስጌ አገሮች ለአነስተኛ የውኃ ጠቀሜታ እንኳን ፈቃጅ መሆን አለብኝ ባይ ናት። ለዚህም ኢትዮጵያን ማዳከም ወይንም ማጥፋት ተልኮዋ ሆኗል።

የአባይ ጠቀሜታ

  • ግብፅና ሱዳን ፍፁም ተጠቃሚዎች ሲሆኑ፤ በተቃራኒው የውኃ መነሻ የሆነችው ኢትዮጵያ ተጠቃሚ አልሆነችም።
  • ግብፅ 3.0 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በመስኖ ታለማለች።
  • ሱዳን 1.8 ሚሊዮን ሄክታር እንደዚሁ በናይል ወሰኗ ታለማለች።

ኢትዮጵያ አትጠቀምም በመስኖ አለማችም።

የግብፅ በረሃ በናይል ውኃ በሺ ዓመታት የሚቆጠር የመስኖ እርሻ ልምድ ለምቶ እራሳቸውን ከመመገብ አልፈው የዳበረ ኢኮኖሚ ገንብተውበታል። አባይን ወደ ምዕራብ የግብፅ በረሃ ቀይሰው በመውሰድ ተጨማሪ 1.2 ሚሊዮን ሄክታር በረሃ ለማልማት መንቀሳቀስ ከጀመሩ ቆይተዋል።በዚህ ምዕራባዊ ከተማ ከአንድ ሚሊዮን ሕዝብ በላይ የሚኖርበት ዘመናዊ ከተማ እየተገነባ ነው። የሲናይንም በረሃ ለማልማት በዓመት 4.5 ቢሊዮን ሜትር ኩብ የአባይ ውኃ የሚያስተላልፍ ቧንቧ ዘርግተዋል። የመስኖ ሥራቸውን ለማካሄድ ያስቻላቸውም ታላቁ የአሳዋን ግድብ ነው።ግድቡ 162 ቢሊዮን ሜትር ኩብ ውኃ የማከማቸት አቅም አለው። በክረምት ወራት ከኢትዮጵያ የሚፈሰውን ውኃ አጠራቅመው በመያዝ በሰከንድ 1500 ቶን ውኃ እየለቀቀ በረሃውን ያለማል። ይህም ሆኖ በግብፆች ዕቅድ ተጨማሪ በረሃ ለማልማት 15ቢሊዮን ሜትር ኩብ ውኃ ተጨማሪ ያስፈልገዋል። ለዚህም የተለያዩ ፕሮጀክቶች አስጠንተዋል። ጥናቱ ተጠናቆ ግንባታውም ተጀምሮ የነበረው አንዱ ፕሮጀክት በደቡብ ሱዳን ክልል ያለው የጀንገሌ ካናል ፕሮጀክት ነበር። የናይል ወንዝ በደቡብ ሱዳን ሱድ እየተባለ የሚጠራውን ረባዳና ረግረግ ሰፊ መሬት አቋርጦ ያልፍል።ወንዙ በክረምት ከአፍ እስከ ገደብ ሲሞላ ግደቡን ጥሶ ለጥ ወዳለው ሜዳ መፍሰስ ይጀምራል።ግድቡን አልፎ የተንጣለለው ውኃ ተመልሶ ወደ ወንዙ ሊገባ ስለማይችል፤እንደተንጣለለ ይደርቃል።ይህም በፀሐይ ሙቀት እየተነነ ይጠፋል። ታዲያ ግብፃውያን የጀንግሌ ካናልን ፕሮጀክት ያጠኑትና ሥራውንም የጀመሩት በትነት የሚባክነውን ውኃ በማግኘት የናይልን ውኃ መጠን 10% ከፍ ለማድረግ ነበር።

1ኛ የጀንግሌ ካናሉ ግንባታ የተጀመረው የደቡብ ሱዳን ነፃ አውጪ ድርጅት የነፃነት እንቅስቃሴ በጀመረበት ወቅት ስለነበር ፕሮጀክቱ ሳይገፋ አገራችን ይደርቃል፣ ኢኮሎጂውም ይለወጣል፣ በማለት ኤስ .ፒ .ኤል. ኤም ፕሮጀክቱ ላይ ጥቃት በመሰንዘር አጨናገፈው።

2ኛ ተጨማሪ ውኃ ለማግኘት ያስችላል ተብሎ የተጠናው ሌላው ፕሮጀክት ደግሞ በኢትዮጵያ ትልልቅ ግድቦች መገንባትና የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት ነው። ግብፅ በረሃማ አገር በመሆኗ የፀሐይ ሙቀት ያጠቃታል፤በዚያ የተነሣ በአገራቸው ከተገነባው ቃላቁ የአስዋን ግድብ በፀሐይ ሙቀት ብቻ በትነት ከተከማቸው ውኃ 12% ይባክናል።ይህ በጣም የሚያሳስባቸው ጉዳይ ነው። ብዙ ውኃ ሊይዝ የሚችል ሌላ ትልቅ ግድብ ለመገንባት የሚቻለበት ቦታ ስለሌላቸው ተጨማሪ ውኃ በሃገራቸው ውስጥ ለማከማቸት ያላቸው ዕድል በጣም የመነመነ መሆኑን ተረዱት። በዚህ የተነሣ ጥረታቸውን በኢትዮጵያ ላይ አድርገዋል።በደጋው ኢትዮጵያ ትላልቅ ግድቦች ለገነቡባቸው የሚችሉበት ቦታዎች በርካታ ናቸው። በሚገደቡት ግድቦች የሚከማቸው ውኃ በትነት የመባከን አደጋ አያጋጥመውም።ውኃው ሳይባክን ለብዙ ጊዜ ተጠብቆ የመቆየት ዕድል አለው።ኤሌክትሪክ ለማምረት እየተባለ ከሚገነቡት ግድቦች ከሚለቀቀው ውኃ ምን ያህል ተጨማሪ ውኃ ሊገኝ እንደሚችል ግብፃውያን አስጠንተው አውቀውታል።በጥናቱ መሠረት በኢትዮጵያ 23 ትላልቅ ግድቦችን በአባይ መጋቢ ወንዞች ላይ መገንባት የሚቻልባቸው ቦታዎች ተለይተው ታውቀዋል፤መነሻ ጥናት ተካሄዶባቸዋል፤እንደጥናቱ በእነዚህ ቦቻዎች በሚገነቡ ግድቦች ብዙ ቢሊዮን ሜትር ኩብ መጠን ያለው ውኃ ይከማቻል።ከዚያም በያንዳንዱ ግድብ የሚተከሉት የኤሌክትሪክ ማመንጫ ተርባይን ለማሽከርከር ውኃ ይለቀቃል።የአባይ ወንዝ በሚሞላበት ወቅት የአገራችንን ድንበር አልፎ ሱዳን ሲገባ የሚያፈሰው የውኃ መጠን 400 ሜትር ኩብ ውኃ በሰኮንድ ሲሆን አባይ ደረቀ በሚባልበት በበጋው ወቅት ደግሞ 4 ሜትር ኩብ ውኃ በሰኮንድ ይፈሳል። ልዩነቱን አጢኑት በበጋው የሚፈሰው በአንድ መቶ ጊዜ ይቀንሳል።ከዚህ ሁኔታ መገንዘብ የሚቻለው በሱዳንም ሆነ በግብፅ በክረምት ወራት ከኢትዮጵያ የሚፈስላቸውን ውኃ ገድበው በመያዝ በበጋ ወራት እየለቀቁ መጠነኛ የእርሻ ሥራ ከማካሄድ ውጭ የመስኖ እርሻ እንቅስቃሴ አያካሄዱም ማለት ነው። በኢትዮጵያ ግድቦች ተገንብተው ውኃ እየለቀቁ ተርባይኖችን ማሽከርከር ሰንጀምር ግን ይህ ሁኔታ ሙሉ በሙሉ ይለወጣል። ከተጠኑት 23  የግድብ ሥፍራዎች ውስጥ አነስተኛ ውኃ የማከማቸት አቅም ያላቸው አራት ግድቦች ቢገነቡና በየአንዳንዱ ግድብ ኤሌክትሪክ ለማመንጨት፤ አራት አራት ተርባይኖች ቢተከሉና እነዚህን ተርባይኖች ለማሽከርከር 20 ሜትር ኩብ ውኃ በሰኮንድ ቢለቀቅ ሱዳንና ግብፅን አባይ ሲደርቅ 80 ሜትር ኩብ ውኃ በሰኮንድ ያገኛሉ ማለት ነው።

ኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ብቻ ለማምረት ፈልጋ ግድብ ከገደበችና ተርባይኖችን ለማሽከርከር አንድ ጊዜ ውኃ መልቀቅ ከጀመረች በኋላ ውኃውን በከፊል ወይም በሙሉ ለመስኖ እርሻ ልማት መጠቀም ብትሞክር የሱዳንና የግብፅን ሕዝቦች በረሃብ ፈጀች፤ የአባይን አቅጣጫ ቀየረች፤ በሚል ሰበብ ለጦርነት መነሳታቸው አይቀርም። በዓለም አቀፍ ደረጃም እንድተወገዝ ፓለቲካዊና ኤኮኖሚያዊ ጫና እንዲወድቅባት ያደርጋሉ።

በዚህ ምክንያት በአባይ ወይም በአባይ ገባር ወንዞች ላይ ግድብ ገንብተን የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት ከመጀመራችን በፊት ውሎ አድሮ ኢትዮጵያን የሚጎዳ ሁኔታ አለመፍጠሩን ከብዙ አቅጣጫዎች መመርመር አለብን። እንደሚታወቀው የኤሌክትሪክ ኃይል ለማንኛውም አገር ዕድገትና ሥልጣኔ ወሳኝ ኃይል ነው። ኃይል እንደመሆኑ ሁሉ ኢትዮጵያም የኢሌክትሪክ ኃይል በከፍተኛ ደረጃ ያስፈልጋታል። በቀላል መንገድ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማግኘት ደግሞ ያላትን የውኃ ኃይል መጠቀም ይኖርባታል። በውኃው ኃይል ኤሌክትሪክ ስናመርት ግን ተርባይኖቹን የሚያሽከረክረው ውኃ ተለቆ የሚሄድ ሳይሆን ለመስኖ ልማት ላይ መዋል ይኖርበታል።ግድብ ፣ገድበን ኤሌክትሪክ ለማመንጨት ስናስብ፣ የሚለቀቀው ውኃ እታች ወርዶ ማሳውን እንዲያጠጣ ተደርጎ መታቀድ ይኖርበታል።በዚህ አኳኋን ካልታቀደ በከፍተኛ ወጪ ያጠራቀምነውን ውኃ ያለምንም ክፍያ ለሱዳንና ለግብፅ አሳለፈን ሰጠን ማለት ነው። ከዚህ ግንዛቤ በመነሣት በደርግ ጊዜ የመልካ ዋከና የኤሌክትሪክ ማመንጫ ጣቢያ ሲገነባ በተጓዳኝ በኡጋዴን ጎዴ አካባቢ ተርባይኑን ለማሽከርከር የሚለቀቀው ውኃ ተጠልፎ እስከ 50ሺ ሄክታር የመስኖ እርሻ እንዲያጠጣ ታቅዶ ኤሌክትሪክ ማመንጨት ሥራ እንደጀመረ የ20ሺ ሄክታር ማሳ  እንዲያለማ ተደርጎ ነበር።በሌላ በኩል ከልማት ጋር ሣይያያዝ የተገነባው የፊንጫ ኤሌክትሪክ ማመንጫ ጣቢያ የሚለቀቀው ውኃ ያለጥቅም መፍሰሱን በመመልክት ለስኳር ፋብሪካ ጥሬ ዕቃ የሚሆን ሸንኮራ አገዳ በ10ሺ ሄክታር ማሳ  እንዲያለማ ታቅዶ ሥራው ተጀምሮ ነበር።የጣናን ሃይቅ በማሳደግ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማመንጨት ሲወሰን በተመሳሳይ መንገድ የሚለቀቀውን ውኃ በመጠቀም በበለስ ሸለቆ እስከ 100ሺ ሄክተር የመስኖ እርሻ ለማት ለማካሄድ እንቅስቃሴው ተጀምሮ ነበር።በሌሎች አካባቢዎችም የኤሌክትሪክ ኃይል ለማመንጨት በሚታሰብበት ጊዜ የሚለቀቀው ውኃ ጥቅም ላይ ውሎ የአገራችንን ኤኮኖሚ ለማሳደግና በምግብም ራሳችንን እንድንችል እንዲረዳ ጎን ለጎን መታቀድ ነበረበት።

ከመስኖ ልማት ጋር ሳይያያዝ ግድብ መገንባትና ኤሌክትሪክ ማመንጨት የግብፅን ፍላጎት በፍቃደኝነት ማሟላት ማለት ነው።ግብፅ ሙሉ ወጪውን በመሸፈን በኢትዮጵያ ትላልቅ ግድቦችን ለመገንባት የኤሌክትሪክ ኃይል በማመንጨት የሚለቀቀውን ውኃ ሳይቀናነስ እንድትወስድ ማረጋገጫ ቢሰጣት ያለ ማቅማማት እንደምትስማማ በእርግጠኛነት መናገር ይቻላል።ግብፅ ውኃውን ከምንም ነገር አስበልጣ ስለምትፈልገው በኢትዮጵያ ግድቦች ቢገነቡና ኤሌክትሪክ በቻ እንዲመረት ቢደረግ ምንም ዓይነት ተቃውሞ አታሰማም።ለማስረጃ ያህል በጣና ሃይቅ የአባይ ወንዝ መውጪያ ላይ የተወሰነ ግድብ ተገንበቶ የጣና ውኃ መጠን እንዲጨምር ከተደረገ በኋላ በምዕራብ አቅጣጫ ጣና ተሸነቁሮ ውኃውን ቁልቁል በመልቀቅ ተርባይን እንዲያሽከረከር ተደርጎ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት ከተጀመረ ቆየት ብሏል፤ የተከዜ ወንዝ ተገድቦ የተጠራቀመው ውኃ እየተለቀቀ ኤሌክትሪክ ማምረት ከተጀመረ ዓመታት ተቆጥረዋል።ታዲያንስ ግብፅች የተጠራቀመ ውኃ በጣም በሚያስፈልጋቸው በድርቅ ጊዜ ሳይቋረጥ የሚያገኙት መሆናቸውን ሰለሚያውቁ ለምን በጣና ሃይቅ ኤሌክትሪክ ይመረታል፣በተከዜ ወንዝ ላይ ግድብ ተገንብቶ ኤሌክትሪክ ማመንጨት ለምን ተጀመረ ጥቅማችንን ይጎዳል ብለው አልተናተሩም ፤ ተቃውምም አላሰሙም፤ ምክንያቱ ተጠቃሚዎቹ እነሱ ናቸውና።

አባይን አስመልክቶ ይህን ያህል ከተነጋገርን  ስለ’’ ታላቁ የሚሊኒዮም ግድብ’’  አንዳንድ ነገር ብናነሳ መልካም ይመስለኛል።እንደተነገረን ግድቡ የሚገነባው በቤኔኛንጉል ክልል ከሱዳን ድንበር 17 ኪሎሜትር  ርቀት በሚገኝ ቦታ ላይ ነው። ግድቡ 62 ቢሊዮን ሜትር ኩብ ውኃ ይይዛል።የግንባታው ወጪ 80 ቢሊዮን ብር ሲሆን በኢትዮጵያ ሕዝብ መዋጮ ይሸፈናል ተብሏል።በግድቡ ውኃ 5250 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ይመነጫል።እንግዲህ ከግድቡ ኢትዮጵያ የምታገኘው ጥቅም የኤሌክትሪክ ኃይል ብቻ መሆኑ ነው።ግብፅና ሱዳን ግን ተጨማሪ ውኃ ያገኛሉ።ኤሌክትሪክ ኃይል ለማምረት ምን ያህል ተርባይኖች እንደሚተከሉ አይታወቅም። 5250ኪሎ ዋት ኤሌክትሪክ ለማምረት አንዱ ተርባይን 50 ሜጋ ዋት እሚያመነጭ ቢሆን እንኳን ከ 100 ተርባይኖች በላይ መትከል ይኖርባቸዋል።አንዱን ተርባይን ለማሽከርከር 5 ሜትር ኩብ ውኃ በሰኮንድ መልቀቅ ያስፈልጋል ቢባል እንኳን 100 ተርባይኖችን ለማሽከርከር 500 ሜትር ኩብ ውኃ በሰኮንድ መልቀቅ ያስፈልጋል ማለት ነው። አባይ ሲሞላ በክረምት ወራት ከተጠራቀመው ውኃ ተርባይኖችን ለማሽከርከር መልቀቅ አስፈላጊ አይሆንም። ወንዙ በግድቡ ላይ ሰለሚያልፍ እግር መንገዱን ተርባይኖቹን እያሽከረከረ ያልፋል።በግድቡ የተከማቸውን ውኃ መልቀቅ የሚያስፈልገው በበጋ ወራት አባይ ሲደርቅ ነው።ተርባይኖች ከዓመት ዓመት መሽከርከር ሰለአለባቸው ከግድብ እየተለቀቀ  የሚወርደው ውኃ በቋሚነት ያስፈልጋል። በዚህ አሠራር በክረምት ወራት አባይ ሲሞላ ከመገኘው የውኃ መጠን የበለጠ ግብፅና ሱዳን በበጋ ወራት ያገኛሉ ማለት ነው።ይህ መጠን በተፈጥሮ ከሚያገኙት በእጅጉ ይበልጣል።በተፈጥሮ የሚያገኙት ውኃ እየቆጨን እያለ እያንዳንዱ እትዮጵያዊ እየተመጠጠ በተሰበሰበው ገንዘብ ትልቅ ግድብ ገድበን ውኃ አጠራቅመን በተጨማሪ መስጠታችን እንደሆነ የኢትዮጵያ ሕዝብ የተረዳው ወይም የተገነዘበው አይመስልም።ሕዝቡ የሚመስለው ወንዙ ተገድቦ ለልማት ውሎ ከረሃብ እንደሚወጣ ነው። በጥቅሉ አባይ ሊገደብ ነው እየተባለ ይነገረዋል።በሚገደበው ግድብ ከሚከማቸው ውኃ አንድ ሄክታር መሬት እንኳን በመስኖ እንደማይለማ አይነገረውም። ከታላቁ ግድብ ጋር ምንም የመስኖ ልማት ፕሮግራም አልተያዘም። ወደፊት ውኃውን ለልማት እናውለዋለን እንዳይባል ከግድቡ በታች ለእርሻ የሚሆን መሬት የለም። በርባራ አካባቢ ነው፤ ከዚያም ቢሆን ውኃው ተለቆ ተርባይን ከአሽከረከረ በኋላ በቀጥታ ሱዳን ውስጥ ይገባል።ምክንያቱም በሱዳን ጠረፍና በግድቡ መሐል 17 ኪሎ ሜትር ብቻ እርቀት ነው ያለው።የውኃ ጉዳይ ለግብፅ የመኖር ወይም ያለመኖር ጥያቄ ነው። ከኢትዮጵያ የምትወጣዋን ውኃ ትቆጣጠራለች። ይህ አዲሱ ግድብ ሥራው ተጠናቆ ኤሌክትሪክ ለማመንጨት ውኃ መልቀቅ ከጀመረ በኋላ ውኃውን ማቆም አይቻልም።ምክንያቱም ከዓመት ዓመት የሚፈሰው ውኃ እየተለካ ይመዘገባል።ኤልክትሪክ ማምረት አቁማአለሁ ብላ ኢትዮጵያ ብታቆም ጦርነት እንደማወጅ ተቆጥሮ በግብፅና ከሱዳን ጋር ውጊያ መግጠምን ያስከትላል።በመሆኑም ዛሬ የሐገር ፍቅር ስሜታችንን ቀስቅሰው በሚገባ ገልፅ ሳይሆንልን የግድቡን ሥራ መደገፋችን ገንዘብ ማውጣታችን ወደፊት መዘዝ ያስከትልብናል። ‘አባይ ሊያለማን ወይስ ሊያጠፋን’ ብን መጠየቅም ይኖርብናል። ግድቡ የመስኖ ልማት ጋር ቢያያዝ ከረሃብ ከድህነት ልንወጣ ስለምንችል ማንኛውንም ዓይነት መስዋዕትነት ሕዝብ ቢከፍል ተገቢ በመሀነ ነበር፤ ከሕዝብ ጎን ጋር ያልተዛመደ ግዙፍ ሥራ መወጠኑ በኋላ አሁን ለሚደረገው የሚያስጠይቅ ሊሆን ይችላል። የኢትዮጵያ ሕዝብ ባልተካፈለበትና በድበቅ በተያዘ የዚህን ግዙፍ ሥራ በሕዝብ ሰም ማንነታቸው ባልታወቁ ነገ በሃላፊነት በማይጠየቁ ግለሰቦች መንግሥት  ነን ባሉ  መመራቱ ለወደፊቱ የትወልድ ጦሰ መሆኑን ቆም ብለን፤ የሚመጣው መዘዝ በጥልቅት አስተውለን፤ የዜግነትን ኃላፊነታችንን መወጣት  ግድ ይለናል።የሚገርመው ደግሞ ከዚህ ድንቅ ከተባለው ግድብ የሚገኘው የኤሌክትሪክ ኃይል ለሱዳንና ለግብፅ ይሸጣል መባሉ ነው።የሚሸጠውም በጣም በአነስተኛ ዋጋ ነው።በአሁኑ ጊዜ ለሱዳን አንድ ኪሎዋት የሚሸጠው በስድስት ሳንቲም የአሜሪካን ሲሆን፣ሱዳን በሃገሯ እስከአሁን የምትሸጠው ሃያ ስድስት ሳንቲም የአሜሪካ ነው።በዚህ ዓይነት የ ሃያ ሳንቲም ትርፍ ታገኛለች ማለት ነው።ሱዳንና ግብፅ በውኃችን የተነሣ ጠላት አድርገውን በዙ ጎድተውናል።ወደፊትም ይጎዱናል። ሃገራችንን ለመከፋፈልና ለመገነጠል ለተሰለፉት ዛሬ ኤርትራ ገንጥለው ለሚያስዳድሩትና የኢትዮጵያን ሕዝብ በዘር በጎሣ ከፋፍለው የሚመሩትን ቡዱኖች አጋር ሆነው ቆይተዋል።’አንዳንዴ የአባይ ግድባ ለነዚህ ሃገሮች ዎሮታ ይሆን’ ብለው የሚጠይቁ ሃገር ወዳዶች አሉ። ታዲያ በዚህ የጠላትነት መንፈስ እየተመለከቱን እያሉ ኤሌክትሪክን ያህል የልማት ኃይል አቅራቢ ሆነን እንዲያድጉና እንዲበለጽጉ በወታደራዊ ቴክኔክና ቴክኖሎጂ እንዲዳብሩ መርዳቻችን እንደሆነ መገንዘብ አልቻልንም።ኤሌክትሪክ ለጎሮቤት አገሮች የመሸጥ ሐሣብ በደርገ ዘመን ተነስቶ ነበር።የጦር መሣሪያ ከማስታጠቅ አይተናነስም ተብሎ ሐሣቡ ውድቅ ተደርጎ ነበር።ኢትዮጵያ የሚያስፈልጋትን የኤሌክትሪክ ኃይል  ከሌሎች ወንዞች ማመንጨት ይቻላል ተብሎ፤በግልገል ግቤ በርካታ ግድቦች ተገድበው በቂ የኤሌክትሪክ ኃይል የሚመረትበት ቦታ የሌለ ይመስል ታላቁ ግድብ ኤሌክትሪክ በኤሌክትሪክ ያደርገናል ችግራችን በሙሉ ይወገዳል፤እየተባለ የሚካሄደው አዳናጋሪ ፕሮፓጋንዳ ወደፊት ሃቁ መታወቁ አይቀርም።እኔ እንደምገምተው ከግብፅ ጋር ስምምነት አድረገው በጋራ የነደፉት ፕሮጀክት ይመስለኛል።በጥናቱም ላይ የግብፅ እጅ ይኖርበታል የሚል ግምት አለኝ።የዚህ ግድብ ሥራ ግብፅን የሚጎዳ ቢሆን ኖሮ በዓለም ከፍተኛ ጩህትና የፖለቲካ ትረምስ ይሰማ ነበር። ግብፅ ያለችው ነገር ቢኖር ቴክኒካል ወረቀቶቹን ስጡኝ ነው፤ይህም ለማለት ያህል እንጂ ቴክኒካል ጥናቱ ቀድሞ በእጇ ይገኛል። አሁን ለግብፅና ለሱዳን የሚጠቅም ሥራ ኢትዮጵያ በማቀሳቀሷ ከዚህ በፊት በአባይ ጉዳይ ላይ አልነጋገርም፤ ስምምነትም በአዲስ መልክ አላደርግም ሲሉ የነበሩ ሁለቱ አገሮች በጉዳዩ ላይ እንደራደራለን የሚል አቋም ይዘዋል።የኢትዮጵያ ሕዝብ ገንዘብ ማውጣቱን እንዲቀጥል ብቻ አልፍ አለፍ እያሉ በለሆሳስ የግድቡ ሥራ አሳስቦናል ይላሉ።

ዘለዓለማዊ የሃገር መታደግና ዕድገት ሳይሆን ሰለዓለማዊ ጠንቅ እንዳይተከልባት ለምን? ለማን? እንዴት? የሚለው የሃገር ጥቅም መለኪያ፣ሊተኮርበት ይገባል።ከራስ እያወለቁ ጠላትን እያስታጠቁ ግንባታ ስንኩል ስለሆነ አባይ መዘዝ ሳይሆን ሕዝብ አገዝ እንዲሆን ሁሉም ዕድሉ አሁን መሆኑን መገንዘብ ይገባዋል።

የኢትዮጵያ ፍቅር ከቃሊቲ


ሪያድ የኢትዮጵያ ኤንባሲ ሜይ 23 2013 ቀነ ቀጠሮ ስቷቸው የነበሩ ኢትዮጵያውያንን በአግባቡ መስተናገድ ተስኖት ዲፕበሎማቱ ሲዋከብ ዋሉ

$
0
0

በሪያድ የኢትዮጵያ ኤንባሲ ሰሞኑንን የሳውዲ መንግስት ያወጣውን የምህረት አዋጅ ተከትሎ ከጅዳ ቀጥሎ ብዛት ያላቸውን እድለኛ ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችንን እያስተናገደ የሚገኝ መሆኑ ይታወቃል …. ይህ በዚህ እንዳለ ሰሞኑንን ኤንባሲ ውስጥ የሚገኙ ዲፕሎማቶች ወደ ኤንባሲ ቅጥር ግቢ የሚመጣውን ባለጉዳይ ወገኖቻችንን በአግባቡ በማስተናገድ ላይ መሆናቸውን አንድ ዲፕሎማት የሰጡኝን አስተያየት አብነት አድርጌ የዲፕሎማቶቹን መስተንግዶ በማድነቅ መግለጼ ከሪያድ የኢትዮጵያ ኤንባሲ ዲፕሎማቶቻችን ጀርባ ያለው የተዝረከረከ አሰራር .ይታወሳል።

በዚህም መሰረት የተጠቀሱት ዲፕሎማት አቶ መስፍን ነገሮች ሁሉ አለጋ በአልጋ የሆነ ያህል በኩራት እና በሙሉ ልብ ያወጉኝን ሁሉ ተቀብዬ ለኛዎቹ በጅዳ የኢትዮጵያ ቆንስላ ጽ/ቤት ተወካዮቻችን ጥሩ ተሞክሮ ይሆናል በሚል ወደ ጅዳ ሰንቄ የመመለሰውን ልምድ ልመቅሰም በማሰብ የመመለሻዬን ግዜ ለአንድቀን በማራዘም ሃሙስ ፓስፖርት ለመውሰድ ቀነ ቀጠሮ ተይዞላቸው የነበሩትን ከ1700 በላይ የሚሆኑ ባለጉዳዮች በምን ተአምር ሊስተናገዱ እንደሚችሉ ለመታዘብ ረፈድፈድ አድርጌ በሪያድ የኢትዮጵያ ኤንባሲ ወደ ሚገኝበት ዲፕሎማቲክ ኮርተር አቀናሁ።

አካባቢው ከወትሮው ለየት ባለ ሁኔታ በሴት እህቶቻችን እና ወንድሞቻችን ተጨናንቆን የሳውዲ ልዩ የፀጥታ ሃይሎች ህዝብ ደንብ እና ስረአት ለማስያዝ ደፋቀና ይላሉ። ተራ የያዙ ሴት እህቶቻችን ሰልፍ በጣም ረዠም የመሆኑ ያህል መጨረሻውን ለማየት ለአይን ይታክታል ! የወንዶቹም እንደዛው ።ሁሉም ነገር ድብልቅልቅ ብሎል ! በተለይ በኢትዮጵያ ሰዓት አቕጣጠር ከሌሊቱ 10 30 አካባቢ መተው ወርፋ የያዙ ሴቶች እና ወንዶች እንዳሉ የኤንባሲው የጥበቃ ሰራተኛ ለአንድ ባልጀራው ሹክ ሲለው ሰማሁ። ሰለሁኔታው የበለጠ ለመረዳት ወደ ኤንባስው ቅጥር ግቢ መዝለቅ የግድ ስለነበር ውስጥ ለመዝለቅ ወደ መቢያው በር ተጠጋሁ ። እነዛ በዲስፒሊን የታነጹ የሳውድ ፖሊሶች ወዴት ነው የሚል ጥያቄ ቢጤ ጠየቁኝ። ምን ማለት እንደሚገባኝ፡ቀድም ብዬ ተዘጋጅቼበት ስለነበር ያልኩትን ብዬ ወደ ውስጥ እንድዘልቅ ጠይኳቸው ። ምላሹም አወንታዊ ስለነበር ፀሃይ ለጭንቅላት የቀረበች ያህል የሚንቀለቀለውን ሃይለኛ ሙቀትን መቋቋም ተስኗቸው የመግቢያውን የብረት በር ተደግፈው ተራቸውን ይጠብቁ የነብሩ ወገኖች ገለል ገለል አድርገው እንድገባ ጋበዙኝ። እኔም አመስግኜ በሩ ላይ ያለውን ኢትዮጵያዊ የጥበቃ ሰራተኛ ሰላም ብዬ ወደ ውስጥ ዘለኩ ።

ቀደም ብለው ወደ ኤንባሲው ቅጥር ግቢ ለመግባት እድል ያገኙ ብዛት ያላቸው ሴቶች ( በስማቸው የመጀመሪያ ፊደል )የስማቸውን መጠራት ይጠባበቃሉ። በሩ ላይ የዲያስፖራው ሀላፊ አቶ ተመስገን ስልችት ባለ የፊት ገጽታ ታጅበው እነዚህን ሴት እህቶቻችንን አንድ ረዘም ካለ ጎልማስ ጋር ስም እየጠሩ ፓስፖርት ለመስጠት የአቅማቸውን ያህል ይጥራሉ ። ከዚህ ባሻገር እኚሑ የዲያስፖራ ሃላፊ አልፎ አልፎ ከሴት እህቶቻችን ለሚቀርብላቸው ጥያቄ ለሰስ ባለው ድምጻቸው ማብራሪያ ይሰጣሉ ። እንደገባኝ ከሆነ ፓስፖርት የተዘጋጀው በመጀመሪያ የስም ፊደል ( በአልፋ ቤት ) በመሆኑ ወጣቱ ድምጹን ከፍ አድርጓ ስም ይጠራል ጀሚላ ጀማነሽ ጀማል ጂሃድ….. ወዘተ ። ክፋቱ ! አቤት ብሎ የሚቀርብ ግን አንድም ሰው የለም ! «ከብት ባልዋለበት ኩበት ለቀማ ይሉሃል እንዲህ ነው»። ! ነገሩ ግራ ገብቶኝ ለ 10 ደቂቃ ያህል ቆም ብዬ ሂደቱን ማስተዋል ጀመርኩ ። ከሚጠራው 50 እና 60 የስም ዝርዝር ውስጥ አንድ ሰው ብቻ የሚስተናገድበት ሁኔታ ከግዜ እና ውጭ በፀሃይ ከሚንቃቃው ወገናችን አንጻር የአሰራር ስህተት እንዳለ ተርዳሁ ። ያለወንጀላቸው በፀሃይ ግለት አናታቸው የሚበሳው ወገኖች ስቃይ ተሰማኝ ! ለሊት መጥተው ወረፋ በመያዛቸው ብቻ ወደ ግቢው የመግባት እድል ያገኙቱ ባለጉዳዮችን ስመለከት ከሚያቀርቡት ጥያቄ በመስተንግዶው የረኩ አይመስልም ። ገሚሱ እረ የፓስፖርት ያለህ እያሉ እሮሮ ያሰማል! ገሚሱ ምንም መረጃ የሌለን ሰዎች ምንድነው ማድረግ የሚገባ ይላሉ ! የኤንባሲው አመዘጋገብ እና ቀጠሮ አሰጣጥ ላይ ትልቅ ስህተት እንደነበር ሌላኛው ድክመት መሆኑንን ተርዳሁ ። ተመዝግቦ ቀጠሮ የተሰጠው ባለጉዳይ የምህረት አዋጁ የሚመመለከትውም የማይመለከተውም ኢትዮጵያዊ የመሆኑ የአሰራር ግድፈት የኤንባሲው ሰራተኞች በራሳቸው ግዜ የፈጠሩት የተዘበራረቀ መስተንግዶ አንዱ አካል መሆኑንን በተጨባጭ አረጋጋጥኩ።

በሪያድ የኢትዮጵያ ኤንባሲ ዲፕሎማቶች አቶ መስፍን ቀደም ብለው በኩራት ሲያስረዱኝ የነበረው የትኛውን ህብረትሰብ መስተንግዶ እንደሆነ ግራ ገባኝ። የመስተንግዶውን ድራማ ለመታዘብ በቆምኩበት ፡ የኤንባሲ ሰራተኛ መስያቸው ! አንዳንድ እንደኔ ግራ የገባቸው ሴት እህቶች እንደ ማክበር እያሉ ኢትዮጵያዊ ጨዋነት በተላበሰ አጠራር አባባ አባባ እባኳዎን ! እባኳዎን ! በሚል አሳዛኝ፡ድምጽ እንድረዳቸው ተማጽኖአቸውን ያሰሙኛል ። ውስጤን ቢከነክነኝም እኔ እራሴ እንግዳ ስለሆንኩ የማውቀው መረጃ ስለሌለኝ ከነግሩ ጦም እደሩ ብዬ ወደ አቶ መስፍን ቤሮ ወደሚያስገባው የህንጻ በር አቀናሁ። የምህረት አዋጁ ከተጀመረበት ግዜ ጀምሮ የሚመጡትን እህት ወንዶሞቻችንን ለማስተናገድ ቀጠሮ ይሰጥ የነበር አንድ ደልደል ያለ ወጣት ቀጠሮ ሲሰጣቸው የከረሙትን ባለጉዳዩች ወደ ህንጻው ዘልቀው እንዳይገቡ በጉልበት ይከላከላል ። ወደ አቶ ተመስገን ቢሮ መግባት እንደምፈልግ ነግሬው በትህትና ወደ ህንጻው እንድገባ ፈቀደልኝ ። በአጋጣሚ አባሳደር መሃመድ ሃሰን በረዳ ላይ ቆመው አንድ ለእግርኳስ ግጥሚያ ወደ ሜዳ ገብቶ በተቃራኒው እየተመራ ያለ ደካማ ቡድን የሚያስተባብር አሰልጣኝ ይመስል ፡ በደከመ አንደበት « አንተ በዚህ ሂድ አንተ በዛ ግባ እያሉ » ያለምንም ውጤት እጃቸውን ወደ ሃላ አጣምረው ይንጎራደዳሉ። እያድረጉ ያለው ጥረት ከአንባሳደርነት ድረጃ አንጻር ማለፊያ ቢሆንም ህዝቡ እየተስተናገደ ያለበትን የተዝረከረከ አሰራር አለማየታቸው ነው ክፋቱ። የአሳ ግማቱ እንዲሉ የሪያድ ኤንባሲ ዲፕሎማቶች የተዝረከረክ አሰራር የቱ ጋር እንዳለ ለማወቅ የግድ ነብይ መሆን አይጠይቅም። እኚህ ክቡር አባሳደር ከቢሮቸው ወተው እያስተናገዱ ያሉት ለተሳትፎ ወይስ ለዜጎቻችን ጊዜያዊ ችግር መፍትሄ ለመሻት ? ክቡር አባሳደር ውጭ፡በጸሃይ ሃሩር እየነፈረ ያለውን ኢትዮጵያዊ ማየት ተስኖቸው ወይስ ግራ ገብቷቸው ? ለግዜው በሳቸው ሁኔታ ውስጤ በጣም በገነ ! አሁንም ወደ አቶ መስፍን ቢሮ ወደ ሚያዘልቀው ኮሪነር ላይ ሌላ ተይንት ገጠመኝ ። አንድ መልከመልካም ወጣት ከ30 በማይበልጡ ሴቶች ታጅቦ የ400 ሰዎችን ስም ዝርዝር የያዘ ሊስት እያገላበጠ ሰም ይጠራል ። እዚህም ማንም አቤት የሚል የለም ! አብዛኛው ተስተናጋጅ ከግቢ ውጭ ነው። ለማነው ጥሪው የሚተላለፈው ? ! ወጣቱ ከሰው ተግባቢ ቀልደኛ ብጤ ስለነበር ቀረብ ብዬ እንዴት ነው አሰራራችሁ የሚል ጥያቄ በፈገግታ ወርወር አደርኩለት ። ወጣቱም ሸሪፍ የሚባል እና የኤንባሲ ሰራተኛ መሆኑንን ገልጾልኝ በመጀመሪያ የስም ፊደል ቅደም ተከተል (በአልፋ ቤት ) ህዝቡን እያስተናገደ መሆኑንን አወጋኝ። ጥያቄን ጠንከር አድርጌ ውጭ በጸሃይ የሚንገላቱት እህቶቻችን እንዴት ሊሰሙህ ይችላሉ ? ደግሜ ጠየኩት ። በአልፋ ቤት ስለሆነ መስተንግዶው ውጭ ያሉት በቅደም ተከተላቸው ወደዚህ እንዲገቡ ይድረግ እና አሁን እየሰራን ባለው መልኩ እንስተናግዳለን አለኝ። አባባሉ ተገቢ ቢሆንም በወቅቱ እሱ ሲጠራቸው የነበሩ ተስተናጋጆች ስማቸው በዜድ የሚጀምር ከመሆኑ ጋር ወደ ጊቢው ያልገቡ አያሌ ኢትዮጵያውያኖች እንዳሉ ጥሪውን አቁሞ ስህተቱን ለአለቅቹ በማስረዳት አዲስ የአሰራር ስልት መቀየስ እንዳለባቸው ምክር ቢጤዬን ሹክ አልኩት « የበሰበሰ ዝናብ አይፈራም እንዲሉ» ወጣቱ ዝም ብሎ ጥሪውን ተያያዘው ። በሪያድ የኢትዮጵያ ኤንባሲ ዲፕሎማቶች « አራባ እና ቆቦ የአሰራር ስልት » በተሰጠው መመሪያ መሰረት እይተሰራ ያለው ስራ ምን ያህል ውጤታም እንደሚያደርግ ባላውቅም። የወጣት ሸሪፍን ተዕይንት የሚከታተሉ ባለጉዳይ እህቶቻችን ነገሩ ስህተት እንደ ሆነ ቢያውቁም ከመሞት መሰንበት እንዲሉ ከሚቀዘቅዘው ክፍል ላለመውጣት መጨረሻውን እሱ ያብጀው በሚል እንደ አዝማሪ ስም የሚጠራውን ወጣት ከበው ( አጅበው )የግል ወሬያቸውን ይቆዝማሉ ። ወጣቱ ላንቃው እስኪ ሰነጠቅ ይጮሃል እዚህም አቤት ባይ የለም ! አልመጡም እየተባለ ፓስፖርት እና የስም ዝርዝዝር ሊስት ወደ መጣበት መሳቢያ እየገባ ይቆለፍበታል ።

ሰሞነኛው የሪያዶች ተሞክሮ ለጅዳ ተወካዩቻችን አብነት ይሆናል ያልኩት ሁሉ ገና ከመነሻው ትዝብት ደበዘዘ ። በሪያድ የኢትዮጵያ ኤንባሲ ዲፕሎማቶች የመስተንግዶ ብቃት ዛሬ በተግባር መፈተኑ ተሰማኝ፡፡ የምሳ ሰዓት ግዜ ያቸውን መስወአት በማድረግ ቢሮ አቸው ባለጉዳይ የሚያስተናግዱት ታታሪ ሰው አቶ መስፍን ያጫወቱኝ፡ ሁሉ የእንቦይ ካብ ሆነብኝ ። ጎበዝ ከጊዚያዊ ጭንቀት ለማምለጥ፡ባለ ጉዳይን በብጣሽ ወረቀት ቀጠሮ ሰጥቶ ማሰናበት እና በወቅቱ ኤንባሲዬ ነው ብሎ የመጣውን ወገን ፍላጎት አሞልቶ እንደ አመጣጡ መሸኘት ልዩነት እንዳላቸው አቶ መስፍን ሳያውቁት ቀረትው ይሆን ? አሁንም ጎዞዬን ወደ አቶ መስፍን ቤሮ ሳቀና ጅዳ ውስጥ በአይን ከምንተዋወቅ ሰው ጋር በአጋጣሚ ተገናኘን ሰላምታ ተለዋውጠን በቀጥታ ለተወሰኑ ደቂቃዎች በመስተንግዶ ዙሪያ አንድ ሁለት እያልን ወሬያችንን በስፋት መቆዘማችንን ተያያዝ ነው ። ከወዳጄ ጋር ጅዳ ከተማ በአይን ብንተዋወቅም ነዋሪነቱ ግን ሪያድ ነው ።ስለ ጅዳው ቆንስላ ጽ/ቤት መስተንግዶ ወጣት ነብዩ ሲራክ ከጅዳ በድህረ ገጹ ላይ የለጠፈውን ልክ በአካል ሄዶ እንዳየ ያወጋኝ ጀመር ። እኔም ስለሪያድ ኤንባሲ አንዳንድ መረጃዎችን ማወቅ ጉጉቴ ስለጨመረ የማውቀንም የማላውቀውንም እየተቀበልኩ የወዳጄን እንዳይከፋው የሚለውን ሁሉ ሰማሁ። በጣም ተግባባን ! የሪያድን ኤንባሲ ጓዳ ጓድ ጓዳ ላስጎብኝህ ብሎ የአሰራር ስህተት ወደ የሚፈበረክበት ክፍልን ለማሳየት እጄን ይዞ ወድ ፎቅ አመራን ። ልክ እንደ መኖሪያ ቤቱ ያስጎበኝ ገባ ። በቀኝ በኩል ያለው የአቶ ተመገን ቢሮ መሆኑንን ጠቅሷልኝ በሩ ለማንኛውም ኢትዮጵያዊ ክፍት እንደሆነ ገለጸልኝ። የኔ ጉጉት ቀደም ብሎ ወዳጄ የጠቀስልኝን የሪያድ ዲፕሎማቶች የአሰራር ድክመት ጓዳ ለማየት ብቻ ስለሆነ ጎደኛዬ የሚለውን ጆሮዬን ሰጥቼ ከማዳመጥ ውጭ ምንም አይነት አስተያየት ለመሰንዘር አልወደድኩም። አሁንም ወደ ተጠቀሰው ቦታ ለመድረስ ከሪያድ ጅዳ የትጓዝኩ ያህል ተሰማኝ ። የተባለውን ጉድ ለማየት የተጠቀሰው ቢሮ በር ላይ ደረስን በሩን አንኳኳን ማነው ! የሚል የጓልማስ ድምጽ ተሰማን””’ ይቀጥላል



መኢአድና ሰማያዊ ፓርቲ መንግስትን ለመክሰስ መረጃ እያሰባሰቡ ነው

$
0
0

እዚህ ፍትህ ካጣን ወደ ዓለምአቀፉ ፍ/ቤት እንሄዳለን 20ሺ ሰው ሲፈናቀል አላውቅም ማለት ተቀባይነት የለውም በቅርቡ የመላ ኢትዮጵያውያን አንድነት ድርጅት (መኢአድ) እና ሠማያዊ ፓርቲ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክል….ል በአማራ ተወላጆች ላይ የደረሠውን መፈናቀል አስመልክቶ ድርጊቱን በፈፀሙት የመንግስት ባለስልጣናት እና ተቋማት ላይ ክስ ለመመስረት መዘጋጀታቸውን ገልፀዋል፡፡ በዋናነት የክሡ መነሻ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ የደረሠው መፈናቀል ይሁን እንጂ ከአመት በፊት በደቡብ ክልል ጉራፈርዳ ወረዳ የደረሠው መፈናቀልና ያስከተለው ጉዳትም በክሡ እንደሚካተት ፓርቲዎቹ ተናግረዋል፡፡

 ማስረጃዎችን አሠባስቦ በማቀናጀት ሃገር ውስጥ ለሚገኙ ፍርድ ቤቶች ክስ በመመስረት በኩል ደግሞ የቀድሞው የቅንጅት አመራር አባልና በአሁን ሠአት ከማንኛውም የፖለቲካ ድርጅት አባልነት ተገልለው በአለማቀፍ የህግ ባለሙያነት በመስራት ላይ የሚገኙት ዶ/ር ያዕቆብ ኃይለማርያም እንደሚሳተፉ ታውቋል፡፡ በክሱ አቀራረብና ባህሪ እንዲሁም ተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ የአዲስ አድማስ ጋዜጠኛ አለማየሁ አንበሴ ዶ/ር ያዕቆብ ኃ/ማርያምን በቢሮአቸው አነጋግሯቸዋል፡፡ የክሡ ሂደት ምን ላይ ደረሠ? በሠማያዊ ፓርቲና በመኢአድ አነሣሽነት ነው ክሡ ሊመሠረት የታሠበው፡፡ ነገር ግን እስካሁን ክሡ አልተጀመረም፡፡ ማስረጃ ሠብስበን ከተጐዱት ሠዎች የውክልና ስልጣን ወስደን ወደ ስራው እንገባለን፡፡

አሁን ግን ገና ነው፤ የውክልና ስልጣኑም አልተዘጋጀም፡፡ በአካባቢው ያሉ ሠዎችን ማግኘት ያስፈልጋል፡፡ ስራው አሁን በውል ተጀመረ ማለት ባይቻልም በቅርቡ ሠዎች ወደዚያው ሄደው የተጐዱና የተፈናቀሉ ሠዎችን በመጠየቅና የደረሠባቸውን ጉዳት በማየት መረጃ እያሠባሠቡ ነው፡፡ ክሡን የምንመሠርተው ከዚያ በኋላ ይሆናል ማለት ነው፡፡ መጀመሪያ እንደሚታወቀው መረጃውን ማሠባሠብ ያስፈልጋል፡፡ በግልፅ ህግ መጣሡን በደንብ ማረጋገጥ ያስፈልጋል፡፡ እነዚህ ከተሟሉ በኋላ በቀጥታ ወደ ክሡ እንሄዳለን፡፡ መጀመሪያ የሠዎቹን ውክልና ሣታገኙ እንዴት ለመክሠስ እየተዘጋጃችሁ መሆኑን ገለፃችሁ?

መጀመሪያ ውክልናውን ማግኘታችሁን ማረጋገጥ አልነበረባችሁም? እንግዲህ ጉዳዩን ወደ ፍርድ ቤት ይዘን የምንቀርበው በሁለት አይነት ነው፡፡ የወንጀልም የፍትሃ ብሄር ጉዳይም አለው፡፡ የወንጀል ጉዳይን በተመለከተ ማንኛውም ሠው እንደተጐጂው ሆኖ ለፍትህ አካል አቤት ብሎ፣ ፖሊሶች ጉዳዩን ከመረመሩና ማስረጃውን ካጠናቀሩ በኋላ ወደ አቃቤ ህግ ይመሩታል፡፡ አቃቤ ህግ ክስ ይመሠርታል ወይንም በቂ ማስረጃ የለኝም፤ ክስ አልመሠርትም ብሎ ሊተወው ይችላል፡፡ በቂ ማስረጃ ካለ ደግሞ ክስ መስርቶ ፍርድ ቤት ይቀርባል፡፡ በሁለተኛ ደረጃ በቀጥታ እኛ የምንሣተፍበት ደግሞ አለ። እነዚህ ሠዎች ከቤታቸው ተፈናቅለዋል፤ የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል፣ የንብረት መውደም ደርሶባቸዋል፣ ጤናቸው ታውኳል፣ ብዙ አይነት ጉዳት ነው የገጠማቸው፡፡ ያ ሁሉ በገንዘብ ተሠልቶ የሚገባቸውን ካሣ፣ ተጠያቂ የመንግስት አካላት እንዲከፍሉ ነው የሚደረገው፡፡ መኢአድና ሠማያዊ ፓርቲ ከተጐጂዎች መካከል በርካቶቹን ጠይቀው ፈቃደኝነታቸውን አረጋግጠዋል፡፡ የውክልና ስልጣን ከዚያ በኋላ ይመጣል ማለት ነው፡፡

ክሱ በዚህ አገር ያልተለመደ ዓይነት ይሆናል ብለው ነበር፡፡ ሊያብራሩት ይችላሉ? ብዙ ሠው የያዘ ቡድን አንድ አይነት ጉዳት ከደረሠበት አንዱ ብቻ ከሶ ፍርድ ካገኘ ሌሎቹም ክስ ሣይመሠርቱ ከውጤቱ ተጠቃሚ ሊሆኑ ይችላሉ። ይሄ በፈረንጆች “ክላስ አክሽን ሱት” ይባላል። ለምሣሌ የተፈናቀለው የአማራው ህብረተሠብ ተመሣሣይ በደል ነው የደረሠጁ እና ከእነሡ ውስጥ አንድ ሠው ብቻ ከሶ ፍርድ ካገኘ (ከረታ) ሌሎቹ የተጐዱ ሠዎች ክስ ሣይመሠርቱ፣ ለፍርድ ቤቱ ተመሣሣይ በደል እንደደረሠባቸው በማመልከት ብቻ ከፍርዱ እኩል ተጠቃሚ ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ እንግዲህ ይህ በሃገራችን ብዙም አልተለመደም ግን እኛ ይህ አካሄድ በሃገራችን ይሠራል የሚለውን ልንፈትሸው ነው፡፡ ጉዳዩን በምሣሌ ማየት ይቻላል። አንድ መለያ ያለው የጥርስ ሣሙና ከገበያ ገዝተህ ሣሙናው የተመረዘ ቢሆንና ብዙ ሠዎች ተጠቅመውት ከተጐዱና አንድ ሠው ብቻ ክስ አቅርቦ ከኩባንያው ካሣ ካገኘ፣ ያንን የጥርስ ሣሙና ተጠቅመው ተጐጂ የሆኑ ሠዎች ከዚያ ፍርድ ውጤት ተጠቃሚ ይሆናሉ፡፡

እኛም በዚህ መልኩ ነው ክሣችንን የምንመሠርተው፡፡ በእያንዳንዱ ተጐጂ ስም ክስ የማቅረብ ሃሣቡ የለንም፡፡ ውክልናውን ከአንድ ሠው ብቻ ብታገኙም መክሠስ ትችላላችሁ ማለት ነው? አዎ በሚገባ ይቻላል፡፡ ውክልና የሠጠን ሠው ከፍርድ ሂደቱ በሚያገኘው ውጤት ተመሣሣይ ጉዳት ያጋጠማቸው ሁሉ ተጠቃሚ ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ በዚህ መሠረት የአንድ ሠውም ውክልና የመንግስትን ተጠያቂ አካላት ለመክሠስ ያስችለናል፡፡ በአገራችን ይህን ለማድረግ የሚያስችል የህግ ማዕቀፍ አለ?

በህገ መንግሥቱም አለ፣ በወንጀለኛ መቅጫውም በፍትሃ ብሄር ህጉም አለ፡፡ ለምሣሌ በህገ መንግስቱ ላይ “ክላስ አክሽን ሡት” የሚባለውን በተመለከተ የተጠቀሠ አለ፡፡ በህገ መንግስቱ አንቀፅ 37 ላይ “ማንኛውም ቡድን ወይም ተመሣሣይ ጥቅም ያላቸውን ሠዎች የሚወክል ግለሠብ ወይም የቡድን አባል የመጠየቅና የማግኘት መብት አለው” ይላል፡፡ እንግዲህ ማንኛውም ግለሠብ፣ ተመሣሣይ ጥቅም ያላቸው የቡድን አባላትን ወክሎ የመጠየቅና የማግኘት መብት አለው፡፡ እንግዲህ ያ የሚወክለው ግለሠብ ጠበቃ ሊሆን ይችላል፡፡

የቡድኑ አባል ደግሞ ከተበዳዮች አንዱ ሊሆን ይችላል፡፡ በተለያዩ ምክንያቶች ከተጐጂዎች ውክልና የሚሠጣችሁ ሠው ብታጡስ…ምን ታደርጋላችሁ? የተሠሩ ወንጀሎችን ከአንዳንድ ሠዎች ጠይቀን፣ ያንን ሪፖርት ለፖሊስ እናቀርባለን። ፖሊሶች ለአቃቤ ህግ ያቀርባሉ፡፡ አቃቤ ህግ መረጃና ማስረጃዎችን መዝኖ ክስ ይመሠርታል፡፡ በፍትሃብሄር ካሣ ለማግኘት ግን እነሡ የውክልና ስልጣን ካልሠጡን አይሆንም፡፡ የወንጀሉ ክስ ግን እነሡ ውክልናውን ቢሠጡም ባይሠጡም ይቻላል፡፡ እኛ ሣንሆን በወንጀሉ አቃቤ ህግ ነው የሚከሠው፡፡ እኛ ግን እስካሁን የተረዳነው፣ ሠዎች የዚህ የፍትሃብሄር ክስን በተመለከተ በመኢአድና በሠማያዊ ፓርቲ አማካኝነት ክሡን ለማቅረብ ፍላጐት እንዳላቸው ነው፡፡ ዋነኛ ማስረጃችሁ ሊሆን የሚችለው ምንድን ነው? ዋነኛ ማስረጃ የሚሆኑት ተጐጂዎቹ ራሣቸው ናቸው፡፡ ለምስክርነት ይቀርባሉ፡፡ የመንግስት ባለስልጣናትም ለምስክርነት ይቀርባሉ፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሣለኝ ይሄ ነገር ከባድ ወንጀል እንደሆነና መፈፀም እንደሌለበት፤ በአጥፊዎች ላይም መንግስት እርምጃ እንደሚወስድ አረጋግጠዋል፡፡ እሣቸውም በአካልም ሆነ ንግግራቸው በቪዲዮ ማስረጃነት ያለ ጥርጥር ይቀርባሉ፡፡ እርግጥ ማስረጃ በተለይ በተጐጂዎች ሲቀርብ የፍርሃቱ ነገር ሊኖር ይችላል፡፡ የክልሎቹ ባለስልጣናትም ሆኑ የፌደራሎቹ ሊያስፈራሯቸው ይችላሉ፡፡ ጥቃት የደረሠበት ሠው ደግሞ ይፈራል። አሁንም ጥቃት ውስጥ ያሉ ሠዎች ናቸውና ሊፈሩ ይችላሉ፡፡ ግን መኢአድና ሠማያዊ ፓርቲ እንዳረጋገጡልን በዚህ ጉዳይ ላይ ለመግፋት የሚፈልጉ ሠዎች አሉ፡፡ አንዱ የክሱ ጭብጥ “ዘር ማጥፋት” የሚል መሆኑን በሠጣችሁት መግለጫ ላይ ጠቅሳችኋል። ዘር ማጥፋት ሲባል ምንድን ነው? ዘር ማጥፋት በሚለው ክስ ለማቅረብ የሚያስችላችሁ የህግ ማዕቀፍ ይኖራል? ሁለት አይነት ወንጀሎች ናቸው፡፡ የዘር ማጥፋት የሚለው አንዱን ብሄረሠብ ወይም ዘር በከፊልም ሆነ ሙሉ ለሙሉ ለማጥፋት በማቀድ፣ በማሠብ ጥቃት መፈፀም ማለት ነው፡፡ ያን ጥቃት መፈፀም እንግዲህ ዘር ማጥፋት ሊሆን ይችላል። ዘር ማጥፋት (ዲፖርቴሽን) ሊሆን ይችላል፣ ማፈናቀልም ሊሆን ይችላል፣ ልጆች እንዳይወልዱና የዘር መተካካቱ እንዳይቀጥል ማድረግም ሊሆን ይችላል፡፡

ይሄ እንግዲህ በሠው ዘር ላይ የሚሠራ ወንጀል ነው – ጀኖሣይድ ወይም የዘር ማጥፋት ወንጀል ነው። አሁን እኛ እንደምንገምተው አማሮችን ከየክልሉ የማባረሩና የማፈናቀሉ ነገር ቆይቷል፡፡ ከበደኖ ጀምሮ አርባጉጉ፣ ጉራፈርዳ አሁን ደግሞ ቤንሻንጉል… ሌሎችም አሉ፡፡ ይሄ ቢደረግም የአማራን ዘር በከፊልም ሆነ በሙሉ ለማጥፋት ታቅዶ የሚደረግ ነው ወይ ለሚለው ማስረጃ የለንም፡፡ እነዚህ ሠዎች ለመፈናቀላቸው ከቦታ ቦታ መነቀላቸው፣ ንብረታቸውን ማጣታቸው፣ በአካላቸው ላይ ጉዳት መድረሡን እናውቃለን፤ ማስረጃውም አለ። እንግዲህ የዘር ማጥፋት ሣይሆን የዘር ማጥፋት ወንጀል የምንለው ከነበሩበት አካባቢ በዘራቸው ምክንያት ከተፈናቀሉ ነው፡፡ አንድ ሠው በዘሩ፣ በሃይማኖቱ ወይም በሚናገረው ቋንቋ ምክንያት ጉዳት ከደረሠበት በሠው ዘር ላይ የሚሠራ ወንጀል ነው፡፡ አሁን ሠዎች በአማራነታቸው፣ በዘራቸው በተቀነባበረ መልክ ለብዙ ጊዜ የዘር ማጥፋት ወንጀል በዚህ መልኩ ተፈፅሞባቸዋል፡፡

በአካባቢው አንድ ዘር ብቻ እንዲኖር ካለ ፍላጎት፣ እነዚህ ዘሮች (አማሮች)ከሚኖሩበት ተፈናቅለዋል፡፡ እና ይሄ ዘር ማጥፋት ይባላል፡፡ ሁለተኛው የዘር ማጥፋት ወንጀል የሚጀምረው አንድ ሠው በሃይማኖቱ፣ በዘሩ ምክንያት በተቀነባበረ መልኩ በሠፊው ግድያ፣ መፈናቀል፣ የመሣሠሉ ነገሮች ከተፈፀሙበት ነው። ሁለቱም በጣም ከባድ ወንጀሎች ናቸው፡፡ በአለማቀፍ ህግ መሠረትም በተመሣሣይ የወንጀል ፈርጅ ነው የሚቀመጡት፡፡ ተመሣሣይ ቅጣት ያስከትላሉ፡፡ እኛ አሁን በኢትዮጵያ የተፈፀመው ወንጀል የዘር ማጥፋት ነው ብለን ደፍረን ባንወጣም፣ የዘር ማጥፋት ወንጀል ለመሆኑ ምንም ጥርጥር የለውም፡፡ በተለይ በአማራዎች ላይ ያነጣጠረ ነው፡፡ እኔ በአማርኛ ተናጋሪዎች ላይ የሚለውን አልቀበለውም፡፡ ምክንያቱም ሁላችንም አማርኛ ተናጋሪዎች ነን፡፡ በዚህ መሠረት አማራዎች ለረጅም ጊዜያት በተቀነባበረ መልኩ ከተቀመጡበት ሲፈናቀሉ ኖረዋል፡፡ ይህ ደግሞ በአለማቀፍ ህግም በሃገራችን የወንጀለኛ መቅጫ ህግም ወንጀል ነው፡፡

“በዘር ማጥፋት” ወንጀል መክሠስ የሚያስችላችሁ የህግ ማዕቀፎች አሉ? በደንብ አሉ፡፡

አሁን እኔ እንዳጋጣሚ የወንጀለኛ መቅጫ ህጉን አልያዝኩትም እንጂ ይሄን የሚቀጣ አንቀፅ አለ፡፡ እንደውም የደርግ ባለስልጣናት በዘር ማጥፋት ወንጀል ተከሠው ነበር፡፡ በእርግጥ ክሡ ትክክል ነበር ማለት አይቻልም፡፡ ምክንያቱም ወንጀሉ ያነጣጠረው የፖለቲካ ቡድንን መሠረት አድርጐ ነበር፡፡ የዘር ማጥፋት ወንጀል የምንለው በሃይማኖት፣ በቋንቋ እና በዘር ሲሆን ብቻ ነው፡፡ በፖለቲካ እምነት መሆን የለበትም፡፡ ከዚህ አንፃር በህጋችን የዘር ማጥፋት ምንድን ነው የሚለው በግልፅ ተቀምጧል፡፡ የዘር ማጥፋት ወንጀል ማለት በሠው ዘር ላይ የሚፈፀም ወንጀል ወይም ማፈናቀል መሆኑ በህጋችን በግልፅ ተቀምጧል፡፡ የደርግ ባለስልጣናትም የተከሠሡት አንደኛ በዘር ማጥፋት፣ ሁለተኛ ደግሞ በዘር ማጥራት፣ ሶስተኛ ደግሞ በተራ ግድያ ተጠያቂ ሆነው ነበር፡፡ ጉዳዩ ከመሬት እና ከይዞታ ጋር የተገናኘ እንጂ የዘር ጥላቻ አይደለም የሚሉ አካላት አሉ? የዘር ጥላቻ ሆነም አልሆነም ዋናው ነገር መፈናቀላቸው ነው፡፡

ከቤት ንብረታቸው ብዙ ጊዜ የኖሩበትን ቦታ በግድ ማስለቀቅ ጥላቻ ቢኖረውም ባይኖረውም ወንጀል መሆኑ አይቀርም። በህገ መንግስቱ አንቀፅ 32፣ የመዘዋወር መብትን በተመለከተ “ማንኛውም ኢትዮጵያዊ በህጋዊ መንገድ በሃገሪቱ ውስጥ የሚገኝ የውጭ ዜጋ በመረጠው የሃገሪቱ አካባቢ የመዘዋወርና የመኖሪያ ቦታ የመመስረት እንዲሁም በፈለገው ጊዜ ከሃገር የመውጣት ነፃነት አለው” ይላል፡፡ ደግሞ ለኢትዮጵያውያን ብቻ አይደለም፤ ለውጭ ዜጐችም ህጋዊ በሆነ መንገድ ወደ ኢትዮጵያ ከገቡ በፈለጉበት መኖርና ወደፈለጉበት መንቀሣቀስ ይችላሉ፡፡ ለውጭ ሃገር ሠዎች እንኳ መብቱ ተሠጥቷል፡፡ ማንኛውም ዜጋ በየትኛውም የሃገሪቱ ክልል ላይ መኖርና ሠርቶ መለወጥ ይችላል ማለት ነው፡፡ እርግጥ አንዳንድ የተከለሉ አካባቢዎች አሉ፡- እንደጦር ሠፈር፣ ቤተመንግስት፣ የእንስሣት ፓርኮች የመሣሠሉት … እዚያ ልግባ ቢሉም ልኑር ማለት አይቻልም፡፡ በተረፈ ግን ዘሩም ሆነ ቋንቋው ምንም ቢሆን የፈለገበት ቦታ ሄዶ የመኖር መብት እንዳለው ህገ መንግስቱ በግልፅ ይደነግጋል፡፡

አንድ ጊዜ ከጉራፈርዳ ስለተፈናቀሉ ሠዎች ጉዳይ በፓርላማው ጥያቄ ቀርቦ ነበር፡፡ ጠ/ሚ መለስ በወቅቱ እነዚህ ሠዎች ደን ይመነጥሩ ነበር ብለው መልስ ሠጡ፡፡ የዚህ አንደምታው የተወሠደው እርምጃ ትክክል ነው የሚል ነው፡፡ እነዚህ ሠዎች ዛፍ ይቆርጡ እንደሆነ ህግ ካለ በህግ ይጠየቃሉ፤ ጫካ ይመነጥሩ እንደሆነም እንደዚያው፡፡ አሁን አቶ ኃይለ ማርያም የተለየ መልስ ሰጥተዋል፡፡ አቶ መለስ ፍፁም ህጋዊ አድርገው የቆጠሩትን አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ ህገወጥ መሆኑንና መደረግ እንደሌለበት፤ መንግስትም እርምጃ እንደሚወስድ ገልፀዋል፡፡ ከአካባቢው አማራዎች ብቻ ሣይሆኑ ኦሮሞዎችም የመፈናቀል እጣ ገጥሟቸዋል ተብሏል።

ይሄንንስ እንዴት ነው የሚያዩት? በእርግጥ ጠ/ሚኒስትር ኃይለማርያም ብለውታል፡፡ ነገር ግን በአማራዎች ላይ እየደረሰ ያለው መጠነ ሰፊ ነው፡፡ የቆየም ነው፡፡ በግብታዊነት ሰዎችን ማፈናቀል በፕላን የተሠራ የቆየ ድርጊት ነው። ሊፈፀም የማይገባው ወንጀል ነው የተፈፀመው፡፡ አሁን ክስ እንመሠርትባቸዋለን ከምትሏቸው ሃላፊዎች መካከል በህዝብ ተመርጠው የምክር ቤት አባላት የሆኑ አሉ፡፡ የእነዚህን ሰዎች ያለመከሰስ መብት ከግምት አስገብታችኋል? እንግዲህ አንድ የህዝብ ተወካይ ሊከሰስ የሚችለው ፓርላማው የዛን ሰው ያለመከሰስ መብት ሲሰርዝ ነው፡፡ እነዚህ ሰዎች ምናልባት እንደዚህ አይነት ያለመከሰስ መብት እንዳላቸውና እንደሌላቸው ማጣራት ይኖርብናል፡፡

ካላቸው ፓርላማ ወይም ምክር ቤት በዚህ በዚህ ወንጀል ምክንያት ያለመከሰስ መብታቸውን መሰረዝ አለበት ብለን ማመልከት አለብን፡፡ ያኔ ምክር ቤቱ ፍቃድ ከሰጠና ከሠረዘ ይከሰሳሉ ማለት ነው፡፡ በእርግጥ ይህ ሂደት ካልታለፈ መክሰስ አይቻልም። የትኛውም ፓርላማ እንዲህ አይነት ከባድና ግልጽ ወንጀል በሚፈፀምበት ጊዜ ያንን ያለመከሰስ መብትን ያሠርዛል፡፡ እኛም የትኛው ነው ያለመከሰስ መብት ያለው የሚለውን ካጣራን በኋላ፣ አስቀድመን ለምክር ቤቶቹ አመልክተን መብቱ እንዲሠረዝ እንጠይቃለን፡፡ ክሳችሁ የሚያካትተው በየትኛው ጊዜ እና በየትኛው የሃገሪቱ ክልል የተፈፀሙትን ወንጀሎች ነው? አሁን ለጊዜው ቤንሻንጉል እና ጉራፈርዳ የተከሰተውን ነው ያሰብነው፡፡ ሌላው በቀጠሩን ፓርቲዎች የሚወሰን ነው፡፡ በእርግጥ ድርጊቱ በብዙ ቦታዎች የተፈፀመ ነው፡፡ ግን ክስ የሚመሠረተው አንድም እንዲህ አይነት ድርጊት ለወደፊቱ እንዳይደገም ማስተማሪያ እንዲሆን ነው፡፡

ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ እንዲቆም ለማድረግ ነው፡፡ ክስ ብዙ ጊዜ የሚመሠረተው ከክሱ ውጤት ሌላው እንዲማርና ተበዳዩ እንዲካስ ነው፡፡ ክሱ በአገር ውስጥ ፍ/ቤቶች ተቀባይነት ካጣ ወደ አለማቀፍ ፍ/ቤት እንሄዳለን ብላችኋል፡፡ ኢትዮጵያ የአለማቀፍ ፍርድ ቤት አባል ሳትሆን ክስ መመስረት ይቻላል? የክሱ አንዱና ዋናው አላማ ይህ ድርጊት ከእንግዲህ በማንም ኢትዮጵያዊ ላይ እንዳይፈፀም ነው፡፡ ሌላው ደግሞ ይሄ ክስ እዚህ ሊሳካልን ባይችል በአለማቀፍ ፍርድ ቤት ጉዳዩን የሚከታተሉ ኢትዮጵያውያን አሉ፡፡ ለነዚህ ኢትዮጵያውያን የዳበረ ማስረጃ ለመስጠት ነው፡፡ በአለማቀፍ ፍርድ ቤት ክስ ለመመስረት መጀመርያ የአገር ውስጡን ማጣራት አለብን፡፡ በአገር ውስጥ ፍትህ ከተነፈግን ወይንም የአገሩ መንግስት ሊሰማ ካልፈለገ ጉዳዩ ወደ አለማቀፍ ፍርድ ቤት ሊያመራ ይችላል፡፡ በፊት እንደተባለው ኢትዮጵያ የአለማቀፍ ፍርድ ቤት አባል አይደለችም፡፡ ለምን እንዳልሆነች እኔ በእውነት ሊገባኝ አይችልም፡፡ ምክንያቱም ከአፄ ኃይለስላሴ ጀምሮ በደርግም ዘመን ኢትዮጵያ አለማቀፍ ስምምነቶችን በመቀበል ንቁ ተሣትፎ ነበራት፡፡ የተባበሩት መንግስታትን ቻርተር ለመፈረም እኮ የመጀመሪያዎቹ ጥቁር ህዝቦች እኛ ነን፡፡

ኢህአዴግ ለምን ሊቀበለው እንዳልፈለገ አይገባኝም፡፡ ሆኖም ግን አገር ውስጥ ከባድ ወንጀል በሚፈፀምበት ጊዜ አባል አይደለችም፤ ስለዚህ አትከሰስም ተብሎ አይታለፍም፡፡ አባል ከሆነ በቀጥታ ፍርድ ቤቱ ጉዳዩ እንዲመረመር ያዛል፤ ተመርምሮ ክስ ይቀርብበታል። እንደ ኢትዮጵያ የፍርድ ቤቱ አባል ካልሆነ፣ ጉዳዩ ለተባበሩት መንግስታት የፀጥታ ምክር ቤት ቀርቦ፣ የፀጥታው ምክር ቤት ፍርድ ቤቱ ምርመራ እንዲያደርግና ክስ እንዲመሠርት ሊያደርግ ይችላል፡፡ አሁን ኢትዮጵያኖች የሚንቀሳቀሱበት መንገድ የተባበሩት መንግስታት የፀጥታው ምክር ቤት በጉዳዩ እጁን ያስገባና የአለማቀፍ ፍርድ ቤትን ምርመራ እንዲያደርግ ያዛል (ክስ እንዲመሠረት ሊያዘው አይችልም) ጉዳዩ ወደ ወንጀል ከመራ፣ ክሱ በተጐጂዎች ወይም ወኪሎች ሊቀርብ ይችላል፡፡ ኢትዮጵያ የአለማቀፍ ፍርድ ቤት አባል አለመሆኗ፣ ወንጀል ከተሰራ ከክስ ሊያስመልጣት አይችልም፡፡ እዚህ ፍትህ አለመኖሩ ከተረጋገጠ፣ በዚህ መልኩ ወደ አለማቀፉ ፍርድ ቤት እንሄዳለን፡፡

ክሱን የምትመሠርቱት ግለሰብ ባለስልጣናት ላይ ነው ወይስ ተቋማቱን ነው የምትከሱት?

ለምሣሌ ፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስቴርን እንደመስሪያ ቤት ነው ወይስ ሚኒስትሩን ነው? እኛ ተቋማቱን ነው የምንከሰው፡፡ እርግጥ ለተቋማቱ ተጠሪዎች አሉ፡፡ ተከሳሾች የሚሆኑት ደግሞ የክልል አስተዳዳሪዎች ብቻ አይደሉም። እንደውም ከፌደራል ጉዳይ መስሪያ ቤት ይጀምራል፡፡ እርግጥ አቶ ኃይለማርያም፤ ይሄ በኪራይ ሰብሳቢዎች፣ በሌቦች የተፈፀመ ነገር ነው፤ መንግስት አያውቀውም ብለው ነው መግለጫ የሰጡት፡፡ ይሄ ተአማኒነትና ተቀባይነት የሌለው ነገር ነው፡፡ ሃያ ሺህ ሰው ሲባረር አላውቅም ማለት የማንን ጐፈሬ ሲያበጥሩ ነበር ያስብላል፡፡ ፌደራል መንግስት ማወቅ ነበረበት፤ ባያውቅም የግዴታ ማወቅ ነበረበት። አላወቅሁም ካለም አለማወቅ ከተጠያቂነት ስለማያድን ማወቅ ይገባው ነበር፡፡ ባያውቅ እንኳ ማወቅ ስለሚገባው በህግ ይጠየቃል። በዚህ መሠረት ክሳችን ከፌደራል መንግስት ይጀምራል፡፡ ወደ ክልል አስተዳደሮች ይሄዳል። ከዚያም ወደ ወረዳ፣ ፌዴራል ፖሊስ እንዲሁም ከጉዳዩ ጋር ወደተነካኩት አካላት ይሄዳል፡፡

እንግዲህ ክሱ እንደገለጽኩት ገና አልተረቀቀም፤ በመነጋገርና መረጃ በማሰባሰብ ላይ ነው ያለነው፡፡ ሀገር ውስጥ ካሉት ፍርድ ቤቶች ምን ውጤት ትጠብቃላችሁ? የመጨረሻ ውጤቱስ ምን ይሆናል ብላችሁ ነው የምታስቡት? እኛ መቸም የምንጠብቀው ህጉ ይተገበራል ብለን ነው፡፡ የወንጀል ህጉም ሆነ ሌሎች ህጐች ይተገበራሉ ብለን ነው የምንጠብቀው፤ ግን የሚሆነው ሌላ ሊሆን ይችላል፡፡ ክሳችንን ውድቅ ሊያደርጉ ይችላሉ፡፡ ፍርድ ቤቱ ክሱን ተቀብሎ ካሣ የሚያስከፍል ወንጀል አላገኘንም ብሎ ክሱን ሊዘጋው ይችላል፡፡ ሆኖም ግን እኛ አስቀድሜ እንዳልኩት ይሄን ክስ ያነሳነው በአለማቀፍ ችሎት የቀረበ እንደሆነ፣ መጀመሪያ በሃገር ውስጥ ፍትህ ለማግኘት ተሞክሯል ወይ ተብሎ ስለሚጠየቅ ነው።

ፍትህ ለማግኘት ሞክሬ ፍትህ አላገኘሁም ወይም መንግስት ክሱን ለመቀበል ፈቃደኛ አልሆነም ካልክ፣ አለማቀፍ ፍርድ ቤት ጉዳዩን ሊቀበለው ይችላል፡፡ ለዚህ ድጋፍ እንዲሆን ነው ይህን ክስ የምንመሠርተው፡፡ በእውነት ፍትህ በሀገር ውስጥ አግኝተን ለእያንዳንዱ ካሣ ቢከፈል በጣም እገረማለሁ፤ እደነቃለሁ፡፡ ቢሆን ግን እሰየው ነው። ጉዳዩን እንዴት እንደሚያመልጡት አላውቅም፤ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ራሳቸው በደል ተፈጽሟል፣ ህግ ተጥሷል ካሉ እንዲሁ ዝም ብሎ ተነግሮ የሚታለፍ አይደለም፡፡ በደል ከተፈፀመ የግድ ለተበዳዩ የሚሆን ካሣ ይከተላል፡፡ ይሄ ሊሆን ግድ ነው፡፡ ይህ ባይሆን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ራሳቸው ተጠያቂ ይሆኑበታል፡፡ ወንጀል መሆኑን እያወቁ፣ በደል መፈፀሙን እያመኑ ዝም ብለው ካለፉት፣ ነገ በራሳቸው ቃል ተጠያቂ ይሆኑበታል፡፡


አቶ ስብሐትና የተንኮል ፖሊቲካ በፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም (መነበብ ያለበት)

$
0
0

ጥቅምት 2005  አቶ ስብሐት ነጋ ሙሉ ነጻነቱን የሚወድ ሰው መሆኑን አደንቅለታለሁ፤ አስቦም ይሁን ሳያስብ አንደልቡ የመናገር ባሕርይ አለው፤ በበኩሌ ይህንን ባሕርዩንና በመብቱ መጠቀሙን አከብርለታለሁ፤ ሀሳቡ የተሳሳተ ይሁንም አይሁንም… እኔ የምስማማበት ሆነ አልሆነም፣ እኔ ልቀበለውም አልቀበለው ስብሐት ነጋ በሙሉ ነጻነቱ ተጠቅሞ ሀሳቡን ሁሉ መግለጹን አከብርለታለሁ፤ እሱም የእኔን ሀሳብ የመግለጽ ነጻነት አንደሚያከብርልኝና እንደሚያስከብርልኝ ተስፋ አለኝ፤ ከዚያም በላይ ነጻነት ሁልጊዜም፣ የትም ቦታ ከኃላፊነት ጋር የተቆራኘ መሆኑን እንድንገነዘብ ያሻል፤ ኃላፊነት የሌለበት ነጻነት የለም፣ ኃላፊነት የሌለበት ነጻነት ስሙ ሌላ ነው፡፡ በቅርቡ አቶ ስብሐት በአደረገው ቃለ መጠይቅ አዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር የተሾመው ወያኔ ዱሮም አስቦበት ወንበሩን ከአማርኛ ተናጋሪዎችና ከኦርቶዶክስ አማኞች ለማጽዳት በተዘጋጀበት እቅድ ነበር ብሎአል፤ ልብ ላለው አነጋገሩ በሁለት በኩል ስለት ያለው ቂል የያዘው ሰይፍ ነው፤ ከፊት ለፊት የተሰነዘረው አማርኛ ተናጋሪውንና የኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን አማኙን ለመምተር ነው፤ ቂል የሚያደርገው አማራ የሚባል ጎሣ ቢኖርም የኦርቶዶክስ ሃይማኖት በአማርኛ ተናጋሪዎች ታጥሮ ትግሬንና ኦሮሞን፣ ወላይታንና ጉራጌን፣ ሌሎችንም የማይነካ መስሎት ከባድ ስሕትት ላይ መውደቁ ነው፤ ከሁሉም በላይ እሱን የሚያህል ሰው የተክለ ሃይማኖትን ታሪክ አለማወቁ ያሳዝናል፡፡ አማራንና የኦርቶዶክስ ተከታዮችን መትሮ ሲመለስ ደግሞ ሰይፉ የሚቀላው ወላይታንና ጴንጤነትን፣ ምናልባትም እስልምናን ይሆናል፤ አማራን ለመምተር ተነሥቶ ሌላውን ስንቱን ቀላው! እስልምናን በጥርጣሬ ያስገባሁት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ እስላም ነው የሚባል ያልተጣራ ወሬ በመስማቴ ነው፡፡ አቶ ስብሐት በፊት ለፊት የተናገረው ገና የዛሬ ሀያ አንድ ዓመት ‹‹እንዳያንሰራራ አድርገን አከርካሪቱን እንሰብረዋለን›› ተብሎ ያለቀለትን አማራ ዛሬ ወንበር ማጣቱን ለማብሰር አልነበረም፤ ይህ በጣም ግልጽና ከማንም ያልተሰወረው እውነት ነበር፤ ስውር ዓላማም አለው፤ ያንን ብዙ ሰው አይገነዘበውም ይሆናል፤ በአቶ ስብሐት አነጋገር ውስጥ ዋናውና ተንኮልን ያዘለው ዓላማ ወንበሩን የያዘው ዋናው የወላይታ ጴንጤ ሲሆን ምክትሉ ደግሞ እስላም መሆናቸውን ለመናገር ያለው ፍላጎት ላይ ነው፤ ከአቶ ስብሐት ነጋ በቀር የአዲሶቹን ሹሞች ዘርና ሃይማኖት ከጉዳይ ያስገባ ያለ አይመስለኝም፤ አቶ ስብሐት በፊት-ለፊት ዓላማው ተስፈንጣሪ ተራማጅ ሲመስል በስውሩ የተንኮል ዓላማው ግን ኋላ-ቀር ወግ-አጥባቂ ይሆናል፤ በዘርና በሃይማኖት ላይ ሲያተኩር ዋናውን ቁም-ነገር ጠቅላይ ሚኒስትሩና ምክትሉ ሰዎች፣ ከዚያም ቀጥሎ ኢትዮጵያውያን መሆናቸውን ፈጽሞ ዘንግቶታል፤ ለእኛ ትልቁ ነገር ይህ ነው፤ በሁለታችን መሀከል ያለው ልዩነት ስብሐት ኢትዮጵያውያንን የሚያዛምዳቸውን ሁሉ አያይም፤ እኔ ደግሞ ኢትዮጵያውያንን የሚለያያቸውን ሁሉ አላይም፡፡


አባይም ይቀየስ ኢህአዴግም ይቀየስ!”

$
0
0

የዘመናት ብሶት የወለደው ጀግናው የኢህአዴግ ሰራዊት ከዚህ በፊት ደርግ ሲጠቀምበት የነበረውን የሬድዮ ጣቢያ ለሰፊው ህዝብ ጥቅም ተቆጣጥሮታል፡፡ ጉንቦት ሃያ ሺ ዘጠኝ መቶ ሰማኒያ ሶስት አመተ መህረት!” አለ ታጋዩ…

 

 

“የዘመናት ብሶት የወለደው ጀግናው የኢህአዴግ ሰራዊት ከዚህ በፊት ደርግ ሲጠቀምበት የነበረውን የሬድዮ ጣቢያ አሁን ደግሞ ለራሱ ጥቅም ተቆጣጥሮታል፡፡ ቆጣጥሮታልም፤ ግንቦት ሃያ ሺ ዘጠኝ መቶ ሰማኒያ ሶስት አመተ መህረት!” አልኩ እኔ…

“ኢህአዴግ ደርግን ደመሰሰ እና ሌላ ቀዳበት”  አለ ልጅ ያሬድ!  ”ኢህአዴግ ደርግን ደምስሶ በደርግ ዜማ ሌላ ቀዳበት” አልኩ እኔ

ዛሬ ግንቦት ሃያ ነው፡፡

አነዛ ፀጉራቸውን አሳድገው አዲሳባ የገቡ ሰዎች ዲሞክራሲን እና መልካም አስተዳደር ያሳድጉልናል… ብሎ ተስፋ የጣለባቸው ሁሉ በቴስታ ብለው ከጣሉት እነሆ ሃያ ሁለት አመት እንደዋዛ ሆናቸው፡፡

መልካም አስተዳደሯንም ለራሳቸው እያደሯት፤ ዴሞክራሲዋንም ራሳቸው እየኮመኮሟት ህብረተሰቡን እንቁልጭልጭ አሉት፡፡

ዛሬ የግንቦት ሃያ በዓል ሲከበር የአባይ ወንዝን የማስቀየስ ስራ ይሰራል ተብሏል፡፡  ወንዙ ተቀይሶ ምን ላይ ሊሆን ነው… እንዴት ነው ነገሩ በሳፋ ነው እንዴ ግድቡ የሚሰራው… ብዬ ልጠይቅ ወይስ አልጠይቅ…!

አስታውሳለሁ፤ “አባይ ይገደብ በቃ” ብለው ጠቅላዩ የወሰኑት ከሁለት አመት በፊት “በቃ” በሚል ሀይለ ቃል …ኢህአዴግ ይበቃዋል ግንቦት ሃያን ዘንድሮ ለመጨረሻ ጊዜ እናከብራለን ከዛም ለድጋፍ ሰልፍ ወጥተን በዛው እንቀራለን፡፡ ኢህአዴግ እስካልወረደ ድረስም እቤታችን አንገባም…. የሚል እንቅስቃሴ በፌስ ቡክ በኩል ተጀምሮ የነበረ ጊዜ ነው፡፡

በዚህ በ”በቃ” ጦስ እነ ርዮት አለሙ እነ ውብሸት ታዬ እነ አቶ ዘሪሁን ገብረ እግዚአብሄር እነ ሂሩት ክፍሌ ወድያው  ለእስር ሲዳረጉ ቀስ በቀስ ደግሞ ሌሎችም ለቃሊቲ እና ለቂሊጦ ተዳርገዋል፡፡ (በተለይ የነዚህ ወዳጆቼን ፍርድ ሂደት ስከታተል ነበር እና አጋነንክ ቢሉኝም ባይሉኝም የአቃቤ ህግ ማስረጃ “በቃ የሚለውን የፌስ ቡክ እና የአደባባይ እንቅስቃሴ ትኩር ብላችሁ አይታችኋል” የሚል ነበር)

እንቅስቃሴው በፌስ ቡክ ተጀምሮ በየአደባባዩም “በቃ” የሚል ሃይለቃል በመፃፍ ተሟሙቆ የቀጠለ ነበር፡፡ በርካቶችም ግንቦት ሃያ መስቀል አደባባይ የሚፈጠረውን ተዓምር እያሰቡ አንድም ደስታ አንድም ፍርሃት ሲፈራረቅባቸው አንደነበር ትዝ ይለኛል፡፡

ይሄኔ አቶ መለስ ፈርሸው ዘየዱ፤ (ሁል ጊዜ ቁጭ ብለው አሰቡ… እያልንኮ ፍራሽ የሌላቸው አስመሰልናቸው… “ፈርቸው” ማለት ፍራሽ ዘርግተው እጅግ በተመስጦ ማሰብ ማለት ነው…) አስበው አስበውም፤ “ለምን አባይን አንገድበውም…” አሉ እርሳቸው ብለው እምቢ… እንዴት… ለምን… በምን… አይባልምና እሺ እሺ ተብሎ ተጀመረ፡፡  የዛን ጊዜውን ግንቦት ሃያም መንግስታችን ለአባይ ግድብ ድጋፍ ሰልፍ ውጡልኝ፡፡ አለ… በዛውም የህዝቡ የተቃውሞ ሃሳብ ተገደበ፡፡

የአቶ መለስን ብልጠት በመኮረጅ ፈተናዎች ይታለፋሉ ብለው የሚያምኑት አቶ በረከት ደግሞ ዛሬ እነሆ በግንቦት ሃያው አባይ ወንዝን የማስቀየስ ስራ እነደሚሰራ በቴሌቪዥናቸው ብቅ ብለው ነገሩን፡፡

ጥሩ ኮርጀዋል…! አኮራረጃቸው ስም ሁሉ ሳይቀር እንደሚቀዳ አይነት ኮራጅ ነው፡፡

ህዝቡ ይህንን ዜና ሲሰማ ምን አላቸው… የሚለውን ቤት ለቤት ሄደን መጠየቅ ብንችል ጥሩ ነበር፡፡ መጠየቅ ባንችል ግን መጠርጠር እንችላለን እና አንዲህ እንጠረጥራለን፤

“አባይ ይገደብ፤ ኢህአዴግም ይገደብ፤ አባይ ይቀየስ ኢህአዴግም ይቀየስ!” ሳይላቸው አይቀርም፡፡

abetokichaw.com


ይህ በደል እና ግፍ አይመለከተኝም ብሎ የቀረ ቀረበት!!!

$
0
0
 1ኛ.ኢትዮጵያ ሀገራችን የብዙ ሺህ ዓመት አኩሪ ታሪክ ያላት እና የተለያዩ ቋንቋዎች የሚነገርባት ፣ህዝቦ የቋንቋ ልዩነት ሳይገድበው አንዱ ከሌላው የተዋለደ፤ እጅግ ውብ እና ማራኪ ቋንቋ ፣ብህል ፣ልምድ፣ ወግ ፣አለባበስ እና አመጋገብ ወዘተ… የሚታይባት ድንቅ ሃገራችን ናት፡፡ ይሁን እንጂ የወያኔ መንግስት ስልጣን ከያዘ ለዚያውም በ21ኛ ክፍለ ዘመን አንድ ከሚያደርገን ኢትዮጵያዊነት በላይ የምንናገረው ቋንቋ እና የተወለድንበት አካባቢ መሠረት ያደረገ ጠባብ ጎሰኝነት ጎልበት እንዲኖረው ለማድረግ እየሞከረነው፡፡ ከዚህም በላይ በጎሣ መከፋፋሉ ሲያስቆጨን ይበስ ብሎ እናተ ከዚህ ቦታ ለቃችሁ ሂዱ! ይህ የእናንተ ቦታ አይደለም በማለት ዜጎችን ማፈናቀል፣ መግደል ፣ሀብት ንበረት ማውደሙ እና ዘረኝነትን ማስፋፋቱ ያላስቆጨው ያላንገበገበው ማነው ? ይህን ቁጭቱን እና በደሉን መግለፅ የማይፈልግ ማነው? 2ኛ. በዓለም ላይ ካሉ ታላላቅ እምነቶች መካከል ክርስትና እና እስልምና ዋንኞቹ ናቸው፤ እነዚህን እምነቶች በመቀበል እኛ ኢትዮጵያዊያን ከቀዳሚዎቹ መካከል እንገኛለን፤ ክርስትናን እና እስልምና እምነቱን መቀበላችን ብቻ ሣይሆን የተቀበልነው እምነት ህግና ሥርዓት አክብሮ በማስከበር ወደር አይገኝልንም፡፡ በእነዚህ ታላላቅ እምነቶች መንግስት እጁን በማስገባት የፖለቲካ ዓላማ ማስፈፀሚያ ለማድረግ ያልፈነቀለው ድንጋይ ምን አለ ? በተለይ በሙስሊሞች ላይ እየፈፀመ ያለው በደል እና በእምነቱ ተከተዮች (የሙስሊም መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴዎች) ላይ ያለጥፋታቸው በሐሰት በመወንጀል አሸባሪ ብሎ በእስር ማሰቃየቱ እጅን አስጨብጦ ጥርሱን ነክሶ ያልተቆጨ ማነው? 3ኛ. አንዶአለም… አራጌ፣ ናትናሄል መከንን፣ በቀለ ገራባ፣ ኦልባና ለሊሳ እና ሌሎችም የፖለቲካ እስረኞች እንደማንም ኢትዮጵያዊ የራሰቸው ንሮ እና ህይወት ያላቸው ናቸው፡፡ ይሁን እንጂ ነፃነት እና ፍትህ ለነሱ ሁለተኛ ጉዳይ አይደለም የመጀመሪያ ጥያቄያቸው ነው! ከራስ ወዳድነት አልፈው ይህ ጥያቄ የኛ ብቻ ሣይሆን የኢትዮጵያዊያን ጥያቄ ነው በማለት በአደባባይ ስለነፃነት እና ፍትህ የዘመሩ በዚህም አኩሪ ተግባራቸው በእኛ የኢትዮጵያዊያን ዘንድ ልዩ ቦታ የምንሰጣቸው ነን፡፡ ይሁን እንጂ የወያኔ መንግስት እነኚህ ምርጥ የኢትዮጵያዊያን በማሰር እያሰቃያቸው ይገኛል፤ ይህ ስቃያቸው ያልተሰማን ከዚህ ስቃይ እንዲወጡ ምን ባደርግ ይሻላል እያልን እራሳችንን ያልጠየቅን ስንቶቻችን ነን ? በሆነው ነገር ያልተቆጨ ማነው ? 4ኛ. በሀገር እና በህዝብ ላይ የሚፈፀም በደል ማቆም አለበት፤ መንግስት እየወሰዳቸው ያለው እርምጃ የዜጎች ሰብአዊእና ዲሞክራሳዊ መብቶችን የጣሱ ናቸው በማለት ሃሳብን በነፃነት የመግለፅ መብታቸውን ተጠቅመው ከምንም በላይ የጋዜጠኝነት ስነምግባር ጠብቀው ሚዛናዊ መረጃ ለእዝብ ያደረሱ ዓለም ዓቀፍ ተሸላሚ የሆኑ ጋዜጠኖች በእስር ላይ ይገኛሉ፡፡ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ፣ እርዮት ዓለሙ እና ውብሸት ታዬ በስራቸው ዓለም ያደነቃቸው አድናቆቱም በሽልማት የታጀበ መሆኑ ለማናችንም ግልፅ ነው፡፡ እነዚህ የዓለም ህዝብ ቆሞ ያጨበጨበላቸው ጋዜጠኞች የወያኔ መንግስት በሽብርተኝነት ወንጅሎ በማሰር እያሰቃያቸው ይገኛል ፡፡ ይህ አይቶ ወይም ሰምቶ ዝም ማለት እንዴትስ ይቻላል ? እነዚህ ከላይ የተዘረዘሩት አራት (4) ዋና ዋና ሃሳቦች ሀገርን እና ህዝብን የሚወድ ከምንም በላይ ለራሱ አላፊነት የሚሰማው ኢትዮጵያዊ ሁሉ ይህን በደል እና ግፍ የሚፈፅመውን አካል መጠየቅ እንደዚሁም እነዚህ በሐይል የተያዙ የኢትዮጵያ ልጆች እንዲለቀቁ መጠየቅ የሞራል ግዴታ ብቻ ሳይሆን እያንዳንዱ ለራሱ ሲል የሚያደርገው ነገር ነው ፡፡ ወዳጆቼ መቼም ምን ለማለት እንደፈለኩ ግልፅ ይመስለኛል ፤የፊታችን እሁ ድግንቦት 25 ቀን 2005 ዓ.ም ሰማያዊ ፓርቲ በጠራው የተቃውሞ ሠልፍ ቦታው ተገኝተን በአደባባይ ስለነፃነት እና ፍትህ ድምፃችን ከፍ አድርገን በህብረት እንዘምር !!! የዕለቱ ፕሮግራም ሰማያዊ ፓርቲ ማዘጋጀቱ እርግጥ ነው ቁም ነገሩ ግን ፓርቲው ያነሳው የህዝብ ጥያቄ ነው ! በህዝብ ላይ ደግሞ በደል እና ግፍ እየደረሰ ነው ይህ በደል እና ግፍ አይመለከተኝም ብሎ የቀረ ቀረበት፡፡
                                 Posted By Issa Adusemed

ለብዙ ኢትዮጵያውያን ግንቦት 20 ካለፈው ይልቅ መጪውን የሚፈሩበት ጊዜ ነው

$
0
0
ዛሬ ግንቦት 20 ነው።ግንቦት 20 የኢትዮጵያ የፖለቲካ መዘውር የተዘወረበት ለመሆኑ አሌ አይባልም። ዕለቱ እንደ አቶ ሃይለማርያም የመጀመርያ በጠቅላይ ሚኒስትርነት ማዕረግ እንዳደረጉት ንግግር …” ኢትዮጵያ ልትበታተን ስትል የዳነችበት ቀን” ነው ለብዙ ኢትዮጵያውያን ግን ግንቦት 20 ካለፈው ይልቅ መጪውን የሚፈሩበት ጊዜ ነው።ይህንን ሁለተኛውን ሃሳብ እኔም እጋራዋለሁ። ካለፈው ይልቅ መጪው ይቀርበናል።ያለፈውማ አለፈ።መጪው ግን ቢዘገይም ቢፈጥንም አይቀርም።እና ግንቦት 20 ካለፈው ይልቅ ለመጪዋ ኢትዮጵያ እንዴት አስጊ ያደርገዋል። ይህንን ለማብራራት ግንቦት 20 እንደ ሀገር ለኢትዮጵያ ይዞት የመጣውን በጥቂቱም መጥቀስ ይፈልጋል።ስለተሰራው የመንገድ እርዝመት፣ህንፃ፣ወዘተ ማተት ይቻላል።እርግጥ ነው መንገድ ተስርቷል።ህንፃ ተገንብቷል።ከተሞች ሰፍተዋል።ይህ ሁሉ  ግን መጪውን አስፈሪ ጊዜ ለሀገር ከመተው አልገታውም።

መጪውን አስፈሪ የሚያደርገው የግንቦት 20 ውጤቶች ምን ምን ናቸው?

እንድሜ ለግንቦት 20 ብዬ ብጀምርስ-

  • እድሜ ለግንቦት 20 ዛሬ ኢትዮጵያ በአለም ታይቶ በማይታወቅ መልክ በቁጥር ተከልላ ክልሎች ስለ ድንበሮቻቸው ሲደራደሩ አንዳንዴም ሲጋጩ ለማየት በቅተናል። ምሳሌ የአፋር እና ትግራይ፣ የሱማሌ እና ኦሮሞ፣ የአማራ እና አፋር ወዘተ መጥቀስ ይቻላል።
  • እድሜ ለግንቦት 20 አንድሰው ከአንዱ የሃገሪቱ ክልል ተነስቶ እንበል ደቡብ ወይንም ጅጅጋ  ገብቶ መሬት ገዝቶ ልረስ ወይንም ልነግድ  ቢል እርሱ ከመምጣቱ በፊት ከ 60 እና 70 አመት በፊት የሰፈሩቱ ከጉርዳፈርዳ፣ጋምቤላ፣ጅጅጋ እና አሶሳ ካለምንም ካሳ ሲባረሩ ያያል እና መጪው እያስፈራው አይሞክረውም።
  • እድሜ ለግንቦት 20 ወላጆች ልጆቻቸውን በፈለጉት ቋንቋ ትምህርታቸውን እንዲከታተሉ ለማድረግ በታሪካዊ አጋጣሚ የሚኖሩበት ክልል ቋንቋ ውጭ እንዳይስተምሩ ታግደዋል።ለምሳሌ ኦሮምኛ ተናጋሪ ልጁ በአማርኛ እንዲማር ቢፈልግ ግን በኦሮምያ ክልል ቢኖር አማርኛ ወደምነገርበት ክልል መሄድ ብቸኛ አማራጩ ነው።በምዕራቡ አለም የሚኖር አንድ ኢትዮጵያዊ ግን ልጁን በሀገሩ ቋንቋ እንዲያስተምር ባህሉን እንዲጠብቅ ድጋፍ ይደረግለታል።
  • እድሜ ለግንቦት 20 ኢትዮጵያ ወደብ አልባ ሆና የባህር ኃይሏን በትና  30 እና 40 ኪሎሜትር እርቀት የባህሩ ማዕበል ሲማታ እየተሰማ ከ85ሚልዮን በላይ ሕዝብ ወደብ አጥቶ የጅቡቲን እና የሱዳንን ወደቦች በከፍተኛ ገንዘብ እንዲከፍል ተወስኖበታል፣
  • እድሜ ለግንቦት 20  ጦርነት ቆመ በተባለበት ጊዜ በአዲስ አበባ ብቻ ከ 100ሺህ በላይ ”ጎዳና ቤቴ” ያሉ ሕፃናት መንገድ ላይ ፈሰው ኃላፊነት የሚወስድ መንግስት አጥተው ለማየት የበቃነው በግንቦት 20 ፍሬ ነው። (በቀድሞው መንግስት የተመሰረተው የሕፃናት አንባ እንዴት በአሁኑ መንግስት እንደፈረሰ ይህንን ሊንክ ከፍተው ቪድዮውን ይመልከቱ (http://gudayachn.blogspot.no/2013/05/main-play-list-on-home-page-playlist.html)፣
  • እድሜ ለግንቦት 20 ከሃያ ሁለት አመት በፊት ”የጫት ቤት” ብሎ በር ላይ መለጠፍ የምያሳፍርባት አዲስ አበባ ዛሬ ጫት በየዘርፉ ”የበለጩ ፣የባህርዳር፣ የወልሶ ጫት ቤት” ብቻ ተብሎ ሳይሆን የሚለጠፈው ”ጫት እናስቅማለን፣ እንፈርሻለን” ተብሎ የተፃፈባቸው ባብዛኛው ትምህርት ቤቶች የሚገኙበትን ቦታ ፈልገው የሚከፈቱ የጫት ቤቶች በዝተው ለመታየት በቅተዋል። ምን ይህ ብቻ ዩንቨርስቲዎቻችን በየዶርሙ ጫት ሸጉጠው ሲገቡ- ሲ ቃምባቸው ደጉ መንግስታችን በዝምታ አልፎ ትውልዱን ጫት ቃሚ አድርጎታል።
  • አድሜ ለ ግንቦት 20 ምሳ ሰዓት ላይ ከቢሮ ወጥተው ጫት ቅመው የሚመለሱ የባንክ ሰራተኞች፣መሀንዲሶች ወዘተ አፍርቷል ግንቦት 20።ከደንበል ህንፃ ጀርባ የሚገኙ የመቃምያ ቦታዎችን ብንመለከት በምሳ ሰዓት ደንበል ህንፃ የሚሰሩ ምሁራን ዩንቨርስቲ ሳሉ በተፈቀደላቸው የመቃም መሰረት ሥራ ከያዙ በኃላም ለመላቀቅ ትቸግረው ይታያል።እረ  እንዲያውም በሥራ ሰዓት ሾለክ ብለው የሚቅሙ ሰራተኞች መኖራቸውን የእዚህ ፅሁፍ ፀሐፊ እማኝ ነው። እድሜ ለግንቦት 20።
  • እድሜ ለግንቦት 20 ወላጅ አልባ ሕፃናት ጎዳና እንዳይወጡ በሕዝቡ የሚደገፍ እንደ ሕፃናት አምባ መስርቶ ከማሳደግ ይልቅ ለአንድ ሕፃን እስከ 25000 ዶላር መንግስት እየተቀበለ በጉዲፈቻ ስም ለአሜሪካ እና አውሮፓ የተቸበቸቡት እና ብዙዎች በህሊና ስቃይ እና የማንንነት ጥያቄ እንዲሰቃዩ የተደረጉት በግንቦት 20 ፍሬ ነው (ሰኔ 25/2012 እአአቆጣጠር  በቢቢሲ ድህረ ገፅ ላይ በወጣ አንድ ዘገባ መሰረት ኢትዮጵያ በአመት 5ሺህ በላይ ሕፃናት በማደጎነት ወደ አሜሪካ  ብቻ እንደሚሄዱ  እና አሜሪካ ከዓለም ላይ በማደጎነት ከምትወስደው ሕፃናት ኢትዮጵያውያን ሕፃናት ከ አምስቱ አንዱ እንደሆኑይገልፃል።(http://www.bbc.co.uk/news/world-africa-18506474)
  • እድሜ ለግንቦት 20 ሴት እህቶቻችን ተስፋ ቆርጠው ለአረብ ሀገር ባርነት  በአስርሺዎች የተጋዙት በሄዱበት ሀገርም ስበልደሉ የሚሰማቸው አጥተው አሳር ፍዳቸውን የሚያዩት ከግንቦት 20 ፍሬ ወዲህ ነው።
  • እድሜ ለግንቦት 20 ”የኤርትራ ጥያቄን ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ መፍታት የሚቻለው የ ሻብያን ሃሳብ በመቀበል ነው” ብለው ስያግባቡን የነበሩት  አቶ መለስ- ጦርነቱ አበቃ ከተባለ ከ ሰባት አመታት በኋላ ለዳግም እልቂት ”ድንበር” በሚል ሰበብ ዳግም የኢኮኖሚ ፀባቸውን ወደ ወታደራዊ ግጭት ቀይረው በአስር ሺዎች የረገፉት በ ግንቦት ሃያ ውጤት ነው፣
  • እድሜ ለግንቦት 20 ስደት ቀድሞ የነበረ ቢሆንም በከፍተኛ ተስፋ መቁረጥ በባህር፣በእግር ወዘተ ወጣቱ ከሀገር የሚወጣው ከግንቦት 20 ፍሬ ወዲህ ነው (ወደየመን በጀልባ ተሳፍረው ከገቡት ስደተኞች ከ 70%በላይ ኢትዮጵያውያን መሆናቸውን የተባበሩት መንግሥታት የስደተኞች ኮሚሽን በዘንድሮው ዘገባው መጥቀሱን ልብ በሉ) ፣
  • እድሜ ለግንቦት 20 ወጣቶች ተምረው በእውቀታቸው ሀገርንም መጥቀም ሲገባቸው፣የስራ ዕድል የሚያገኙበት ወይንም  ስነልቦናቸውን የሚጠብቅ ግን ለፈጠራ የሚያዘጋጅ የስራ መስክ ከመፍጠር ይልቅ በምረቃቸው ጊዜ (የአዲስ አበባ ዩንቨርስቲ  2004ዓም ምረቃ ላይ አቶ ጁነዲን ለተማሪዎቹ እንደተናገሩት)ከዩንቨርስቲ ሲወጡ  የኮብል ስቶን ሥራን መስራት እንደሚገባ የተነገራቸው በግንቦት 20 ውጤት ነው።
  • እድሜ ለግንቦት 20 በሚድያውስ ቢሆን (ጎረቤት ኬንያን ለማነፃፀርያ እንጠቀም) ኬንያ የህዝብ ብዛቷ 30 ሚልዮን ሲሆን እኛ 85 ሚልዮን መሆኑን እናስታውስ እና ኬንያ በይዘታቸውም ሆነ በአቀራረባቸው የመንግስት እጅ ያልተጫናቸው 8 የቴሌቭዥን ጣቢያ፣ 38 ራድዮ ጣብያዎች፣ ከእሩብ ሚልዮን በላይ አንባቢ ያላቸው በየቀኑ የሚታተሙ 4 ጋዜጦች (http://www.pressreference.com/Gu-Ku/Kenya.html#b) ሲኖሩ ሃሳብን የመግለፅ መብት እና በሀገሪቱ የፖለቲካ ጉዳይ ላይ የመወያየት ነፃነት ከእኛ ጋር ሊወዳደር የማይችል መሆኑን ስናስብ እና ጋዜጠኞች መንግስትን ወቀሱ ተብለው በአሸባሪነት ዘብጥያ መውረዳቸውን ስናስብ እድሜ ለግንቦት 20 እንላለን።
  • እድሜ ለ ግንቦት 20 ጋና ነፃነቷን ስታገኝ የገነባነው ስታድዮም ዛሬ ጋና ከነፃነት አልፋ እስከ መቶ ሺሕዝብ የሚይዝ ስታድዮም ስትገነባ እኛ አሁንም አንድ ለእናቱ በሆነ ስታድዮም መገኘታችን የግንቦት 20 ውጤት ነው።እርግጥ ነው በዛሬው የግንቦት 20 በዓል የስፖርት አካዳሚ ምረቃ በአል እየተከበረ ነው። ስታድዮምስ ?
  • እድሜ ለግንቦት 20 ቀድሞ ጉቦ የሚለው ቃል ሲነሳ ስለ 20 እና 30 ብር ጉቦ እናስብ ነበር። ዛሬ ጉቦ፣ሙስና እና ዝርፍያ ማለት አድገው ተመንድገው  ዝርፍያ ማለት የብሔራዊ ባንክን የወርቅ ክምችት በወርቅ መሰል ነገር መቀየር ሲሆን ጉቦ ማለት ደግሞ የሀገር መሬት እና ውሃን  ለሕንድ እና ለአረብ በርካሽ መቸብቸብ ፣ በባለስልጣናት ቤት እንደባንክ ቤት በኢይሮ ብሉ በዶላር ቢሉ በፈለጉት የገንዘብ አይነት ከቤት ማስቀመጥ ማለት ነው (በቅርቡ የግምሩክ ባለስልጣናት ቤት  ተገኘ የተባለውን ብር ያስታውሱ)።

ይህንን ሁሉ ስናስብ ነው እንግዲህ ግንቦት 20 ካለፈው ይልቅ መጪውን የሚያስፈራ የሚያደርግብኝ።ከሁሉ የከፋው ግን መንግስት ስለሰራሁት መንገድ እና ድልድይ ስታመሰግኑኝ መስማት ብቻ ነው የምፈልገው ከማለቱም በላይ መሰረታዊ ስህተቶችን ”የጨለምተኞች አመለካከት’፣ የአመለካከት ችግር” እያለ ማጣጣሉን መቀጠሉ ነው አሳዛኙ።

አበቃሁ

ጌታቸው, ኦስሎ


አባይ የሰብአዊ መብቶች ጥሰት መደበቂያ አይሆንም!

$
0
0

በስዊትዘርላንድ የሚገኙ የሲቪክ ተቋማት፣ የፖለቲካ ሃይሎችና፣ የዴሞክራሲና ሰብአዊ መብቶች ግብረ ሃይል የጋራ አቋም መግለጫበኢትዮጵያ ላለፉት ሁለት አስርት አመታት በስልጣን ላይ ያለው ራሱን ወያኔ /ኢህአዴግ… ብሎ የሚጠራው ገዢ አምባገነናዊ ቡድን በነዚህ አመታት የፈጸማቸውን እንዲሁም አሁንም እየፈጸማቸው ላሉት ግፎች መደበቂያ ይሆነው ዘንድ አፍራሽ ቀያሽ በሆነው መሃንዲሱ ሟቹ መለስ ዜናዊ አማካይነት የህዝቡን ቀልብ ይስብልኛል ያለውን የአባይ ግድብ ግንባታ ፕሮጀክት ከዛሬ ሁለት ዓመት ቀደም ብሎ በሚያዚያ ወር 2003 ማወጁ ይታወሳል፣ በመሰረቱ ግድቡ ጥልቅ ጥናት ያልተደረገበት፣ ከበስተጀርባው ውስብስብና ያልተፈተሹ ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊ፣ ማህበራዊና፣ ዲፕሎማሲያዊ ችግሮችን አግተልትሎ የያዘና ይልቁንም በወቅቱ በቱኒዚያ በግብጽና ሌሎች በዓረቡ አለም አካባቢዎች የተነሳውን ህዝባዊ ቁጣና ማእበል እንዳይዛመት ብሎም የህዝብን ቀልብ ለመስረቅ ተብሎ እንደሆነ የኢትዮጵያ ህዝብ አስቀድሞ ያውቀዋል። በመሆኑም የተጠቀሱት አንኳር ችግሮች እንደተጠበቁ ሆነው መሰረታዊ የሆኑትን የህዝቦችን ጥያቄ ሳይመልሱ በአባይ ስም ህዝብን እያጭበረበሩ መኖር አይቻልም።

ገዢው ቡድን ስልጣን ላይ ከወጣበት ከመጀመሪያዎቹ አመታት ጀምሮ በዴሞክራሲያዊነት ስም እያጭበረበረ ነገርግን በስውርም በገሃድም ዜጎችን በማሸማቀቅ፣ መብቶቻቸውን በማፈን፣ ያለፍርድ በማሰር፣ ሲከፋም በመግደል ግፈኝነቱን አጠናክሮ የቀጠለበት ሲሆን ለዚህም በአገዛዙ የመጀመሪያ ምእራፍ የተፈጸሙት የአርባ ጉጉ፣ የበደኖ፣ እና አኙዋክ ማህበረሰቦች ጅምላ ጭፍጨፋ በቂ ምስክሮች ናቸው።

በወራሪ ስም ፋይዳው ለማይታወቅ ይልቁንም የሃገሪቱን ግዛት አሳልፎ ለሰጠውና የአገዛዙን እድሜ ለማራዘም በተከፈተው የኢትዮ_ኤርትራ ጦርነት ላይ ቁጥራቸው ከ60, 000 በላይ ወንድሞቻችን በበረሃ ደማቸው ከንቱ ሆኖ ቀርቶአል። ሲቀጥልም የይስሙላ ዴሞክራሲያዊነት ልፈፋውን የልመና ቋት/ከረጢቱን/ የሚሞሉለት ምእራባውያን እንዲሰሙለት በ1997 ዓም ነጻ ምርጫ አካሂዳለሁ በማለት ለፍፎ “በለፈለፉ ባፍ ይጠፉ“ እንዲሉ አምባገነኖቹ ገዢዎች በህዝብ ማእበል ተውጠው ያወሩበት ምላስ ሳይታጠፍ በህዝብ ድምጽ ላያገግሙ ተቀጡ ። ሆኖም ግን ይህን የህዝብ ማእበል ባዘጋጇቸው ቅጥር ነፍሰ ገዳይ አጋኧዚዎች በጥይት አረር አነደዱት። በዚህም ሳቢያ ከ200 በላይ ወገኖቻችን ግንባርና ደረታቸውን በጨካኞች ጥይት ተበስተው በየጎዳናው ወደቁ፣ የፖለቲካ መሪዎች፣ የሲቪክ ተቋማት መሪዎችና አባላት፣ጋዜጠኞች፣ የሰ/መብት ተሟጋቾች ወጣቶች፣ የ70 እና የ80 ዓመት አዛውንቶች፣ ከ13 እስከ 18 ዓመት ያሉ ታዳጊ ህጻናት ሳይቀሩ የእስር ሰለባ ሆነዋል።

ከዚህ በኋላ ይህ ገዢ ቡድን የወሰዳቸው አረመኔያዊ እርምጃዎች ሃገሪቱን ቁልቁል ወደ ገደል ነዳት ።ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊ፣ ሃይማኖታዊ፣ እንዲሁም ባህላዊ እሴቶቻችን በሙሉ ተንኮታኩተው የህዝቡም ስነ ልቦና ተሰብሮ ሳይጠገን ቆየ። በዚህ /ገዢዎች በደረሰባቸው ሽንፈት/ ሳቢያ ራሳቸው የደነገጉትን ህገ መንግስት ራሳቸው ጣሱት፥ የመሰብሰብ፣ የመደራጀት፣ ሃሳብን በነጻ የመግለጽ፣ ሰላማዊ ሰልፍ የማድረግ፣ በነጻነት የመዘዋወር፣ ዜጎች በመረጡት ስፍራ የመኖር፣ የፈለጉትን የማምለክ የመከተልና እምነቱን በነጻነት የማስፋፋት፣ ዜጎች ያለፍርድ ቤት ትእዛዝ ያለመያዝና መኖሪያ ቤታቸው ያለመፈተሽ፣ ሰርቶ የመኖር፣ የንብረት ባለቤት የመሆን መብቶቻቸው በሙሉ በአንድ ጠ/ሚኒስቴር ትእዛዝ ታገዱ።

በተጨማሪም ያለህግ በአንድ ሰው በሟቹ መለስ ዜናዊ ትእዛዝ ከተከለከሉት መብቶች ውጪ “የጸረ ሽብር ህግ“ በሚል ስያሜ የወጣ በራሱ ሰላማዊውን ዜጋ የሚያሸብር ሕግ በማውጣት ጭል ጭል ባለችው ኩራዝና በአንድ አይን በምትታይ ሜዳ ላይ የተሰበሰቡትንና የሚቃወሙትን ኃይሎች ሰብስቦ እስር ቤት አጉሮአል ። “የነፃ ፕሬስ መተዳደሪያ” በሚል ባወጣው ደንብ ደግሞ ጋዜጠኞች፣ ፀሐፊዎችና የኪነ-ጥበብ ሰዎች እንዲሳቀቁና ራሳቸውን ሳንሱር እንዲያደርጉ የሚያስገድድ ሕግ በማውጣት ሲገፋም እውነትን የሚፅፉ ጋዜጠኞችን እጁ የደረሰባቸውን ለቅሞ ሲያስር ቀሪዎቹ በግፍ ለመሰደዳቸው ምክንያት ሆኖአል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ እነዚህን ግፍና በደሎች ሁሉ በትጋት በመፈፀም ላይ እያሉ የህዝቡን የለውጥ ስሜት ለማቀዝቀዝ የኢትዮጵያን ሚሊኒየም እንደ መልካም አጋጣሚ ያዩት ገዥዎች አድርባይ ካድሬዎቻቸው በሚሊኒየሙ ሚሊዮን ብሮችን ያለአግባብ በማፍሰስ የህዝቡን ቀልብ መግዛት ሽተው ነበር፣ ሆኖም ለአንድ ዓመት ሙሉ በየቦታው ሊከበር የታቀደው ሚሊኒየም ከአንድ ሳምንት ጭፈራና የካድሬዎች አስረሽ ምችው ሳያልፍ የህዝቡ ስሜት ተመልሶ ቦታው ገባ ። እንደሚታወቀው ከዚህ ሚሊኒየም በሁዋላ የሀገሪቱ ኢኮኖሚ ዳግም በነሱ(በገዢ ቡድኖቹ) አቅም ሊስተካከል በማይችል መልኩ ተንኮታኮተ፣ የኑሮ ውድነቱ ሕዝቡን አማረረ፣ ስደት በየአቅጣጫው በከፋ መልኩ ተበራከተ፣ የአዛውንት እናትና አባቷን በረሃብና በእርዛት መቆራመድ ዘወትር ማየት ያልቻለች ሴት ለአረብ ግርድና ራሷን አሳልፋ ሰጠች፣ ወንዱም ከረሃብና እንግልት በየመንና ቀይ ባህር ሰጥሞ መሞትን የተመኘበት ዘመን መጣ፣ ታላላቅ የትምህርት ተቅዋማት በገዢው ክፉ የፖለቲካ ቅርሻት ተመረዙ፣ ከዚህ አልፈውም ትምህርታቸውን ጨርሰው የሚወጡትም ዕጣቸው የመንገድ ድንጋይ ንጣፍ ማንጠፍ ሆነ።

ገዢው ቡድን እነዚህን ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ምስቅልቅሎችን ሳይፈታ በእምነት ተቅዋማት ውስጥ ገብቶ መፈትፈት ጀመረ ።ቤተክርስቲያንን አይታ የማታውቀው የጨለማ ዘመን ውስጥ ጨመራት፣ ገዳማት ቅዱሳት መካናት መታረስ ጀመሩ፣ አብያተ ክርስቲያናት የካድሬና የፌደራል ፖሊስ መፈንጫ ሆኑ፣ ባህታውያንና መናንያን ተደበደቡ ታሰሩ፣ ሙስሊም ኢትዮጵያውያን “ድምፃችን ይሰማ “እንዳሉ ጆሮ ዳባ ልበስ ብሎ ይሄው ዓመት አለፈ ከዚህም አልፎ መሪዎቹን አሸባሪ በማለት ሰብስቦ አሰረ ፣ አንድ ብሔር ላይ ያነጣጠረና አማርኛ ተናጋሪውን ብቻ ኢላማ ያደረገ የዘር ማጥፋት እንዲሁም የዘር ማጥራት አሰቃቂ ወንጀል ፈፀመ፣ ለአመታት ከኖሩበት አካባቢ ሃገራችሁ እዚህ አይደለም በማለት ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና፣ ማንነታዊ ቀውስ አስከተለ፣በኢንቨስትመንት ስም ዜጎች ከቀዬአቸው ተፈናቀሉ።

እነዚህንና ሌሎችንም ያልተጠቀሱ ዘግናኝ ወንጀሎችን የፈፀመው ገዢ ቡድን ግፉን ይሸፍንልኛል በማለት ለዘመናት ስለተዘፈነለት የቅኔ ሰዎች ብዙ ስለተቀኙለት አባይ አሰልቺ ዘፈን ያላዝን ገባ፣ መጀመሪያ ላይ ያነሳናቸው ተግዳሮቶች እንደተጠበቁ ሆነው ከሁሉም በፊት አሁንም በፅናት የምንለው መሰረታዊ የህዝቦች መብቶች ይከበሩ፣ ግፍ ይቁም፣ ዘረኝነት ይወገድ፣ የህሊናና የፖለቲካ እስረኞች ይፈቱ ! በመሆኑም በአባይ ስም በሀገር ውስጥ ካለው ምስኪን ሕዝብ ከወር ደመወዙ የሚለቃቅመውና ከዲያስፖራው የሚሰበስበው ገንዘብ መብቶችን ለማፈን የካድሬዎችን ቁጥር ለመጨመርና የተቃውሞ እንቅስቃሴዎችን ለማፈን በቀጥታ ስለሚጠቀምበት በሌላ በኩል ደግሞ ገዢው ቡድን መንግስት ነኝ ብሎ ያለሕዝብ ፈቃድ ራሱን የሰየመው ወያኔ/ኢህአዴግ ላይ ፍፁም እምነት ስለሌለን ከግድቡ በፊት ፍትህ ፍትህ ፍትህ እያልን እንጮሃለን፣ ሕዝባዊና የምናምነው መንግስት እንሻለን ።

በዚህም መሰረት በገዢው ቡድን በጁን 1 በስዊትዘርላንድ ጄኔቫ ከተማ ለማካሄድ የታቀደውን የገንዘብ ዘረፋ ዘመቻ ለመቃወም እንዲሁም ለማክሸፍ ሃገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን ቀን ቆርጠናል፣ በሌላ በኩል ደግሞ በማወቅም ይሁን ባለማወቅ የወያኔ ተልዕኮ አስፈጻሚ ለሆናችሁ በሙሉ ከህሊና ወቀሳ በላይ የታሪክ ተወቃሸነት እንዳለ አውቃችሁ በዚህ የግፍ ድርጊት እንዳትሳተፉ ለማሳሰብ እንወዳለን። ስለዚህም በፍራቻም ሆነ በጥቅማጥቅሞች ተታላችሁ የዚህ ዝግጅት ተባባሪ የሆናችሁ ባለሃብቶች፣ ባለሬስቶራንቶች፣ አርቲስቶች በስዊትዘርላንድም ሆነ በሌላ ሃገር ያሉ ኢትዮጵያውያን እንዲያውቋችሁና አገልግሎቶቻችሁን እንዳይጠቀሙ የምናጋልጥ መሆኑን፣ እንዲሁም የእምነት ተቋማትና ግለሰቦችን ጨምሮ የነጻነት ትግሉ አካል እንድትሆኑ ጥሪያችንን እያስተላለፍን፣ ከአባይ በፊት የእምነት ነጻነት ይከበር፣ ዜጎችን ከቀዬአቸው ማፈናቀል ይቁም፣ “አባይም የሰብአዊ መብቶች ጥሰት መደበቂያና የአምባገነኖች እድሜ ማራዘሚያ አይሆንም” !!! እንላለን።

ትንሣኤ ለኢትዮጵያ—ድል ለተጨቆኑት!


ኢትዮጵያዊቷ ወጣት በአትላንታ 25 ዓመት እስር ተፈረደባት

$
0
0

ኢትዮጵያዊቷ ወጣት ሮዳስ ተክሉ እዚህ አትላንታ ከተማ በዋለው የወንጀል ጉዳዮች ችሎት ቀርባ ጉዳይዋ ሲታይ ከቆየ በኋላ ባለፍው ሰኞ MAY 20/2013  25 ዓመት እስር ተፈረደባት። ሮዳስ ተክሉ ይህ የተፈረደባት የሰው ነፍስ በማጥፋቷ ወንጀሉንም መፈጸሟን በማመኗ ነው… የኋላ ታሪኩ እንዲህ ነው። ፌብሩዋሪ 5 ቀን 2009 አመሻሽ ላይ በአትላንታ የተፈጸመው ወንጀል መላው የአትላንታ ነዋሪ የሆኑ ኢትዮጵያውያንን በቅርብ፣ ነገሩን የሰሙና በሌሎች ከተሞች ያሉትን ደግሞ በሩቅ ያስደነገጠ ነበር። 3754 ቢፈርድ ሃይዌይ የሚባለው የአትላንታ መንገድ ላይ የጸጉር መከርከሚያ ሱቅ ከፍቶ በመስራት ላይ የነበረው ኤርሚያስ አወቀ ፣ ማምሻውን ጭምር አምሽቶ እየሰራ ነበር። ከምሽቱ 8 ፒ ኤም አካባቢ ሮዳስ ተክሉ ሱቁ ድረስ መጣች። የፖሊስ ሪፖርት እንደሚያሳየው ሮዳስ ሱቁ ድረስ ከመጣች በኋላ ጭቅጭቅ ተጀመረ። እሱ እንድትወጣለት ቢጠይቃትም አልወጣችም። ይልቁኑ በእጇ ሽጉጥ ይዛ ስለነበር ፣ ስልኩን አንስቶ 911 ደወለ፣ ስልኩን ላነሳችው ኦፕሬተር “አንዲት ሴት ሱቄ ድረስ መጥታ ልትገለኝ እያስፈራራችኝ ነው፣ መሳሪያ ይዛለች .. እያለ ገና ተናግሮ ሳይጨርስ ስልኩ ተቋረጠ። ከዚያ በኋላ በአካባቢው የነበሩ ሰዎች የጥይት ድምጽ መስማታቸውን ይናገራሉ። ፖሊስ ካለበት፣ ነገሩን የሰሙም በጸጉር ቤቱ አካባቢ ሲደርሱ ኤርሚያስ በደም ተነክሮ ወድቋል፣ ወዲያው ወደ ሆስፒታል ተወሰደ ፣ ሆስፒታል ሲደርስም ህይወቱ አለፈ። በወቅቱ አንዲት ሴት ከቤቱ ወጥታ ስትሄድ አይተናል ከሚል ጥቆማ ውጪ ማን ገደለው የሚለው ጥያቄ እንቆቅልሽ ሆነ። በማግስቱ ፌብሩዋሪ 6 ግን ፖሊስ ሮዳስ ተክሉ የተባለችና የቀድሞ ፍቅረኛው ነች የተባለች ሴት በጥርጣሬ መያዙን አስታወቀ። እሷም ወደ እስር ቤት ተወሰደች። ኤርሚያስም የፖሊስ ምርመራ ከታወቀና ዶክተሮች የሞቱን መንስኤ ካስታወቁ በኋላ ፌብሩዋሪ 11 ቀን በርካታ የአትላንታ ነዋሪ ኢትዮጵያውያን በተገኙበት በጸጉር ቤቱ ደጃፍ የሻማ ማብራት ሰነ ስር ዓት ተካሄደ፣ በማግስቱ ፌብሩዋሪ 12 ጸሎተ ፍትሃት ከተደረገለት በኋላ አገር ቤት ተወስዶ እንዲቀበር በተያዘለት ፕሮግራም ይሄዳል ሲባል ፣ ፖሊስ ተጨማሪ ምርመራ ያስፈልገኛል በማለቱ እስከ ፌብሩዋሪ 24 ሳይላክ ቆየ። ፌብሩዋሪ 24 ቀን ግን አስክሬኑ ወደ አገር ቤት ለቀብር ተላከ። ከዚያ በኋላ ዜናው በአድማስ ሬዲዮም ሆነ አትላንታ ባለው ድንቅ መጽሔት ከወጣ በኋላ በወቅቱ የወጣት ሮዳስ ተክሉ ቤተሰቦች “እሷ በግድያው የለችበትም፣ ይህንን ድርጊት እሷ ትፈጽማለች ብሎ ማሰብ ትክክል አይደለም” ሲሉ ተናግረው ነበር። ሆነም ቀረ ላለፉት አራት ዓመታት ነገሩ ከፍርድ ቤት እስር ቤት ፣ ከ እስር ቤት ፍርድ ቤት ሲንከባለል ቆየ፣ የ ኤርሚያስ አወቀ የቅርብ ቤተሰብ የሆኑት አቶ ላቀው ለአድማስ ሬዲዮ እንደገለጹት በመካከል ተጠርጣሪዋ ልጅ፣ በጠበቆቿ አማካኝነት “አእምሮዋ ትክክል አይደለምና ለፍርድ ልትቀርብ አይገባም” ብለው ሲከራከሩ የቆዩ ሲሆን፣ ዳኞቹም የ አ ዕምሮዋ ነገር በሃኪሞች እንዲታይ ፈቅደው ቆይተዋል። በኋላ ግን ችሎት መቆም እንደምትችል በመታመኑ ፣ ጉዳዩ በከሳሽ አቃቤ ህግ እና በተከሳሽ ሮዳስ ተክሉ ጠበቆች መካከል ክርክሩ ቀጥሎ አራት ዓመት ከፈጀ። እንደ አቶ ላቀው ገለጻ ፣ በመጨረሻ ላይ ሮዳስ ወንጀሉን መፈጸሟን እንድታምን ተጠይቃ “አዎ ፈጽሜያለሁ፣ ነገር ግን በደም ፍላትና ሳላስበው ያደረኩት ነው” ስትል በማመኗ ዳኛዋ 25 ዓመት ጽኑ እስራት ፈርደውባታል። ምናልባት ጥፋቷን ባታምን እና ነገሩ በክርክሩ ብትሸነፍ የሞት ፍርድ ሊጠብቃት ይችልም ነበር ብለዋል። ዳኛዋ በፍርድ ውሳኔያቸው እንደገለጹት “ ኤርሚያስ ገበየሁን በ 10 ጥይት መግደል ሳይታሰብ፣ ባጋጣሚ የተደረገ አይደለም” ሲሉ ውሳኔያቸውን አጽንተዋል። በተያያዘ ሁኔታ ሮዳስ ተክሉ እዚያው እስር ቤት እያለች አንዲት ሴት ልጅ መውለዷም ታውቋል። የወለደችው ግሬዲ ሆስፒታል በፖሊስ ታጅባ ሄዳ ሲሆን፣ ባሁኑ ሰአት ህጻኗን አንዲት ነርስ እዚያው ግሬዲ እያሳደገቻት መሆኑ ሲታወቅ፣ የህጻኗን አባት በተመለከተ ዳኛዋ “የቀረበልኝ የዲ ኤን ኤ ምርመራ ስለሌለ፣ በልጅቷ አባት ጉዳይ የምሰጠው አስተያየት የለም” ሲሉ መናገራቸውም ታውቋል። (ምንጭ አድማስ ሬዲዮ አትላንታ)



ጋዜጠኛ ሙሉቀን ተስፋሁን ታሰረ

$
0
0

“ኢትዮ-ምኅዳር” ለሚባለው ሣምንታዊ ጋዜጣ ከአማራ ክልል ሲዘግብ የቆየው ሙሉቀን ተስፋሁን በቤንሻንጉል-ጉምዝ ፖሊስ መያዙን የጋዜጣው ምንጮች አስታወቁ….

“ኢትዮ-ምኅዳር” ለሚባለው ሣምንታዊ ጋዜጣ ከአማራ ክልል ሲዘግብ የቆየው ሙሉቀን ተስፋሁን በቤንሻንጉል-ጉምዝ ፖሊስ መያዙን የጋዜጣው ምንጮች አስታወቁ።ስለጋዜጠኛው እሥራት ከአካባቢው ፖሊስ መልስ ለማግኘት የተደረገው ሙከራ አልተሣካም።

 

የቤንሻንጉል-ጉምዝ ወረዳዎች

ሙሉቀን ከተያዘበት ዕለት ጀምሮ ይህ ዘገባ እስከተጠናቀረበት ጊዜ ድረስ ፍርድ ቤት እንዳልቀረበም የቅርብ ዘመዶቹ ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገመንግሥት “የተያዙ ሰዎች በአርባ ስምንት ሰዓታት ውስጥ ፍርድ ቤት የመቅረብ መብት አላቸው” ሲል በአንቀፅ 19 ንዑስ አንቀፅ 3፤ “ማንኛውም ሰው ያለማንም ጣልቃ ገብነት ሐሣቡን የመግለፅ ነፃነት አለው፤ ይህ ነፃነት በሃገር ውስጥም ሆነ ከሃገር ውጭ ወሰን ሳይደረግበት በቃልም ሆነ በፅሁፍ ወይም በሕትመት፣ በሥነጥበብ መልክ ወይም በመረጠው በማንሃውም የማሠራጫ ዘዴ ማንኛውንም ዓይነት መረጃና ሐሣብ የመሰብሰብ የመቀበልና የማሠራጨት ነፃነቶችን ያካትታል” ሲል በአንቀፅ 29 ንዑስ አንቀፅ 2 ያረጋግጣል፡፡ እንዲሁም በአንቀፅ 29 ንዑስ አንቀፅ 3 እና ንዑስ አንቀፅ 3/ለ የሚከተለው ሠፍሯል “3. … የፕሬስ ነፃነት የሚከተሉትን ሕጎች ያጠቃልላል…፤ …ለ/ የሕዝብን ጥቅም የሚመለከት መረጃ የማግኘት ዕድልን”

ጋዜጠኛ ሙሉቀን ተስፋሁን ዓርብ ግንቦት 16/2005 ዓ.ም ጀምሮ በቤንሻንጉል-ጉምዝ ክልል ዶቢ በምትባል የገጠር መንደር ፖሊስ ጣቢያ ታስሮ መቆየቱንና እስከዛሬም ማክሰኞ ግንቦት 20/2005 ዓ.ም ፍርድ ቤት አለመቅረቡን ቅርበት ያላቸውና ማንነታቸው እንዳይጠቀስ የጠየቁ ምንጮች ለቪኦኤ ገልፀዋል፡፡

በዶቢ ቀበሌ እሥር ቤት ውስጥ ሣለ ሙሉቀንን ባለቤቱና ወንድሙ ሄደው የጎበኙት ሲሆን ማክሰኞ፣ ግንቦት 20/2005 ዓ.ም ጠዋት ግልገል በለስ በተባለ ሥፍራ ወደሚገኘው የዞኑ እሥር ቤት መወሰዱን ምንጩ ጠቁመዋል፡፡

ሙሉቀን ለላከው “ኢትዮ-ምኅዳር” ጋዜጣ መረጃ በመሰብሰብ ላይ እያለ ፖሊሶቹ ጋዜጠኛ ለመሆኑ ማስረጃ እንዲያቀርብ ጠይቀውት ማሣየቱንና “በፖለቲካ ነው የምንፈልግህ” ብለው እንደወሰዱት፤ በአካባቢው የነበሩት ሰዎች “ለምን ትወስዱታላችሁ?” ብለው ሲጠይቁም “እናንተንም እናስራችኋለን” ብለው ያስፈራሯቸው መሆኑን ገልፀዋል፡፡


‹‹አገሬን ያወቅኋት አሁን ነው፤ ዜጋ ነኝ ለማለት አይቻልም፤›› አቶ ነጋ፣የኮሚሽኑ መርማሪ ቡድን በተጠርጣሪዎች 60 የክስ መዝገቦች መቋረጣቸውን አስታወቀ

$
0
0

- የ14 ቀናት ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ተፈቀደለት     – ሁለት ተጠርጣሪዎች በምርመራ ወቅት መደብደባቸውን ተናገሩ‹‹ተያዘ የተባለው ሰነድ ሁሉ በሀብት ምዝገባ ያስመዘገብኩት ነው›› አቶ ገብረ ዋህድ ወልደ ጊዮርጊስየፌዴራል የሥነ ምግባርና የፀረ ሙስና ኮሚሽን ምርመራ ቡድን…..፣ በተለያዩ የሙስና ወንጀሎች ተጠርጥረው በቁጥጥር ሥር በዋሉ ተጠርጣሪዎች እንዲቋረጡ ከተደረጉት 60 የክስ መዝገቦች ውስጥ 28 ያህሉን መሰብሰቡን ግንቦት 19 ቀን 2005 ዓ.ም. ለፍርድ ቤት አስታወቀ፡፡

a9ed2de4dd18d7819ad682d04e71a5e6_L

መርማሪ ቡድኑ በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ሁለተኛ ወንጀል ችሎት ቀርቦ እንዳስረዳው፣ በተጠርጣሪዎቹ ላይ ባለፉት 14 ተጨማሪ የምርመራ ቀናት ላይ የሠራውን የምርመራ ሥራ እንዳብራራው፣ ከገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን ሥራዎች ጋር ግንኙነት ያላቸውን የኤሌክትሮኒክስ መሣሪያዎችን ሰብስቧል፡፡ ከተለያዩ ባንኮች በተወሰኑ ተጠርጣሪዎች ላይ ከአራጣ ብድር ጋር የተያያዙ ማስረጃዎችን፣ በሕገወጥ መንገድ የተገኘን ገንዘብ ሕጋዊ አስመስሎ (መኒ ላውንድሪንግ) መጠቀምን የሚያሳዩ ሰነዶችን መሰብሰቡን ገልጿል፡፡

መርማሪ ቡድኑ ጨምሮ እንደገለጸው፣ ተጠርጣሪዎቹ በአራጣ ብድር የተከሰሱ ሰዎችን ክስ ያቋረጡባቸውን የክርክር መዝገቦችን መሰብሰቡንና በኮንትሮባንዲስቶች ላይ በፍርድ ቤት ተጀምረው ከነበሩትና በሕገወጥ ጥቅም ከተቋረጡት 60 የክስ መዝገቦች ውስጥ 28 የሚሆኑት መሰብሰቡንም ገልጿል፡፡

በአንድ የንግድ ድርጅት ላይ ተወስኖ የነበረን ዘጠኝ ሚሊዮን ብር ግብር ወደ ሦስት ሚሊዮን ብር የተቀነሰበትን ሰነድ፣ እንዲሁም 87 ሚሊዮን ብር ግብር እንዲከፍል ተወስኖበት የነበረን ድርጅት፣ በሕገወጥ መንገድ ወደ ስምንት ሚሊዮን ብር ዝቅ የተደረገበትን ሰነድም መሰብሰቡን ቡድኑ ለችሎቱ ተናግሯል፡፡

ዋና ኦዲተር መሥሪያ ቤት ኦዲት ሊያደርጋቸው የሚገቡ ስምንት ኩባንያዎች መኖራቸውን ማረጋገጡን የገለጸው መርማሪ ቡድኑ፣ ኦዲት የሚደረጉትን ለይቶ መጨረሱንና ለመሥሪያ ቤቱ ደብዳቤ መጻፉን አሳውቋል፡፡ መርማሪ ቡድኑ የምስክሮችን ቃል በከፊል መቀበሉንና የንብረት ጥናትም በከፊል መሥራቱን ገልጾ፣ የቀሩትንም የምርመራ ሥራዎች ጠቁሟል፡፡

ያላግባብ ክሳቸው የተቋረጡ 40 የክስ መዝገቦችን መሰብሰብ፣ በሕገወጥ መንገድ ግብር እንዲቀነስ የተደረገባቸውን ሰነዶች፣ ሕጋዊ በማስመሰል ሕገወጥ ገንዘብን ለመጠቀም የተዘጋጁ ሰነዶችን መሰብሰብ፣ የስምንት ኩባንያዎችን ግብር ማጣራት፣ የኦዲተሮችን ቃልና የቀሪ ምስክሮችን ቃል መቀበል እንደሚቀረው በመግለጽ፣ ተጨማሪ የ14 ቀናት የምርመራ ጊዜ እንዲፈቀድለት ፍርድ ቤቱን ጠይቋል፡፡

መርማሪ ቡድኑ ላለፉት 14 ቀናት በተጠርጣሪዎቹ ላይ የሠራቸውንና የሚቀሩትን ሥራዎች ለችሎቱ ካሳወቀ በኋላ፣ በጠየቀው ተጨማሪ የ14 ቀናት የምርመራ ጊዜን በሚመለከት አስተያየታቸውን እንዲሰጡ በችሎቱ የተፈቀደላቸው፣ በኢትዮጵያ የገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተርና የሕግ ማስከበር ኃላፊ የምርመራ መዝገብ ሥር ያሉ 12 ተጠርጣሪዎች ናቸው፡፡

መርማሪ ቡድኑ በጥቅል ከመግለጽ ባለፈ እያንዳንዱ ተጠርጣሪ ምን እንደሠራ፣ ተጠርጣሪው ከሠራው ወይም ካጠፋው ነገር አንድም እንኳን እንዳልተነገረው፣ ምን ሠርቶ ምን እንደቀረው እስካሁን የሚያውቁት ነገር እንደሌለ ለፍርድ ቤቱ ያስረዱት፣ የአቶ ነጋ ገብረ እግዚአብሔር ጠበቃ ናቸው፡፡ ደንበኛቸው ተጠርጥረው የታሰሩት ክስ በማቋረጥና ባልተፈቀደ የፍራንኮቫሉታ ፈቃድ ሲሚንቶ ማስገባት እንደነበር ያስታወሱት ጠበቃው፣ መርማሪ ቡድኑ 14 ቀናት የምርመራ ተጨማሪ ጊዜ ሲጠይቅ ያልተናገራቸውና ለደንበኛቸው ያልተገለጹላቸው ሰነዶችን ማሸሽ፣ ንብረት ከተገቢው በላይ ማፍራትና ከባለሥልጣናት ጋር መመሳጠር፣ ሕገወጥ ገንዘብን ሕጋዊ አስመስሎ መጠቀም፣ አራጣ ማበደርና ግብር ያላግባብ መቀነስ የሚሉት የሕገ መንግሥቱን ድንጋጌ የሚጥስና ያላግባብ መሆኑን ለፍርድ ቤቱ አስረድተዋል፡፡

በሕገ መንግሥቱ ድንጋጌ መሠረት ስለተጠረጠሩበት ወንጀል በተያዙበት ወቅት ሊነገራቸው ይገባ እንደነበር የገለጹት ጠበቃው፣ በቁጥጥር ሥር ከዋሉ በኋላ መርማሪ ቡድኑ የ14 ቀናት ተጨማሪ ጊዜ ሲጠይቅ ያስመዘገባቸው፣ ‹‹የሲሚንቶው ጉዳይ ምን ሆነ? ሰነድ ጠፋ ወይስ ምን ሆነ? ሊገለጽልን ይገባል፤›› ካሉ በኋላ፣ በወቅቱ ያልተገለጹና እንደ አዲስ ክስ የቀረቡት ጉዳዮች ተገቢ ጥያቄዎች ባለመሆናቸው የ14 ቀናት ተጨማሪው የጊዜ ጥያቄው ውድቅ እንዲደረግላቸው ጠይቀዋል፡፡

አቶ ገብረ እግዚአብሔር እንዲናገሩ ችሎቱን ጠይቀው ሲፈቀድላቸው እንደተናገሩት፣ በምን ተጠርጥረው እንደታሰሩ አያውቁም፡፡ ለምርመራ ሲቀርቡ በተደጋጋሚ የሚቀርብላቸው ጥያቄ ስለንብረታቸው ነው፡፡ የልብ ሕመምተኛ መሆናቸውንና ንብረታቸውም የተመዘገበ መሆኑን በመግለጽ፣ ማወቅ የሚፈልገው አካል በፈለገ ጊዜ ሊያውቅ እንደሚችል ገልጸው፣ እሳቸው ግን በአንድ በተዘጋ ክፍል ውስጥ መሆናቸው አግባብ አለመሆኑን ተናግረዋል፡፡

እምባና ሳግ እየተናነቃቸው ዝቅ ባለ ድምፅ መናገር የቀጠሉት አቶ ነጋ፣ በታሰሩበት ክፍል ውስጥ ሁለት ጊዜ ራሳቸውን ስተው ወድቀው እንደነበርና መደብደባቸውንም ገልጸዋል፡፡

ነጋዴ በመሆናቸው ሀብት ማፍራት እንደሚችሉ የተናገሩት ተጠርጣሪው፣ ምርጥ ታክስ ከፋይ ከሚባሉት ውስጥ አንዱ መሆናቸውን፣ ለአገራቸው 33 ሚሊዮን ብር መድበው በ23 ሚሊዮን ብር ያስገነቧቸውን ፖሊ ቴክኒክ ትምህርት ቤቶችን ለሕዝብና ለመንግሥት ማስረከባቸውን ለችሎቱ አስረድተዋል፡፡

‹‹አገሬን ያወቅኋት አሁን ነው፤ ዜጋ ነኝ ለማለት አይቻልም፤›› ያሉት አቶ ነጋ፣ ሲደበደቡ ራሳቸውን ስተው እንደሚወድቁ አስታውቀው፣ ኢሰብዓዊ ድርጊት እንደተፈጸመባቸው ጠቁመዋል፡፡ የደም ግፊትና የስኳር ሕመምተኛ መሆናቸውንና የልብ ቱቦ ተገጥሞላቸው ያሉ ታማሚ በመሆናቸው ክትትል ካልተደረገላቸው ለሕይወታቸው አስጊ መሆኑን ጠበቃቸው አክለዋል፡፡

የመርማሪ ቡድኑን በጥቅል የመግለጽ ሁኔታ እንደ አቶ ነጋ እሳቸውም እንደሚቃወሙት የተናገሩት የባለሥልጣኑ ሠራተኛ አቶ ጥሩነህ በርታ ሲሆኑ፣ መርማሪዎች ወደ ምርመራ ክፍል በመውሰድ የሚጠይቋቸው ከሥራቸው ጋር የማይገናኝ፣ መረጃ እንደሚያውቁ ተደጋጋሚ ጥያቄ እንደሚቀርብላቸውና በማያውቁት ጉዳይ ላይ መረጃ ሰብስበው ክስ ለመፍጠር መሆኑን ተናግረዋል፡፡ እሳቸው ተጠርጥረዋል በተባሉበት ክስ የማቋረጥ ወንጀል መጠየቅ ያለባቸው እሳቸው ሳይሆኑ ከእሳቸው በላይ ያሉ ኃላፊዎች እንደሆኑ የተናገሩት ተጠርጣሪው፣ እነሱ ሳይጠረጠሩ እሳቸውን አስሮ ማሰቃየት ኢሰብዓዊ ድርጊት መሆኑንም ገልጸዋል፡፡

ሱሪያቸውን ከፍ በማድረግ እግራቸውን ለችሎቱ እያሳዩ መደብደባቸውን የገለጹት ተጠርጣሪው፣ ውኃ እየተደፋባቸው እንደተገረፉ ለበላይ ኃላፊ ቢያመለክቱም፣ መርማሪዎቹ በድጋሚ ሲያገኟቸው ‹‹እንኳን ለኃላፊ ለማንም ብትናገር አንተውህም›› እንዳሏቸው ሲገልጹ መርማሪ ቡድኑ አቤቱታቸውን ተቃውሟል፡፡ የተቃወመበትን ምክንያት እንዲያስረዳ ፍር ቤቱ ሲፈቅድለት፣ ተጠርጠሪው የሚያነሱት ጉዳይ አስተዳደራዊ መሆኑን በመጠቆም፣ ፍርድ ቤት ሊቀርብ እንደማይገባ አመልክቷል፡፡ ፍርድ ቤቱ በሰጠው ምላሽ፣ ‹‹አስተያየታቸው ሊደመጥ ይገባል፡፡ ኮሚሽኑ ከሰብዓዊ መብቶች ጋር በተያያዘ የሚነሱ አቤቱታዎችን እንዲያስተካክል በተደጋጋሚ ቢታዘዝም ሊታረም አልቻለም፤›› በማለት ተጠርጣሪው አቤቱታቸውን እንዲቀጥሉ አዟል፡፡

ተጠርጣሪው ቃላቸውን እስካሁን የተቀበላቸው እንደሌለ በመግለጽ፣ ቢሮአቸውንም ሆነ ቤታቸውን ቡድኑ በርብሮ ምንም አለማግኘቱን፣ እያንገላታቸው ያለው አዲስ ማስረጃ ለማሰባሰብ እንጂ በእሳቸው ላይ ምንም ዓይነት ጭብጥ እንደሌለው ፍርድ ቤቱ እንዲገነዘብላቸው አመልክተዋል፡፡

የባለሥልጣኑ ኦዲተር መሆናቸውንና ደመወዛቸው ከአሥር ሺሕ ብር በላይ መሆኑን፣ የተጣራ 5,600 ብር አካባቢ እንደሚያገኙና ሥራ የሌላቸውን ባለቤታቸውን ጨምሮ፣ ልጆቻቸውንና የእህታቸውን ልጅ ጭምር የሚያስተዳድሩት እሳቸው መሆኑን የተናገሩት አቶ በላቸው በየነ ሲሆኑ፣ መርማሪ ቡድኑ የልጃቸው ላፕቶፕ ጨምሮ በመሥሪያ ቤታቸውና በቤታቸው ያለውን ሁሉንም ሰነድ ስለወሰደ በዋስ እንዲለቃቸው ጠይቀዋል፡፡

የኮሚሽኑ መርማሪ ቡድን በጥቅሉ ሳይሆን እያንዳንዱ ተጠርጣሪ የተጠረጠረበትን ወንጀል ለይቶ ማቅረብ እንደሚገባው የገለጹት ተጠርጣሪው፣ መንግሥት በመደባቸው በተለያዩ ኃላፊነቶች ላይ ለ27 ዓመታት መሥራታቸውን፣ አብዛኛው ሥራዎቻቸውን የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ መለስ ዜናዊ ጭምር ያውቁት እንደነበር፣ ቤተሰብንም ሆነ ሌላ አካል ወይም ማንንም ለመጥቀም በሚል ሕገወጥ ሥራ ሠርተው እንደማያውቁ አስረድተዋል፡፡

በቅርቡ ለዋና ኦዲተር መሥሪያ ቤት ኃላፊዎች ሥልጠና ለመስጠት እሳቸውና ሌላ አንድ ሰው ተመርጠው እንደነበር የተናገሩት ተጠርጣሪው፣ መርማሪ ቡድኑ ኩባንያዎችን ኦዲት እንዲያደርጉለት ለዋና ኦዲተሩ ደብዳቤ መጻፉን አስታውሰው፣ ‹‹ኦዲት የሚያደርጉት ሠልጥነው ነው ወይስ?›› ሲሉ ፍርድ ቤቱ ‹‹ይኼ በማስረጃ ጊዜ የሚታይ ነው፤›› በማለት አስቁሟቸዋል፡፡

አቶ ገብረ ዋህድ ወልደጊዮርጊስ ሁለት ሕፃናት ልጆቻቸው እስካሁን ድረስ የት እንዳሉ እንደማያውቁ፣ የሚረዳቸው ወይም የሚቀልባቸው ሰው ባለመኖሩ ሥጋት ላይ መሆናቸውን ለፍርድ ቤቱ በማስረዳት፣ ባለቤታቸው ኮሎኔል ሃይማኖት ተስፋይና እህታቸው ወ/ሮ ንግስቲ ተስፋይ፣ እንዲሁም በውጭ አገር ለሰባት ዓመታት ቆይቶ ከመጣ አራት ወራት ብቻ የሆነው የወ/ሮ ንግስቲ ልጅ አቶ ሀብቶም ገብረመድኅን በዋስ እንዲፈቱ ጠይቀዋል፡፡

እሳቸው የተጠረጠሩበትን የወንጀል ሰነድ አሽሽተዋል በሚል ቤተሰቦቻቸው መታሰራቸው አግባብ አለመሆኑን የገለጹት አቶ ገብረ ዋህድ፣ ሸሽቷል የተባለው ሰነድ ኮሚሽኑ ባወጣው የሀብት ማስመዝገብ አዋጅ የተመዘገበና ኮሚሽኑ የሚያውቀው መሆኑን አስረድተዋል፡፡ የባለቤታቸው እህት የ60 ዓመታት አዛውንት መሆናቸውን፣ ከአቅም በላይ በሆነ ውፍረት ክብደታቸው ከፍተኛ በመሆኑ ዕርዳታ እንደሚፈልጉና የደም ብዛትና የስኳር ሕመምተኛም ስለሆኑ ከተቻለ በነፃ ካልሆነም በዋስ አንዲለቀቁ ፍርድ ቤቱን ጠይቀዋል፡፡

ኮሚሽኑ የቀረው መደበኛ ሥራው መሆኑን የገለጹት አቶ ገብረ ዋህድ፣ ከእሳቸውና ከቤተሰባቸው ጋር የሚያገናኘው ነገር ስለሌለ በዋስ እንዲለቀቁ ወይም የምርመራ ጊዜው አንዲያጥር አመልክተዋል፡፡

የአቶ ስዬ አብርሃ ወንድም አቶ ምሕረተ አብ አብርሃ ባቀረቡት አቤቱታ እንደገለጹት፣ የሚተዳደሩት በንግድ ነው፡፡ ከ1993 ዓ.ም. እስከ 1999 ዓ.ም. ድረስ በታሰሩበት ወቅት ንብረታቸውን ያስተዳድር የነበረው ኮሜት የሚባል ድርጅት ነበር፡፡ ንብረታቸውን በሚመለከት ከገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን ጋር አለመግባባት ላይ ደርሰው፣ መብታቸውን ያስከበሩት በፍርድ ቤት ነው፡፡ በመሆኑም አሁን ‹‹ተጠርጥረሃል›› ከተባሉበት ክስ ማቋረጥ፣ ኮንትሮባንድ፣ አራጣና ሌሎች ጉዳዮች ጋር እንደማይገናኙ ተናግረዋል፡፡ ከነበሯቸው ከ15 በላይ ተሽከርካሪዎች ልጆቻቸውን እያስተዳደሩ ያሉት በሁለት ተሽከርካሪዎች በሚያገኙት ገቢ ብቻ መሆኑን የገለጹት አቶ ምህረተ አብ፣ ባለሥልጣኑ ከፍተኛ ግብር ጭኖባቸው ከ1999 ዓ.ም. እስከ 2003 ዓ.ም. ድረስ በፍርድ ቤት ባደረጉት ክርክር መብታቸውን ማስከበራቸውን ገልጸው፣ አሁን የተጠረጠሩበትን ምክንያት ስለማያውቁት ዋስትና እንዲከበርላቸው ጠይቀዋል፡፡

ሁሉም ተጠርጣሪዎች በአጠቃላይ መርማሪ ቡድኑ ያቀረበው የምርመራ ውጤት ወንጀሉ ጥቅል መሆኑን፣ በተያዙበት ወቅት ያልተነገራቸው የወንጀል ክስተት እየቀረበባቸው መሆኑን፣ ማስረጃ ተሰብስቦ ቢያልቅም መብታቸው አለመከበሩን፣ ጥርጣሬዎቹ ከሰነድ ጋር የተገናኙ በመሆናቸው ታስረው ሊቆዩ እንደማይገባና ዋስትና ሊፈቀድላቸው እንደሚገባ፣ ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ እንደማያስፈልግ የሚሉትን ሐሳቦች ሁሉም ያነሱ ሲሆን፣ በተናጠል ደግሞ የቤተሰብ ኃላፊ መሆናቸውን፣ የጤና ችግር እንዳለባቸው፣ የመብት ጥሰት እየተፈጸመባቸው መሆኑን፣ ከተያዙ ጀምሮ ቃላቸውን አለመስጠታቸውን ለፍርድ ቤቱ አመልክተዋል፡፡ በምርመራ መዝገቡ የቀረቡት 12 ተጠርጣሪዎች ናቸው፡፡

የኮሚሽኑ መርማሪ ቡድን ተጠርጣሪዎቹ ላነሷቸው ጥያቄዎች በሰጠው ምላሽ፣ የተጠረጠሩበት ወንጀል የተፈጸመው በተናጠል ሳይሆን በቡድንና ውስብስብ በሆነ መንገድ መሆኑን ገልጿል፡፡ ጉዳዩ አገራዊ በመሆኑ በቀላሉ የሚታይ አለመሆኑንም አስገንዝቧል፡፡ ተጠርጣሪዎቹ ከፍተኛ ኃላፊዎችና ባለሀብቶች መሆናቸውን በመጠቆም፣ ሥልጣንንና ገንዘብን ተገን በማድረግ ውስብስብ በሆነና በጥቅም በመመሳጠር በአገር ገቢ ላይና በሌሎች የሕዝብ ጥቅሞች ላይ የተፈጸመ ወንጀል መሆኑን አስረድቷል፡፡ ክስ እንዲቋረጥና ከውጭ የሚገቡ የንግድ ዕቃዎች ቀረጥ እንዳይከፈልባቸው ሲደረግ፣ ለጠቋሚዎች የሚከፈል አበል ለራስ ጥቅም ሲደረግ፣ አንድ ተጠርጣሪ ብቻ የሚሠራው ሳይሆን በቡድንና በመመሳጠር የሚሠራ መሆኑን መርማሪ ቡድኑ ለችሎቱ አስረድቷል፡፡ ድርጊቱ በአጠቃላይ በትብብር የተሠራ መሆኑንና ለቀሪ የምርመራ ጊዜ ተጨማሪ 14 ቀናት ጊዜ እንዲፈቀድለት በድጋሚ አመልክቷል፡፡

ቃል አልሰጠንም ያሉት ተጠርጣሪዎች ቃላቸውን መስጠታቸውን በተለያየ መንገድ መግለጻቸውን፣ ሰብዓዊ የመብት ረገጣ ደርሶብናል ያሉት ተጠርጣሪዎችም በማስረጃ የቀረበ ባለመሆኑ ሊታመን እንደማይችል መርማሪ ቡድኑ ገልጾ፣ ዋስትና ቢፈቀድ የሰነድና የምስክሮች ቃል ሊያጠፉበት እንደሚችሉ በመናገር ዋስትናውን ተቃውሟል፡፡

መርማሪ ቡድኑ በተሰጠው ጊዜ በማን ላይ ምን እንደተሠራ፣ በማን ላይ ምን እንደቀረው በግልጽ አለማስቀመጡን፣ ይኼም ለክርክር በር መክፈቱን፣ በርካታ ምስክሮች የቀሩት በማን ላይ እንደሆነና ሰነድም ሆነ ሌላ መረጃ ለማጣራት የተፈለገው በማን ላይ እንደሆነ ግልጽ አለመደረጉ አግባብ አለመሆኑን ፍርድ ቤቱ ገልጾ፣ በቀጣይ ቀጠሮ በእያንዳንዱ ተጠርጣሪ ላይ በተናጠል የተሠራው ተዘርዝሮ እንዲቀርብ አዟል፡፡

በመጨረሻም ፍርድ ቤቱ በሰጠው ትዕዛዝ ከድርጊቱ ውስብስብነት አንፃር የተጠርጣሪዎች ዋስትና ጥያቄን አለመቀበሉን፣ የመርማሪ ቡድኑን 14 ቀናት ተጨማሪ ጊዜያት መፍቀዱን አስታውቆ፣ በሰብዓዊ መብት ጥሰት ዙሪያ ተጠርጣሪዎች ያቀረቡትን አቤቱታ ኮሚሽኑ አጣርቶ እንዲያቀርብ በማዘዝ ለሰኔ 3 ቀን 2005 ዓ.ም. ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡

በዕለቱ መቅረብ የነበረበት የእነ አቶ መላኩ ፈንታ የምርመራ መዝገብና የእነ አቶ መሐመድ ኢሳ የምርመራ መዝገብ በመሆኑ፣ መዝገቡ የቀረበ ቢሆንም ቀኑ በመምሸቱ ለግንቦት 21 ቀን 2005 ዓ.ም. በይደር ተቀጥሯል፡፡ በእነ መሐመድ ኢሳ የምርመራ መዝገብ ፍሬሕይወት ጌታቸው የተባሉ ተጠርጣሪ በመካተታቸው ጠቅላላ የተጠርጣሪዎች ቁጥር 55 ደርሷል፡፡

ግንቦት 19 ቀን 2005 ዓ.ም. የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን ሹማምንት፣ ታዋቂ ነጋዴዎችና ሌሎች ተጠርጣሪዎችን ችሎት ለመታደም በፍርድ ቤት የተገኙ ታዳሚዎች ከችሎቱ አቅም በላይ ስለነበሩ በርካቶች ችሎቱን መከታተል አልቻሉም፡፡


የአፍሪካ ሕብረት፡ ለነጻነት ወይስ ለባርነት?

$
0
0

የአፍሪካ ሕብረት ታሪክ የሚነገረው ለጭቁን ጥቁር ሕዝቦች ሰብአዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ሉዓላዊነት መከበር፤ ጭቁኖቹ ሕዝቦች እርስ በርስ በመተባበር ነጻነታቸውን በማግኘት የአፍሪካ ሕዝቦች በጋራ… “ነጮች” ሲበዘብዙት የኖረውን የክፍለ ዓለሚቱን የተፈጥሮ ሃብት ባለቤቶቹ ተገቢውን ጥቅም እንዲያገኙ፤ ወዘተ. ጥቁሮች የፈጠሩት ሕብረት በማለት ነው፡፡  የተጨቆኑ ቢተባበሩ ተገቢ ነው፣ በዚህ እየተወሳሰበ እየመጣ ባለ ዓለም በጠረጴዛ ዙርያ እየተመካከሩ እርስ በእርስ እንቅፋት መሆንን በማስወገድ በጋራ ርእይ ለጋራ ጥቅም፣ የግል ጥቅምንና ሉዓላዊነትን ለማስከበር አብሮ መቆም ተገቢ ነው፡፡ ከማሕል አንድ ወንድም-ሐገር አደጋ ውስጥ ሲገባ በጋራ ተመካክሮ መርዳትና መከራውን ማሳለፍ ተገቢ ነው፡፡ ከዚህም በላይ ደግሞ ከነጮች የቅኝ አገዛዝ ለመውጣት የተከፈለው መስዋእትነት መና እንዳይቀርና አሁንም የቀሩ በደሎች እንዲወገዱ፣ ሁሉም ቅኝ ተገዢ የነበሩት ቢተባበሩ አይከፋም፡፡

ሆኖም ግን እየሆነ ያለው የዚህ ተገላቢጦሽ ነው፡፡ እየተሮጠ ያለው ጥያቄ እንደሌለው ጥሩ ነገር ተደርጎ አፍሪካን አንድ አድርጎ የሚያስተዳድር አንድ መንግስት ለመመስረት ነው፡፡ ኒሮ የተባለው እብድ የሮም ንጉስ የሮም ሕዝብ አንድ አንገት ብቻ በኖረውና በቀላሁት ነበር በሚል አባባሉ ይታወቃል፡፡ ሃገሮች ሉዓላዊነታቸውን አሳልፈው ክፍለ ዓለሚቱን ለሚያስተዳድር ቢሮክራሲ ሲያስረክቡ ሕዝቦቹ ከሚጠቀሙት ይልቅ የሚያጡት ይበዛል፡፡ እርስ በእርስ ወደ ጦርነት ላለመግባት በኢኮኖሚያዊ ጥቅም መተሳሰር እና ጠቅልሎ ሉዓላዊነትን አሳልፎ መስጠት ለየቅል ናቸው፡፡

አንድ አፍሪካ?

ፖለቲካዊ ውሕደት ያላት አፍሪካን ለመገንባት “አብዮተኛ” ልጆቿን ቀድመው የጀመሩት በ19ኛው ክ/ዘመን ጠቅልለው ቅኝ ሊገዙ የመጡት ወራሪዎች ነበሩ፡፡ የአፍሪካ ቅርምት እየተባለ በሚታወቀው ወረራቸው ብሪታንያ፣ ፈረንሳይ፣ ስፔን፣ ፖርቱጋል፣ ቤልጄም እና በኋላ ላይ ደግሞ ጣልያን እና ጀርመን አቅማቸው የፈቀደውን ያህል ተቆጣጥረው፣ አንዳቸው የሌላቸው አንድ የማድረግ ሕልም እንቅፋት ሁነዋል፡፡ ስለዚህም በግዜው አፍሪካን አንድ አድርጎ የመግዛት ሕልማቸው በእርስ በእርስ ፍክክራቸው ሳብያ ሳይሳካላቸው ቀርቷል፡፡
አብዮተኞቹ ልጆቿ በ20ኛው ክ/ዘመን አንድ እናደርጋታለን ብለው ሲነሱ ፓን አፍሪካዊነት የሚባል ርዕዮት አነግበው ነበር፡፡ ይህ ርእዮት መላ አፍሪካውያን ትስስራቸውን እንዲያጠናክሩ የሚጠራ ሲሆን ለኢኮኖሚያዊ፣ ማሕበራዊ እና ፖለቲካዊ ሽግግር አንድነት አስፈላጊ ነው በሚል እምነት ላይ ተመስርቶ አፍሪካውያንን ለማዋሃድ የሚሰራ ነው፡፡ ርእዮቱ አፍሪካውያን አንድ አይነት ታሪክ ብቻ ሳይሆን እጣቸውም የተሳሰረ ነው ይላል፡፡ በዚህም መሰረት አፍሪካውያን ከቅኝ ገዢዎች ነጻ በወጡበት ማግስት ነበር ለመዋሃድ መጣደፍ የጀመሩት፡፡
የመጀመርያው አጠቃላይ ውሕደት ያስፈልጋል በሚሉት በጋናው ኩዋሚ ኑኩርማ እና በጊኒው ሴኩ ቱሬ እ.ኤ.አ. በ1958 ዓ.ም የጋናና ጊኒን ህብረት በመፍጠር ጀመሩት፣ በ1961 ማሊ የታከለችበት ቢሆንም በቀጣዩ አመት ጥምረቱ ሊፈርስ ችሏል፡፡ የሚመራቸው ርእዮተ ዓለም ከፓን አፍሪካዊነት ጋር አስተሳስረው ማርክሲስታዊነት ነበር፡፡ ከዚህ የከሸፈ ሙከራ ቀጥሎ አፍሪካን አንድ ለማድረግ የሚወተውቱት እንዴት መሆን እንዳለበት ሳይስማሙ ቀርቶ በሁለት ቡድን ተከፍለው ነበር፡- ፓን አፍሪካዊነትን በማቀንቀን የሚታወቁት የጋናው ኩዋሚ ንኩርማ የሚመሩትና አልጀሪያ፣ ጊኒ፣ ሞሮኮ፣ ግብጽ፣ ማሊ እና ሊብያ የሚገኙበት የካዛብላንካ ቡድን እና የሴኔጋሉ ሊዮፖል ሴዳር ሴንግሆር የሚመሩት ናይጄርያ፣ ላይቤርያ እና ኢትዮጵያ የተቀበሉት የሞነሮቭያ ቡድን ነበር፡፡ የካዛብላንካው አጠቃላይ ውህደት እንዲደረግ ሲሉ የሞነሮቭያው ቡድን ደግሞ ፖለቲካዊ ውህደቱን ያልተቀበለው ሲሆን ኢኮኖሚያዊና ሌሎች ጥቅም የሚያስጠብቁ ትብብሮች እናድርግ ብለው ነበር፡፡ የመጀመርያዎቹ ተራማጅ፣ ማርክሲስታውያን ተደርገው የሚቆጠሩ ናቸው፡፡ ሁለተኞቹ ደግሞ ካፒታሊስትና ብሔራውያን ነበሩ፡፡
በኋላ ላይ ቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ፣ አዲስ አበባ ባደረጉላቸው ግብዣ ተገኝተው ልዩነታቸውን ሊፈቱ ችለዋል፡፡ ከዚህም በመከተል የአፍሪካ አንድነት ድርጅትን እ.ኤ.አ. በግንቦት 25፣ 1963 ዓ.ም መስረተዋል፡፡ ሲመሰረት ዓላማው ያደረገው የአፍሪካውያንን ትብብር ማጠናከር፣ ግጭቶችን በሰላማዊ መንገድ መፍታት፣ ነጻነት ማስጠበቅ፣ ዓለም አቀፋዊ መድረኮች ላይ በጋራ መቆም፣ ቅኝ ግዛት ስር ያሉትን የነጻነት ትግላቸውን መርዳት እና በዓለም መድረክ ነጻ ወይም ገለልተኛ መሆን የሚሉ ናቸው፡፡ ይህ የአንዲትን ሃገር ሉዓላዊነት የማይዳፈር ሃሳብ እንደመሆኑ ንጉሱን ጨምሮ 32 መስራቾች ፊርማቸውን አኑረው ተቀብለውታል፡፡

ከአፍሪካ አንድነት ድርጅት ወደ አፍሪካ ሕብረት?

የአፍሪካ አንድነት ድርጅት የቆመለት ዓላማ ያለፈበት ነው በሚል በ1990ዎቹ ድርጅቱ እንዲቀየር የሊብያው የቀድሞ መሪ ጋዳፊ ሲወተውቱ ከቆዩ በኋላ እ.ኤ.አ. በመስከረም 9፣ 1999 ዓ.ም በሲርጥ እወጃ የአፍሪካ ሕብረት እንዲመሰረት ተወሰነ፡፡ እ.ኤ.አ. በግንቦት26፣ 2001 ዓ.ም በአዲስ አበባ ተመስርቶ፣ በሐምሌ 9፣ 2002 ዓ.ም ስራ እንዲጀምር በደርባን፣ ደቡብ አፍሪካ ታወጀ፡፡ በአዲስ መልክ የተቋቋመው የአፍሪካ ሕብረት ስሙን ብቻ ሳይሆን ግቡንም ቀይሮ፣ የፓን አፍሪካዊነት ቅዥትን ጨምሮ ነበር የመጣው፡፡ ተቋሙ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊና ወታደራዊ ውሕደት መፍጠር ግቡን አድርጎ የተመሰረተ ሲሆን ይህን ለማሳካትም በስሩ የተለያዩ ተቋማትን ፈጥሯል፡፡ በኢኮኖሚው የአፍሪካ ሕብረት ግብ ነጻ የንግድ ቀጠና፣ የቀረጥ ማሕበር፣ አንድ ገበያ እና አንድ ማእከላዊ ባንክ መመስረት ነው፡፡ የአፍሪካ ማእከላዊ ባንክ (በአቡጃ፣ ናይጄርያ)፤ የአፍሪካ ኢንቨስትመንት ባንክ (ትሪፖሊ፣ ሊብያ)፤ የአፍሪካ ሞኒታሪ ፈንድ (ያኦንዴ፣ ካሜሮን) የሚሆኑ ፋይናንሳዊ ተቋማት መስራች ኮሚቴ ተቋቁመው በተጠቀሱት ሃገራት ከትመዋል፡፡ የአፍሪካ ሕብረት “አፍሮ”የተባለ አንድ የአፍሪካ የመገበያያ ገንዘብ እ.ኤ.አ. በ2023 ዓ.ም (ከአስር ዓመት በኋላ) የማስጀመር እቅድ አለው፡፡
ለዚህም ነው ዛሬ ላይ አፍሪካዊነትን የሚያወድስ ፕሮፖጋንዳ ያለማቋረጥ የምትሰሙት፡፡ በቻይና ስጦታ የቆመው አዲሱ የአፍሪካ ሕብረት መሰብሰብያ እና ቢሮዎች የያዘው ሕንጻ ሲመረቅ የፓን አፍሪካዊነት አውራ ሰው በሚል የኩዋሜ ንኩርማ ሃውልት ሲቆምለት፣ የቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ ሃውልት ባለመሰራቱ ኢትዮጵያውያን “ልሂቃንን” ያስከፋ ነበር፡፡ ባርነትህን መውደድ ይሉታል እንዲህ ነው፡፡ አፄ ኃይለ ስላሴ ዛሬ ቢኖሩ አሁን ባለው የአፍሪካ ሕብረት እንደማይስማሙ ማንም ማሰብ የሚችል ሰው የሚቀበለው ነው፣ ሃውልታቸው አለመሰራቱም እንደመልካም እንጂ እንደ መዘንጋት መታየት አልነበረበትም፡- በተዓምር መንግስታቸውን አሳልፈው “ለአፍረካዊ መሪ” አይሰጡም ነበርና፣ ቀድሞ የነበረው የአፍሪካ አንድነት ድርጅትንም ሲቀበሉ እንዲህ ያለውን የካዛብላካው ቡድንን ሃሳብ ሽረው ነበር፡፡ የሆነው ሁኖ አፍሪካውያኑ “ልሂቃን”በነጻነት ለዘመናት የኖረችው ሃገርን ለፓን አፍሪካዊነት ርእዮት ፕሮፖጋንዳ አስፍተው ስለሚጠቀሙባት ኢትዮጵያውያኑን ለማባበል የሆነ መፍትሄ ማበጀታቸው አይቀሬ ነው፡፡ (ይህን እውነት የሚያስታውሳችሁ አታገኙም፣ ዓለም አቀፋዊ አለቆቻቸው አይፈቅዱላቸውምና፡፡)
እ.ኤ.አ.በሐምሌ 2007 ዓ.ም በአክራ፣ ጋና በተደረገው ስብሰባ ላይ “የሞቀ ክርክር” ከተደረገበት በኋላ የሕብረቱን መንግስት (እንደ ዩናይትድ ስቴትስ ኦፍ አሜሪካ) ለመመስረት የሚደረገው ጉዞ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ውሕደት በማጠናከር ይበልጥ መሰራት እንዳለበት፣ በአፍሪካ ሕብረትና በቀጠናዊ ኢኮኖሚያዊ ኮሚሽኖች መሃከል ያለው ግንኙነት እንዲጠናከርና የአፍሪካ መንግስት የሚመሰረትበት የጊዜ ገደብ እንዲቀመጥ የሚያዝ ውሳኔ አውጀዋል፡፡
ኢኮኖሚያዊ ውህደት (አንድ ገንዘብ፣ ገበያና ማእከላዊ ባንክ) ለመመስረት መሯሯጡ ቀውስ ውስጥ የገቡትና በመቀላቀላቸው እየተቆጩ ያሉትን የዩሮ ዞን አባሎችን ልምድ አለማስተዋል ነው፣ በምን ስሌት ነው አንድ ህዝብ የራሱን ገንዘብ የማተም መብቱን (“የወርቅ እንቁላል የምትጥል ዳክዬን”) አሳልፎ መስጠቱ የሚጠቅመው? ሥልጣን ይበልጥ ወደታች እየወረደ በመሄድ ፈንታ በክፍለ ዓለም ደረጃ ማዋሃዱ ነጻነታቸውን ለማግኘት የተዋደቁ ሕዝቦችን በምን ስሌት እንደሚወክል አይገባም፡፡
“የአፍሪካ ህብረት ዋና ዘፈኑ ኋላ ቀር አፍሪካውያን ከበዝባዥ ምእራባውያን ነፃ መውጣት ከፈለጉ በህብረት ራሳቸውን ማጠንከር አለባቸው የሚል የተበዳይነት ስሜት በሚፈጥረው ቁጭት ጥቁሮች ለህብረት እንዲፋጠኑ የሚማፀን ነው፡፡ እውነቱ ግን ስልጣንን ወደ ላይ በመስቀል ተጠያቂነታቸው ግልፅ ያልሆነ አህጉራዊ ቢሮክራሲ በመፍጠር ዓለምን ለመግዛት ለሚሹ አፍሪካን አኮላሽቶ ለማስረከብ ያቀደ ይመስላል፡፡ የአፍሪካ ህብረት ከሌሎች ዓለም አቀፋዊ ተቋማት ጋር በጥምረት የሚሰራ ሲሆን የነሱ ተላላኪ እንጂ አንድም የራሱ አቋም ያራመደበት ግዜ የለም፡፡ አሁን ደግሞ የአሜሪካ ሰራዊቶች በአፍሪካ እያደረጉ ካሉት መስፋፋት ጋር በጥምረት እየሰራ ይገኛል፡፡” ስለ አጠቃላይ ዓለም አቀፋዊ አካሄዱየሉላዊ አገዛዝ ደረጃዎች ይመልከቱ፡፡
ዓለምን አንድ አድርጎ ለመግዛት ያለው ቀጥተኛ ላልሆነ ቅኝ አገዛዝን ብቻ ነው ሕብረቱ የሚጠቅመው፡፡ ሲጀመርም አንድ አድርጎ ለመግዛት የሞከሩት ቅኝ ገዢዎች መሆናቸውን እናስታውስ፡፡ በአንድ አፍሪካ ስም ተታለው ወይም ከዓለም አቀፋውያኑ ጋር አብረው ሊሰሩ የሚችሉ መሪዎች ገሚሶቹ ፍሪ ሜሶን ሲሆኑ፣ የቀሩት ደግሞ የተባሉትን ሁሉ የሚፈጽሙ ሊበራሎች ወይም ደግሞ በተቃራኒው ያሉት አለም አቀፋውያን ሶሻሊስቶች ናቸው፡፡ ጎዳናዎችን በአፍሪካ ሃገራት መሰየምና ሉዓላዊነትን አሳልፎ መስጠት ይለያያሉ፡፡
ቀጥለን ለምእራባውያን ኢምፐርያሊዝም ቁልፍ የሆነውን የፍሪሜሶን ማህበር በአፍሪካ ያለውን ሚና ካመጣጡ እስከ ፖለቲከኞች ጋር ያለውን ትስስር በማየት የፓን-አፍሪካዊነት ዲስኩር ባዶነትን እንታዘብበታለን፡፡

ፍሪሜሶን እና አፍሪካውያን

ፍሪሜሶን“… በርግጠኝነት በመቶዎች ዓመታት በሚያከራክር ሁኔታ ደሞ በሺህ አመታት የሚቆጠር እድሜ ያለው የሚስጥር ማህበር ነው፡፡ ፍሪሜሶናዊነት እራሱን እንደ በጎ አድራጎት ድርጅት አድርጎ ያቀርባል፡፡ ይህ እውነት የሚመስለው ከሚመለምላቸው ሰዎች 97 መቶኛ የሚሆኑት “ሰመያዊ መዓርግ” ከሚባሉት ከመጀመርያዎቹ ሶስት መዓርጎች ስር የሚገኙት ገራገሮች ባላቸው ግብረገብና ከማህበረሰቡ የተሻሉ ግለሰቦች ቀናነት የሚታይ በመሆኑ እውነት ሊያስመስለው ይችላል፡፡ እውነቱ ግን ከፍ ያሉት መዓርጎች በፍሪሜሶን መክብብ ውስጥ ኮር (ማህል) ቦታውን የያዙ ጥቂቶች ለዓለም አቀፋዊ የበላይነት ግባቸው በመሳርያነት ነው የሚያውሉት፡፡” ማለት ይቻላል፡፡ ይበልጥ ለማግኘት ፍሪሜሶኖች — FREEMASONS ማንበብ ይችላሉ፡፡
ፍሪሜሶን ማህበር ሚስጥራቱን ከመካከለኛው ምስራቅ ገዳዮቹ ወይም ሀሻሺን ከሚባሉት ጋር ግንኙነት በፈጠሩት ቴምፕላሮቹ አድርጎ በመጣው ባእድ ሚስጥር (ሰይጣን አምልኮ) ጋር የተቀላቀለ እምነት ማህበር እንደመሆኑ፣ የመካከለኛው ምስራቅ ቁንጮ ግብጽ ደግሞ ከአፍሪካ በቀዳሚነት መሰል የሚስጥር ማህበር በማንሳቀስ ትጠቀሳለች፡፡ እ.ኤ.አ. በ1004 ዓ.ም ዳር ኡል ሂክማት ወይም የእውቀት ቤት በስድስተኛው ከሊፋ ሀኪም ሲመሰረት ማለት ነው፡፡[1] ቀጥሎ ደግሞ ሞሮኮን እናገኛለን፡ ሞሮኮ በሱፊ ሚስጥራት አማካኝነት እራሳቸውን ከፍሪሜሶኖች ጋር አንድ እንደሆኑ አድርገው ያያሉ፡፡ የአሜሪካ መስራች አባቶች አብዛኞቹ ፍሪሜሶን መሆናቸው ይታወቃል (አገር፣ መንግስት፣ ሃይማኖት የማይቀበለው አብዮተኛው ኢሉሚናቲ አካል ግን አይደሉም)፡፡ ጆርጅ ዋሽንግተን እንኳ ኢሉሚናቲን የሚያወግዝ ደብዳቤ ጽፏል፡፡[2] እናም አሜሪካ ነጻነቷን ስታውጅ በቅድሚያ እውቅና የሰጠቻት እ.ኤ.አ. በ1777 ሞሮኮ ነበረች፡፡ ለመጀመርያው ፕሬዚደንቷም ጆርጅ ዋሽንግተንም የሞሮኮ ባንዲራ ተለግሶለታል፡፡ የሞሮኮ ባንዲራ በቀይ መደብ ላይ ባለ አምስት ጫፍ የተጠላለፈ አረንጓዴ ኮከብ ያለው ሲሆን ኮከቡን ሞሮኮዎች የሱሌይማን ማሕተም ይሉታል፡፡[3] በሰሜን አፍሪካ ዘመናዊው ፍሪሜሶን የተስፋፋው ከፈረንሳይ አብዮትና ከናፖሊዮን ጦርነቶች ጋር ተያይዞ ነበር፡፡ ያንግ ተርክ የተባሉት የቱርክ አብዮተኞች ፍሪሜሶንን ወደ ሶርያና ግብጽ ወዳሉት ብሔራውያንና አብዮተኞች እንዲተዋወቁ አድርገዋል፡፡ በግብጽ ፍሪሜሶን የፈረንሳይ እና ብሪታንያ ሽኩቻ መሳርያ ሁኖ ነበር፡፡ መጀመርያ ወደ ግብጽ የመጡት እ.ኤ.አ. በ1798 በናፖሊዮን ሰራዊት ነበር፡፡ ኢሲስ ሎጅ የተባለውን ቅርጫፍ ሲመሰርት ናፖሊዮን ሙስሊም እምነትን እንደማይነካ በራሪ ወረቀት በትኖ ነበር፡፡ ኢሲስ ሎጅ 95 መዓርጎች ያሉት ስርዓት ይከተል ነበር፣ በእያንዳዱ መዓርግ እድገት አባሉ ቃለ መሃላ እየፈጸመ ይሸጋገራል፡፡[4]
እ.ኤ.አ. በ1830 ደግሞ ጣልያን በአሌክሳንድርያ፣ ግብጽ የካርቦናሪ ሎጅ ከፍታ ነበር፡፡ ይሄኛውም ሎጅ እንደላይኛው በውዝግብ የተሞላ ሲሆን በተለይ ፖለቲካዊ ሁኖ በመገኘቱ መንግስት ይከታተለው ነበር፡፡ ሌላም ባለ95 መዓርግ (መምፊስ ራይት) ስርዓት የሚከተል ሜኔስ ሎጅ የተባለም ተመስርቶ ነበር፡፡[5] ሌሎችም የመምፊስ ራይት የሚከተሉ ሳሙኤል ሆኒስ በተባለ ሰው የፈረንሳይ ሎጆች በአሌክሳንድሪያ፣ ኢስማኢልያ፣ በሰይድ ወደብ፣ ስዊዝ እና ካይሮ በተጨማሪም እ.ኤ.አ. በ1845 አል አሕራምን በአሌክሳድርያ መስርቷል፡፡ ይህ በግብጽ ገዢዎች እውቅናን ሊያገኝ የቻለ ሲሆን ብዙ የመንግስት ባለስልጣናትም አባል ሊሆኑ ችለዋል፡፡ ከነዚህም ዝነኛው ኢሚር አብደል-ጋዛኢሪ፣ ፈረንሳዮችን አልጀርያ የተዋጋውና ሶርያ በግዞት እያለ ክርስትያኖች በዳማስከስ ጭፍጨፋ ሲደርስባቸው መቶዎችን በመሸሸግ ያዳነው ይገኝበታል፡፡ ሌላው የመምፊስ ራይት ተከታይ ዝነኛው ሰው ሳልቫቶሬ ዞላ ነው፣ እ.ኤ.አ. በ1849 በስኮቲሽ ራይት ስርአት የሚከተል የጣልያን ሎጅ በአሌክሳድርያ መስርቷል፡፡[6] እ.ኤ.አ.በ1866 እውቅና አግኝተው የግብጽ የተለያዩ ሎጆች በአንድ ማህበር ሆኑ፣ ከፍተኛ መዓርጎቹ በግብጽ ግራንድ ኦርየንት እንዲሰጡና የመጀመርያዎቹ ሦስት መዓርጎች ደግሞ በግብጽ ናሽናል ግራንድ ሎጅ እንዲሰጡ ተደረገ፡፡
ከዲቭ ኢስማኤል የተሰኘው የግብጽ ንጉስ፣ በኢትዮጵያ በአፄ ዮሐንስ 4ኛ ዘመነ ንግስና መላ የናይል ተፋሰስንና የቀይ ባህርን ለመቆጣጠር በማሰብ ወረራ ፈጽሞ ክፉኛ የከሸፈበት ሲሆን በሃገሩ የሜሶኖች የበላይ ጠባቂ ነበር፣ ልጁ ተውፊቅም አባል እንዲሆን አድርጓል፡፡ እ.ኤ.አ. በ1881 ልጁና የመንበረ ሥልጣኑ ተኪ የሆነው ከዲቭ ተውፊቅ ፓሻ የመላ ግብጽ ሎጆች ግራንድ ማስተር ሊሆን ችሏል፡፡[7]
በአፍሪካ የፍሜሶን ጅማሮን ታሪክ በቀላሉ ማግኘት አይቻልም፤ እስክናሰፋው ድረስ ለግዜው ማግኘት የቻልነውን እንዳስሳለን፡፡ አውሮፓውያኑ ፍሪሜሶናዊነትን ወደ አፍሪካ ሲያመጡ መጀመርያ የከፈቷቸው ሎጆች በቅኝ ገዢ ፍሪሜሶኖች የተከፈቱ እንደመሆናቸው ለነጮች ሰፋሪዎች (ነጋዴዎች፣ ታጣቂዎችና ሰራተኞች) የሚሆኑ ብቻ ነበሩ፡፡ የፈረንሳዩ ግራንድ ኦርየንት የመጀመርያ ሎጁን በጥቁር አፍሪካ የመሰረተው እ.ኤ.አ. በ1781በሰይንት ሉ፣ ሴኔጋል ነበር፡፡[8]ቀጥለውም ቅኝ አገዛዛቸው ስር ባስገቧቸው ሃገሮች ሞሮኮ፣ ቱኒዝያ፣ ማዳካስካር፣ ጊኒ እና ኮንጎ ቅርንጫፎቻቸውን ከፍተዋል (ሞሮኮዎቹና ሙር ህዝቦች እየተባሉ የሚታወቁት ከላይ እንዳየነው ቀድሞኑ ከፍሪሜሶን ፍልስፍና ጋር በሱፊ ፍልስፍናቸው ምክንያት አንድ ነበሩ ማለት ይቻላል)፡፡
የዳች ኢስት ኢንዲያ ካምፓኒ አባል የሆኑ ቅኝ ግዛት አስፋፊዎችም በበኩላቸው በኔዘርላንድ ግራንድ ኢስት ስር ፈቃድ በመውሰድ በደቡብ አፍሪካ የመጀመርያውን የፍሪሜሶን ሎጅ፡ ሎጅ ጉድ ሆፕ (ሎጅ ቁ. 12) እ.ኤ.አ. በ1772 መስርተዋል፡፡[9]
ፍሜሶኖቹ ለመበዝበዝና ለመጨፍጨፍ የመጡ ነበር፡፡ ታሪክ ተመራማሪው ፕሮፌሰር ናይጄል ዎርደን እንደሚለው፡
እዚህ ኬፕ ጋር ሰፋሪዎች እንዲመጡላቸው አልፈለጉም፣ ያገራቸውን ሰዎችን ካሰፈሩ ወጪው ይጨምርባቸዋል፡፡ ስለዚህም ወደ ባርያ ጉልበት ፊታቸውን አዞሩ፡፡ ዳች ኢስት ኢንድያ ካምፓኒ (ቪኦሲ) ወደ ኬፕ ታውን ከ1658ጀምሮ 63,000 ባሮችን አምጥቷል፡፡ ከምስራቅ አፍሪካ፣ ከህንድ፣ ከኢንዶነዢያ የመጡ ነበር፡፡ ባርነቱ እስከ 1838 ድረስ ቀጥሎ ነበር፡፡ በዛን ዘመን ዜጎች ባርያ ይገዙ ነበር፣ ኬፕ ታውን የባርያ ማህበረሰብ ሆነች፡፡[10]
በቅኝ አገዛዝ ዘመን ፍሪሜሶኖች ነጻ አውጪ ሁነው ቢታዩም እንኳ ቅኝ ገዢዎቹም ፍሜሶኖች ነበሩ፡፡ የቦር ጦርነት (1899-1902) እየተባሉ የሚታወቁት፣ የብሪቲሽ ግዛትን የሚያስፋፉ ጦርነቶችን በዋናነት ሲያንቀሳቅሱ የነበሩት ፍሜሶኖቹ፡ ሴሲሊ ሮድስና የክቡ ጠረጴዛ ቡድን አጋሮች ናቸው፡፡ በዚህ መንገድ አብዛኛውን የደቡብ አፍሪካ የወርቅ እና የአልማዝ መአድን የሚገኝበትን ቦታ ለመቆጣጠር ችለዋል፡፡[11]በብሪታንያ ቅኝ ገዢነትና ኢምፐርያሊዝም አጥብቆ የሚያምነውና ይህን እንዲፈጽም የሚስጥር ማህበር መስርቶ ሃብቱን ለማህበሩ የተናዘዘው ሴሲሊ ሮድስ በአፖሎ ዩኒቨርሲቲ ሎጅ ነበር ፍሪሜሶን የሆነው፡፡ ዓለምን ሁሉ በብሪታንያ ስር ለማድረግ ባለው ሃሳብ ፍሪሜሶን ላይ ባየው እንከን ነበር የራሱን የሚስጥር ማህበር የመሰረተው፡፡[12]
በምእራብ አፍሪካ ደግሞ እ.ኤ.አ. በ1791 ቡላን ሎጅ በፖርቺጊስ ጊኒ፤ በ1810 ቶሪድዞንያን ሎጅ በኬፕ ካስል፣ ኬፕ ኮስት፤ በ1820ሎጅ ኦፍ ጉድ ኢንተንት በፍሪታውን፣ ሴራልዮን፤ በ1833 ሰይንት ጆንስ ሎጅ በጎልድ ኮስት (የዛሬይቱ ጋና) ተመስርተው የነበሩ ሲሆን አሁን የሉም፡፡[13]በ1859 ጎልድ ኮስት ሎጅ በጎልድ ኮስት (የዛሬይቱ ጋና)፤ በ1867 ሌጎስ ሎጅ በናይጄርያ ተመስርተዋል፡፡ በ1913 የሰሜንና ደቡብ ናይጄርያ ዲስትሪክት ግራንድ ሎጅ የተመሰረተ ሲሆን የሰሜኑና ደቡቡ መዋሃድ ተከትሎ በ1916 ስሙ የናይጄርያ ዲስትክት ግራንድ ሎጅ ተባለ፡፡ አይሪሾቹ ደግሞ በ1897 የማክዶናልድ ሎጅ ካላባር መስርተዋል፡፡ ስኮቲሾቹ ደግሞ በ1915 ሎጅ አካዳሚክ ቁ.1150ን ለመጀመርያ ግዜ መስረተዋል፡፡ በዚህ መልኩ የተለያዩ የአፍሪካ ሃገሮች ቅርንጫፎቻቸውን ከፍተዋል፣ በኢትዮጵያ በይፋ የሚታወቅ ቅርጫፍ የላቸውም፡፡
ዛሬ በብዙ መቶዎች የሚቆጠሩ ሎጆች በመላው አፍሪካ ይገኛሉ፡፡ ሚስጥራዊ እንደመሆናቸው ታሪካቸውን በተሟላ መልኩ አጥርቶ መዘገብ ይከብዳል፡፡ ከላይ ያለው በቂ ባይሆንም አጠቃላይ ምስሉን ያሳያል፡፡ ቀጥለን ከስር ዛሬ አፍሪካን እየመሩ ያሉ ፍሪሜሶን ፕሬዚደንቶችን እንተዋወቃለን፡፡

ፍሪሜሶንን ያገዱ የአፍሪካ መሪዎች

የአፍሪካ ሕብረተሰብ ሃይማኖታዊ በመሆኑና ፍሪሜሶኖች አውቆም ሆነ ተታሎ ቢክዱትም የመጨረሻ ሚስጥሩ ሰይጣን አምልኮ በመሆኑ ፍሪሜሶን መሆን ዛሬ ላይ አወዛጋቢ ነው፡፡ እ.ኤ.አ. በ1963 የኮትዲቯሩ መሪ ፌሊክስ ሁፌት ቦኒ እያሴሩብኝ ነው በማለት ሶሻል ዲሞክራት የነበሩት ተቃዋሚዎቹን ብዛት ያላቸው ከፈረንሳይ ግራንድ ኦርየንት ጋር የተገናኙ ፍሪሜሶን የሆኑትን ሲያሳድድ ነበር፡፡ ፍሪሜሶንም ታግዶ ነበር፡፡ ሆኖም ግን በ1970 “ሁሉ ነገር ፈጠራ ነው” ብሎ እራሱ በማስተባበሉ እግዱን አንስቶ ለሜሶኖቹ ስልጣን ሁሉ ሰጣቸው፡፡
በዛየር ሞቡቱ እ.ኤ.አ. በ1965 ስልጣን ሲይዝ ፍሪሜሶንን ያገደ ሲሆን፣ ተመልሶ በ1972 አንስቶታል፡፡ በማዳጋስካር ፕሬዚደንት ዲዴር ራትሲራካ በመጀመርያ ስልጣን ዘመኑ (1975-93) ፍሪሜሶን ታግዶ የነበረ ሲሆን በ90ዎቹ ተመልሶ መጥቷል በ96 የማዳጋስካር ግራንድ ናሽናል ሎጅ ተመስርቷል፤ በዲዴር ሁለተኛው ስልጣን ዘመኑ (1997-2002) የሚስጥር ማህበሩ አልተነካም፡፡ በጊኒ በሴኮ ቱሬ፣ በማሊ በሞዲቦ ኪየታ፣ በቤኒን በማቲዩ ኬሬኮ ፍሪሜሶነሪ ታግዶ ነበር፡፡ በ1980ዎቹ በቤኒን መልሶ ተከፍቷል፡፡ በማሊና ጊኒ መች መልሶ እንደተከፈተ ለግዜው ባላገኘውም ዛሬ ላይ ግን ይንቀሳቀሳሉ፡፡
በላይቤርያ ሳሙኤል ዶ እ.ኤ.አ. በ1980 በመፈንቅለ መንግስት ስልጣን ሲይዝ ፍሪሜሶኖችን ክፉኛ አሳድዶ ነበር፡፡ ለዘመናት የሃገሪቱ ፕሬዚደንት ቢሮ አፍሮ-አሜሪካውያን በሆኑ የሚያዝ የነበረ ሲሆን፣ እኚህም ከጥቁር አሜሪካውያን ግራንድ ኦርደር፣ ፕሪንስ ሃል ቻፕተር እየተባለ የሚታወቀው ፍሪሜሶን ማህበር ጋር የተገናኙ ነበሩ፡፡
በናይጄርያ ደግሞ ፍሪሜሶኖች የኢኮኖሚው አሽከርካሪ የነበሩ ሲሆኑ በ1970ዎቹ መጨረሻ የያኩቡ ጎዎን ወታደራዊ መንግስት የሚስጥር ማህበሩን የሚያግድ አዋጅ አውጥቶ ነበር፡፡ የመንግስት ባለስልጣናት ስራቸውን አልያም የሚስጥር ማህበሩን እንዲመርጡ ተገደው ነበር፡፡ ሆኖም ግን ዛሬ ላይ ተመልሰው ይንቀሳቀሳሉ፡፡
አሁን አሁን በሙስሊም ሃገሮች ፍሪሜሶን የተወገዘ ቢሆንም ይንቀሳቀሳል፡፡ በእስልምና ሰፊ ዝና ያላቸውና የሙስሊም ወንድማማችነት መስራቹን ሃሰን አልበናን የቀረጹት ሰዎች ጀማል አልዲና አልአፍጋኒ እና መሃመድ አብዶ ፍሪሜሶኖች ነበሩ፡፡ ፍሪሜሶኖቹ ሳላፊያ የሚባል እንቅስቃሴ መስራቾች ናቸው፡፡ ሌላ ሃሰን አልበናን የቀረጸው የሳላፊያ ህትመት “ዘ ላይት ሃውስ” አዘጋጅ የነበረው ራሺድ ሪዳ ፍሪሜሶን ነበር፡፡ እራሱም አልበና የማህበሩ አባል ሁኗል፡፡ የአልበናን ንድፈ ሃሳብ በማስተጋባት የሙስሊም ወንድማማችነት ቀንደኛ የንድፈ-ሃሳብ ሰው ሁኖ የተካው ሰዒድ ኩትብ እንኳ የሙስሊም ወንድማማችነት አባል ያልነበረና ሆኖም ግን ፍሪሜሶን የሆነ ሰው ነበር፡፡[14]
ወደዋናው ታሪካችን ስንመለስ ደግሞ ለምሳሌ በቅርቡ (እ.ኤ.አ. በ2000) የፈረንሳይ ግራንድ ናሽናል ሎጅ ቅርንጫፎቹን በጅቡቲ ከፍቷል፡፡ አባሎች ቁርአን ላይ ሚስጥር እንደማያወጡ ቃለ መሃላ ይፈጽማሉ፡፡ ሴኔጋልም ቢሆን የኃይል ሚዛኑን የተቆጣጠሩት አብዛኞቹ ፍሪሜሶን ናቸው፡፡
ለአፍሪካውያን የፍሪሜሶን አባል መሆን ከገዢዎቹ ነጮቹ ጋር እኩል ስለሚያደርጋቸው እና በባህላዊ እምነት ያሉት ወይም ደግሞ ሱፊዎቹ የሚስማማ ሁኖ ስለሚያገኙት አባል መሆን ያኮራቸዋል፡፡
ስለዚህም በዚህ አወዛጋቢነቱ ምክንያት በግልጽ የፍሪሜሶን አባል መሆናቸውን ያሳወቁ የአፍሪካ መሪዎች ጥቂት ናቸው፡፡ እናም የሆኑትን ሁሉንም ማወቅ ባንችልም ጥቂቶቹን ማየት ይቻላል፡፡

ፍሪሜሶን የአፍሪካ መሪዎች

የሮማንያ የሜሶኖች ህትመትን እንደዘገበው ከሆነ በ16ኛው የአፍሪካ ሕብረት (እ.ኤ.አ. ጥር 24-32፣ 2011 ዓ.ም) በተካሄደው ጉባኤ የአፍሪካ ፍሪሜሶን ግራንድ ማስተሮች ስብሰባ አደረጉ ብሎ ዘግቦ ነበር፡፡[15]ግራንድ ማስተሮቹ የየሃገራቸው መሪዎች የነበሩ ናቸው፡፡ ከተሳተፉት ውስጥ አሊ ቦንጎ (ጋቦን)፣ አብዱላዬ ዋዴ (ሴኔጋል)፣ ዴኒስ ሳሶ ንጌሶ (ኮንጎ-ብራዛቪል) ይገኙበታል፣ በስብሰባቸው የፈረንሳዩ መሪ ኒኮላስ ሳርኮዚ ተገኝቶ ነበር፡፡ ከስር በዝርዝር እንመልከታቸው፡፡
የቀድሞ የኮንጎ ሪፐብሊክ የአሁኗ ኮንኮ-ብራዛቪል የቀድሞ መሪ ፓስካል ሊሱባ እና በሃይል ከስልጣን ያስወገደው ዴኒስ ሳሶ ንጌሶ ፍሜሶኖች ናቸው፡፡ ሆኖም ግን የተለያየ ማህበራት ናቸው፡፡ ሊሱባ የፈረንሳይ ግራንድ ኦርየንት አባል ሲሆን፣ ሳሶ ንጌሶ ደግሞ ከፈረንሳይ ግራንድ ናሽናል ሎጅ ጋር የተገናኘ የሴኔጋል ሎጅ አባል ነው፡፡ ታጣቂዎች በዋና ከተማዋ ከተጋጩ በኋላ የአፍሪካና የፈረንሳይ ፍሪሜሶኖች፡ የፈረንሳይ ግራንድ ሎጅ፣ የአይቮሪኮስት ዩናይትድ ግራንድ ሎጅ እና ግራንድ ኦርየንት እና የካሜሮን ዩናይትድ ሎጅስ በጋራ ሰላም ለማውረድ ሙከራ አድርገው ነበር፣ ባይሳካላቸውም፡፡[16]
እ.ኤ.አ.በ2009 ያረፈው የጋቦኑ መሪ ኦማር ቦንጎም ፍሪሜሶን ነው፡፡ ፕሬዚደንት ሁኖ የተካው ልጁም አሊ ቦንጎም ፍሪሜሶን ነው፡፡ የፈረንሳይ ናሽናል ግራንድ ሎጅ፣ ግራንድ ማስተር የሆነው ወደጋቦን መጥቶ ነበር አባቱ ይዞት የነበረውን ቦታ ያስረከበው፡፡ አሊ ቦንጎ በዛኑ አመት በሊበርቪሌ የዓለም የሬጉላር ፍሪሜሶነሪ ጉባኤ እንዲካሄድ አድርጓል፣ ጉባኤው እንዲካሄድ አባቱ በሕይወት እያለ ያስጀመረው ጉዳይ ነበር፡፡ በጉባኤው የቀድሞ የፈረንሳይ ግራንድ ኦርየንት ግራንድ ማስተር እና ከ2000-2003 የፈረንሳይ ፕሬዚደንት የሽብርና ወንጀል ልዩ አማካሪ የነበረው አልየን ባዉር ተገኝቶ ነበር፣ ከቀብሩ በኋላ አሊ ቦንጎን ሹሞታል፡፡
ፍራንኮይ ስቴፋኒ የፈረንሳይ ናሽናል ግራንድ ሎጅ ግራንድ ማስተር የሆነው ደግሞ አሊ ቦንጎን የጋቦን ግራንድ ሎጅ ግራንድ ማስተር አድርጎ ሹሞታል፡፡ ይህም አሊ ቦንጎን የሁለቱም፡ የጋቦን ግራንድ ሎጅ እና የግራንድ ኢኳቶርያል ራይት ግራንድ ማስተር እንዲሆን ያደርገዋል፡፡ አባቱ ኦማር ቦንጎ የሜሶኖቹን ሎች የፖለቲካ ደጋፊዎቹ መመልመያ አድርጎ ይጠቀምበት ነበር፡፡ ኦማር ቦንጎ ፕሬዚደንት ከመሆኑ አስራ አራት አመት በፊት እ.ኤ.አ. በ1953ነበር አባል የሆነው፣ በጋቦን ሁለት የተለያዩ ሎጆችን እንዲመሰረቱ አድርጓል፡፡ አንዱ ግራንድ ራይት ኢኳተርያል – ግራ ዘመም ከሆነው ግራንድ ኦርየንት ጋር የተያያዘውና፤ ሁለተኛው ደግሞ የጋቦን ግራንድ ሎጅ – ቀኝ ዘመም ከሆነው ከፈረንሳይ ናሽናል ግራንድ ሎጅ ጋር የተያያዘው ነው፡፡ የቦንጎን አመኔታ ለማግኘት ፖለቲከኛው ከነዚህ ከሁለቱ የአንዱ መሆን ይገባዋል፡፡ የጋቦን ገዢዎች ሙሉ ለሙሉ በሚባል መልኩ የነዚህ ሎጅ አባል ናቸው፡፡[17]ሄግሊያዊ ዲያለክቲክ ማለት እንዲህ ነው፣ ሁለቱንም ጽንፎች ከተቆጣጠርክ የውጤቱ ባለቤት ትሆናለህ፡፡
እ.ኤ.አ.ከ2003-2013 የማእከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ መሪ የነበረው፣ ከ1991 ጀምሮ መፈንቅለ መንግስት ሙከራ ሲያደርግ፣ ካገር ሲባረርና አስተዳደር ሲቀየር ሲመላለስ ከቆየ በኋላ ከውጭ አምጥቶ ስልጣን የሰጠውን ፓታሴን ገልብጦ ስልጣን በኃይል እ.ኤ.አ. በ2003 የተቆጣጠረው ፍራንኮይስ ቦዚዜም ፍሜሶን ነው፡፡ በ2013 የዓማጽን ሰራዊት ከሃገር አባሮታል፡፡ የአካባቢው የምእራባውያን ተላላኪ ሃገሮች ቦዚዜን ለማትረፍ ያደረጉት ሙከራ አልተሳካም፡፡ አማጽያኑን ወክሎ የሽግግር መሪ የሆነው አዲሱ የማእከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ መሪ ከውጭ አገሮች ጋር ያሉትን ውሎች እየፈተሸን ነው ብሏል፡፡
ኢድሪስ ዴቢ የቻድ መሪውም ፍሪሜሶን ነው፡፡ ከነዳጅ ተፈጥሮ ሃብቷ የሚገባትን ያህል ያልተጠቀመች ሃገር ስትሆን የዓለም ባንክ በቻድና ካሜሮን የሚያልፍ የነዳጅ ትቦ ሊያዘረጋ ፈንድ ከለቀቀላት በኋላ ፈንዱን ድሆች ልመግብበት ነው ብሎ ካዘዋወረ በኋላ 30 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር የሚሆነውን መሳርያ ለመግዛት ተጠቅሞበታል፡፡[18]
ጁኔ አፍሪኩዌ የተባለ የፈረንሳይ ህትመት ደግሞ ረዘም ያለ ዝርዝር ያወጣ ሲሆን ከነዚህ መሃከል የአይቮሪኮስት መሪ የነበረው ሎረን ባግቦ ደንብ የማያከብር ፍሪሜሶን (ሽርጥ የሌለው ፍሪሜሶን) ሲለው ከፈረንሳይ ጋር ተባብሮ የባግቦን መንግስት የገለበጠው አላሳን ኦታራም ፍሪሜሶን ነው ይለዋል (የሁለቱን ዝርዝር ከስር እንመለስበታለን)፡፡[19]ህትመቱ በተጨማሪም በጥር 2011 የባግቦ ባለቤት ሲሞን ባግቦ ፍሪሜሶኖች ላይ ጦርነት በማወጅ ከኮትዲቯር ተጠራርገው እንዲወጡ ጥሪ አቅርባ ነበር፡፡[20]
በተጨማሪን ከዝርዝሩ የጋቦኑ ኦማር ባንጎ በፊት መሪ የነበረው ምባ፣ የቀድሞ የቶጎ መሪ ናሲንግቤ ኢያዴማ፣ አባቱ ሲሞት መንበረ ስልጣኑን በመረከብ አሁን የቶጎ መሪ የሆነው የኢያዴማ ልጅ ፋኡር ናሲንግቤ፣ ባንከር ነበረውና አሁን የቤኒን መሪ የሆነው ቶማስ ያዪ ቦኒ፣ በአባቱ ቦታ የተተካው የኮንጎው መሪ ጆሴፍ ካቢላ፣ የሴኔጋሉ አብዱላዬ ዋዴ፣ የጊኒው ፕሬዚደንት አልፋ ኮንዴ፣ በመፈንቅለ መንግስት የተወገደው የማሊው መሪ አማዱ ቱማኒ ቱሬ ፍሪሜሶን መሪዎች ብሎ ይዘረዝራቸዋል፡፡[21]
የቡርኪነፋሶው መሪ ብሌዝ ኮምፓኦሬ ደግሞ ግራንድ ማስተር የነበረ ሲሆን፣ አሁን የቡርኪነፋሶ ሎጅ ግራንድ ማስተር የደህንነት ሚኒስትሩ ጂብሪል ባሶሌ ነው፡፡ የጋቦን ተቃዋሚ ፓርቲ መሪ የሆነው የማስተሩ አሊ ቦንጎ “ወንድም” ፍሪሜሶን ነው፡፡[22]
ሌሎችም የቀድሞ የጋና ፕሬዚደንት (2001-2009) የነበረው ጆን ኩፎር፤ አሁን በአፍሪካ ህብረት የሶማልያ ልኡክ የሆነውና ከኩፎር በፊት ለረዥም ግዜ በሁለት የተለያዩ ግዝያት የጋና መሪ የነበረው ጄሪ ጄ. ረውሊንግ፤ የካሜሮኑ ፕሬዚደንት ፖል ቢያ፤ የቡርኪነፋሶው ፕሬዚደንት ብሌዝ ኮምፓኦሬ፤ የኒጀሩ የቀድሞ ፕሬዚደንት ማማዱ ታንጃ፤ የአይቮሪኮስት የቀድሞ መሪ ሮበርት ጉኤ የተረጋገጡ ፍሪሜሶን መሪዎች ናቸው፡፡[23]
የሴኔጋሉ የቀድሞ መሪ የነበረው አብዱላዬ ዋዴም “ፍሪሜሶን ፎር ዳሚስ”የሚባል ለጀማሪዎች የተሰራ የፍሪሜሶን ፕሮፖጋንዳ መጽሐፍ ሲያነብ ታይቶ ውዝግብ ከተነሳ በኋላ ቀድሞ የዶክትሬት ዲግሪውን ከሰራ በኋላ ስለሜሶኖች ከጓደኛው ደጋግሞ ሲሰማ ለማወቅ ሲል አባል ሁኖ እንደነበርና የጠበቀውን እውቀት ማግኘት ስላልቻለ ተመልሶ እንደወጣ ቃለ መጠይቅ ላይ ተናግሯል፡፡[24]
የታንዛንያው መሪ የነበረው ቤንጃሚን ምካፓ ደግሞ በአንድ ወቅት በዳሬሰላም ፍሪሜሶኖች መቶኛ ምስረታ በአላቸውን በሚያከብሩበት ወቅት የክብር እንግዳ አድርገው ጠርተውት ነበር፡፡ የእንግሊዝ ፍሪሜሶነሪ ወደ ምስራቅ አፍሪካ ለመጀመርያ ግዜ ሲመጣ ዛንዚባር ነበር ቅርንጫፉን እ.ኤ.አ. በ1904 የከፈተው፡፡[25]
እራሱን የእኩልነት፣ ወንድማማችነትና ነጻነት ፋና አድርጎ የሚወስድ ማህበር እዚህ ከጠቀስናቸው አብዛኞቹ በብልሹነታቸው ከሚታወቁ መሪዎች ጋር መግጠሙ የሚደንቅ አይደለም፣ በፈረንሳይ የመጀመርያው አብዮት፣ አብዮተኛ ፍሪሜሶኖች ምን እንደሰሩ ታሪክ መዝግቦታል፡፡[26]

የፍሪሜሶኖች ክህደት፡ የአይቮሪኮስት ልምድ

ከላይ ፍሪሜሶኖች በአፍሪካ ቅኝ አገዛዝ እና ባርያ ንግድ ላይ ተሰማርተው እንደነበሩ አስተውለናል፣ አሁን ደግሞ በዘመናዊ የአፍሪካ ፖለቲካ የአይቮሪኮስት ልምድን በመውሰድ የፈጸሙትን በደል እንመለከታለን፡፡ በ2011 በአይቮሪኮስት ምርጫውን ተከትሎ በተነሳ ውዝግብ “ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ” ወድያውኑ ለውረን ባግቦን በማውገዝ ማእቀብ ጥለውበታል፡፡ የሃገሬው ሁኔታ ውስብስብ መሆንና የውጤቱ መቀራረብ ታይቶ ለውሳኔ መቸኮል አይገባም ነበር፣ ሁኔታውን ያወገዘው ብቸኛው መሪ የዩጋንዳው ሙሴቪኒ ነበር፡፡ ያለ አፍሪካ ህብረት እውቅና በምን ስሌት ማን ፈቅዶላቸው ፈረንሳውያኑ ኮትዲቫር ሊገቡ እንደቻሉ ይጠይቃል፡፡[27]
ሰብአዊነትን ባፋቸው ቢያነሱም፣ ፍሪሜሶናዊነት ለምእራባውያን ኢምፐርያሊዝም፣ እና አዲስ የዓለም ስርዓት ማስፈፀምያ ቁልፍ ነው፡፡
የፈረንሳይ ፍሪሜሶኖች ደግሞ በአይቮሪኮስት ጣልቃ በመግባት ጥቅማቸውን በማስጠበቅ ያሹትን ፈጽመዋል፡፡ ባግቦን ያወገዙት አጎራባች የአፍሪካ መሪዎችና የፈረንሳይ ፖለቲከኞችና ከበርቴዎች ሁሉ የአንድ ሎጅ አባሎች ናቸው፡፡ የፈረንሳይ ቅኝ ግዛቶች ይተዳደሩ የነበረው በፍሪሜሶኖች ሰፊ ተሳትፎ ነበር፡፡
በአይቮሪኮስት የተደረገው ዘመቻ የዣክ ሺራክ ነበር፡፡[28]የፈረንሳይ “ሰላም አስከባሪ” ወታደሮች የአይቮሪኮስት አየር ሃይልን እንዲያጠቁ ያዘዘው፣ ሆቴል ዲ አይቮሬን እና የፕሬዚደንት ባግቦን መኖርያ እንዲከቡ ከመቶ በላይ ታንኮች የላከው፣ ምንም ያልታጠቁና ስጋት ያልሆኑ ወጣቶች የፈረንሳይ ወታደሮች ባግቦን እንዳይገድሉ ወይም እንዳይገለብጡ ለመከላከል የተሰለፉት ላይ ተኩስ እንዲከፈትባቸው ያዘዘው ሺራክ ነው፡፡ እንዲህ አይነቱ ያፈጠጠ ጣልቃ ገብነት በሃገራችን የማይታሰብ ነው ልትሉ ትችላላቹ፣ ሆኖም ግን የአሜሪካው አፍሪኮም እና ሰው አልባ ተዋጊ አየሮች በአፍሪካ መስፋፋት ይህ እውን ከመሆኑ የሚያግተው እንደሌለ ያሳያል፡፡
የፈረንሳይ ቅጥረኞች/ወኪሎች የሚፈልጓቸውን ከመፈንቅለ መንግስት መታደግ የማይፈልጓቸውን ለመፈንቀል አያመነቱም፡፡ የምርጫውን ውዝግብ ክፍተት ከማግኘታቸው በፊት ባግቦን ለመፈንቀል ያደረጉት ሙከራ በደንብ የተመዘገበ ነው፡፡ የፈረንሳዮች እንቅስቃሴን ያጋለጠ የተለያዩ ስብሰባዎች መዝገብ የያዘ የፈረንሳይ ላፕቶፕ ሊያዝ ችሎ ነበር፡፡[29]ቡርኪነፋሶ ላይ በተደረገ ስብሰባ መፈንቅለ መንግስት የሚያደርጉበት ዘዴ በደህንነት ዘገባ ላይ ሰፍሮ ነበር፣ እ.ኤ.አ. በሕዳር2006 ላይ በአቢጃን መፈንቅል እንደሚያስነሱ የወሰኑበት ነበር፡፡ ይህ ባግቦን ከምርጫው በኋላ ጣልቃ ገብተው ካስወገዱት ከአምስት ዓመት በፊት መሆኑ ነው፡፡ ባግቦን የጠሉት ከቅኝ አገዛዝ ነጻ ሲወጡ የተደረጉ አሳሪ ውሎችን ለማስወገድ እየታገለ ስለነበር ነው- ከስር እናየዋለን፡፡ የደህንነት ዘገባው፡
“አላሳን ኦታራ [አሁን ባግቦን የተካው] ስብሰባውን በመክፈት ፖቼትን አስተዋወቀ፡፡ [ፖቼትም]ቀጥታ ከሺራክ መልእክት ይዞ እንደመጣና መልእክቱም “ኤዲኦ (ኦታራ) ልጃችሁና ወንድማችሁ ከ2005 ምርጫ በፊት የአይቮሪኮስት ሪፐብሊክ ፕሬዚደንት ይሆናል፡፡” ሺራክ “ሳንስማማበት በአይቮሪኮስት ትጥቅ መፍታት አይኖርም፡፡ ትጥቅ ከመፍታት በፊት የACCRA III ስምምነት ላይ ድምጸ ውሳኔ መሰጠቱ ወሳኝ ነው፡፡
“መላ ፈረንሳይና ዣክ ሺራክ ኤዲኦ በአምስት ወር ውስጥ ማለትም በሕዳር ስልጣን እንዲይዝ ይደግፉታል፡፡ አሁን ማሊ እና ቡርኪነፋሶ ውስጥ እየሰለጠኑ ያሉ ቅጥረኛ ሰራዊቶች (መርሲነሪስ) መልምለን ጨርሰናል፡፡ … ዓላማችን ኤዲኦን ስልጣን ላይ ማውጣት ነው፡፡ … ነሐሴ ተመልሼ ከፕሬዚደንት ኮምፓኦሬ ጋር እመጣለው፣ ከመርሲነሪዎቹ ጋር አስተዋውቃችኋለው፡፡ ኦታራ ስልጣን ለመያዝ በሕዳር ይመለሳል፡፡”
ቀጣዩ ተናጋሪ ብሌዝ ኮምፓኦሬ ነበር፣ የቡርኪነፋሶ ፕሬዚደንት፣ ፖቼትንና ሺራክን በማመስገን ጀመረ፡፡ የአይቮሪኮስት መንግስት የኦታራ መብትን በመጋፋቱ ከወቀሰ በኋላ የሚከተለውን አለ፡
“በዚህ ነገር እኮ የእኔው ስም ነው እየተበላሸ ያለው፡፡ በቡርኪና የእኔ መኮንኖች መርሲነሮቹን ዝግጁ እንዲሆኑ ጥሩ ስራ እየሰሩ ነው፡፡ እደግፋችኋለው፡፡ ከእዛው ሁነን ለእናንተ ነገሮች ቦታቸውን ለማስያዝ እየተንቀሳቀስን ነው፡፡ አትፍሩ፤ በትንሽ ጊዜ ውስጥ ውጊያውን እናሸንፋለን፡፡ በአምስት ወር ውስጥ ሁሉ ነገር ዝግጁ ይሆናል፡፡”
የአምስት ወሩ እቅድ ሳይሳካ ቀርቶ በቀጣቹ አምስት አመታት የባግቦን መንግስት ለመገልበጥ የተለያዩ ሙከራዎች ተደርገው ነበር፡፡ አብዛኞቹ ቀድሞ ተደርሶባቸው ተጨናግፈዋል፡፡ በእነዚህ ሁሉ ሙከራዎች ዋና ተሳታፊዎቹ የፈረንሳይ መልእክተኞች፣ የፈረንሳይ (የተባበሩት መንግስታት)ሰላም አስከባሪዎች እና በዙርያው ያሉ ከላይ ያየናቸው ከፈረንሳይ ፖለቲከኞችና ቁንጮዎች ጋር የፍሪሜሶን ትስስር ያላቸው የአፍሪካ ፕሬዚደንቶች ናቸው፡፡ አስተግባሪ አካላት ደግሞ አቢጃን መቀመጫቸውን ያደረጉ ድምበር ዘለል የፈረንሳይ ድርጅቶች ውስጥ የሚሰሩ የፈረንሳይ ወኪሎች/ኤጀንቶች ናቸው፡፡
ይህ የታወቀ የፈረንሳይ አዲስ ቅኝ አገዛዝ (ኒዮ-ኮሎኒያል) ባሕርያት መገለጫ ነው፡፡ የፈረንሳይ ባለሃብቶችንና ፖለቲከኞችን በፈረንሳይ ስም የሚጠቀሙበት ዘዴያቸው ነው፡፡ በአይቮሪኮስት ልዩ የሚያደርገው “ዓለም አቀፉ ሕብረተሰብም” ከጎናቸው እንዲቆም ማሳመን መቻላቸው ብቻ ነው፡፡
እ.ኤ.አ.በ1960 የአፍሪካ ቅኝ ግዛቶቿን ነፃ ማውጣት ግዴታ ሲሆንባት ፈረንሳይ አሳሪ ውል እያስፈረመች “ለቀቀቻቸው”፡፡ ባስፈረመቻቸው“ፓክት ኮሎኒያል” መሰረት የውጭ ምንዛሪ ክምችታቸው (85 መቶኛ) በፈረንሳይ እንዲቀመጥ ማስገደድ፣ ቁልፍ የሐገሪቱን ጥሬ ሃብት ቁጥጥሩ በፈረንሳይ እንዲሆን፣ በነፃነት መንቀሳቀስ የሚችሉ ሰራዊቶቿን በሐገሪቱ የማስፈር መብት፣ የጦር መሳርያቸውን በሙሉ ከፈረንሳይ የመግዛት ግዴታ፣ የፖሊስና ሰራዊት የበላይ አሰልጣኝ መሆኗ፣ የፈረንሳይ ቢዝነሶች በቁልፍ ዘርፎች (ውሃ፣ ኤሌክትሪክ፣ ወደብ፣ ትራንስፖርት፣ ኃይል ወዘተ …) ላይ ሞኖፖሊያቸው እንዲጠበቅ የሚያስገድድ ውል ነበር ያስፈረመቻቸው፡፡ ይህ ብቻ ሳይሆን ፈረንሳይ ሃገራቱ ከፍራንክ ቀጠና ውጪ ማስገባት የሚችሉት ኢምፖርት ላይ ብቻ ሳይሆን ገደብ ያደረገችው፣ ከፈረንሳይ ኢምፖርት ማድረግ ያላቸውንም ዝቅተኛ ድርሻ ነግራቸዋለች፡፡ እኚህ ስምምነቶች አሁንም ድረስ ያልተቋረጡና ተፈጻሚነት ያላቸው ናቸው፡፡[30]ይህን ታቅፈው ነው ፓን-አፍሪካኒዝም የሚደሰኩሩት፡፡
የዚህ አሳፋሪ ውል ቀራጭ የካሜሮኑ ነጻነት ታጋይ ሙሜ በመርዝ እንዲገደል ውሳኔ ያስተላለፈው ጃኩዌ ፎካርት ነበር፣ በወቅቱ የፈረንሳይ የአፍሪካ ፖሊሲ የፕሬዚደንቱ አማካሪ እና የፈረንሳይ ደህንነት ቢሮ በአፍሪካ የሚስጥር እንቅስቃሴ ሰው ከነበረው ከቻርለስ ፓስኳ ጋር በመሆን እ.ኤ.አ. በ1959 የመሰረተው ሰው ነው፡፡ ይህ ሰው በፕሬዚደንቱ ቢሮ የአፍሪካ የሚስጥር ቡድን እና የአፍሪካና ፈረንሳይ ፍሪሜሶኖች ማገናኛ ሰው ነው፡፡[31]
በዚህ መልኩ በ1960 አዲስ ነፃ የሚወጡት ሃገሮች የሚረባ ነገር ሳያገኙ ባንዲራ፣ መዝሙር እና በተ.መ.ድ. መቀመጫ ተሰጥቷቸው አዲስ ሃገር ሁነዋል፡፡ በዚህን ጊዜ ነበር ፎካርት ቁልፍ ሚና የተጫወተው፣ ከላይ እንዳየነው በፋይናንስና ኢኮኖሚ፣ በባህልና ትምህርት እና በብሔራዊ ሰራዊት ዘርፎች አስገዳጅ ውል በመቅረጽ፡፡
በመጀመርያ አስራአንድ ሃገሮች፤ ሞሪታንያ፣ ሴኔጋል፣ አይቮሪኮስት፣ ዳሆሜ (አሁን ቤኒን)፣ ላይኛው ቮልታ (አሁን ቡርኪነፋሶ)፣ ኒጀር፣ ቻድ፣ ጋቦን፣ ማእከላዊ አፍሪካዊ ሪፐብሊክ፣ ኮንጎ ብራዛቪል እና ማዳጋስካር ናቸው፡፡ ቀድሞ በተ.መ.ድ. ባላደራነት ስር የነበሩት ቶጎና ካሜሮን ወደቡድኑ እንዲገቡ ተጠልፈዋል፡፡ በኋላ ላይ ደግሞ ማሊና የቤልጂየም የነበሩት ሩዋንዳና ቡሩንዲ እና ኮንጎ ኪንሻሳም ተጨመሩበት፡፡ የፖርቱጋል የነበሩት ድንበሮችና ኮሞሮስ እና ለረዥም ግዜ በፈረንሳይ ስር የነበረችው ጅቡቲም በዚሁ ውል ታስረዋል፡፡ እኚህ ሁሉ እስረኞች እ.ኤ.አ. በ1961 አዲስ በተቋቋመው የትብብር ሚኒስትሪ ስር ተደረጉ፡፡ እኚህን ሁሉ ሃገራት በሚፈራረሙት ውል የፈረንሳይ ኢኮኖሚያዊና ወታደራዊ እቅፍ ውስጥ እንዲታፈኑ አድርጓቸዋል፡፡ በዚህ ውል ምክንያት ፈረንሳይ በቀኝ ግዛቶቿ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ሕይወት ውስጥ ሕጋዊ የበላይነት እንዲኖራት አድርጓል፡፡[32]
ባግቦ ከነዚህ ማሰርያዎች ለመላቀቅ ያደረገው ሙከራ ፈረንሳይን እጅግ ማበሳጨቱ በአካባቢው ያሉ አገሮችን አላስደነቀም፡፡ ያካባቢው ፕሬዚደንቶች ስልጣናቸው ላይ እንዲቆዩ ያደረጋቸው የፈረንሳይ ሰራዊት ነው፡፡ ኢኮኖሚያቸው ደግሞ ሞኖፖል እንዲይዙ የተደረጉ የፈረንሳይ ቢዝነሶች ቁጥጥር ስር ነው፡፡ ፕሬዚደንቶቹ ለዚህ ሲሉ 85 መቶኛ ሃገራዊ ሃብታቸውን እንዲይዝ ለፈረንሳይ ግምጃ ቤት ይሰጣሉ፣ በተጨማሪም ወንበራቸውን እንዳያጡ ለፈረንሳይ ፖለቲከኞች ወፍራም መደለያ ይከፍላሉ፡፡
የአይቮሪኮስት መሪ የነበረው ባግቦ የብሪታንያ እና ካናዳ ልኡካንን በማባረር ቀርቦለት ነበረውን መደለያ (ጥገኝነትና ከክስ ነጻ መሆን) አልቀበልም በማለት ዓለም አቀፋውያኑን ንቀት አሳይቶ በመጋፈጡ አገር ውስጥ የነበሩ 9,500 ጠንካራ ሰላም አስከባሪዎች ተጨማሪ 1,000 እስከ2,000 ኃይል ተጠይቆ[33]በጉልበት እንዲወገድ ተደርጓል፡፡ በእርሱ ቦታም የረዥም ዘመን ወዳጃቸውን አስቀምጠዋል፣ ፓክት ኮሎንያልም አልተነካም፡፡
ይህን እንደምሳሌ ጠቀስነው እንጂ ለምሳሌ ጋዳፊን ከስልጣኑ እንዲወርድ የተደረገው በተመሳሳይ የብሔራዊ ጥቅሙንና የምእራባውያን የፋይናንስ የበላይነትን የሃገሩን የንግድ ሚዛን በመጠበቅና የወርቅ ክምችቱን በማብዛት ስለተቀናቀናቸው ነው፡፡ ከተባረረ በኋላ ሊብያ በአልቃይዳ ስር ገብታ ብሄራዊ ባንኳ ደግሞ በለንደን ፋይናንስ ከበርቴዎች እጅ ገብቷል፡፡ ለመጀመርያ ግዜም ባለ እዳ ሃገር ሁናለች፡፡
ጊኒ ጋርም ቢሆን መሪዋ መፈንቅለ መንግስት አድርጎ በጊኒ የነበረውን ቁንጮዎቹ ሲያተርፉበት የነበረውን የአደንዛዥ እጽ መስመር ከዘጋና የቀድሞ መሪ ልጅ (የእጹ ንግ ዋና መሪ የነበረውን ከቀጣ በኋላ) እና ከቻይና ጋር የ50 ቢሊዮን የመአድን ማውጣት ውል መፈራረሙ ፈረንሳዮችን መፈንቅል እንዲያደርጉበት አድርጓቸዋል፡፡[34]
እነዚህ መሪዎች አምባገነን መሆናቸውን ልብ ይሏል፤ ሆኖም ግን ምእራባውያኑ ለዘመናት ወደስልጣን ከማምጣት ጀምሮ ከአምባገነኖች ጋር አብረው የሚሰሩ ሲሆኑ መሪዎቹ ለሃገራቸው የሚጠቅም መስራት ሲጀምሩ ነብስ ግድያ ሙከራዎችና እንዲወገዱ እንደሚያደርጉም ልብ ይሏል፡፡

መደምደምያ

ለምን የተባበሩት መንግስታትና “የዓለም አቀፉ ማሕበረሰብ” ከተበዳዮቹ አፍሪካውያን ሳይሆን ከበዝባዦቹ ጋር እንደሚወግኑ (ከምእራባውያን ትርፍራፊ ለቃሚዎች ውጪ ላሉት) ግራ የሚያጋባ ጉዳይ ነው፡፡ ስለአፍሪካውያን የአዞ እምባቸውን መራጨት ከመጀመራቸው በፊት ይህን በደላቸውን ሊመልሱ ይገባል፡፡
ይህ የቀኝ ገዢዎች ፖለቲከኞችና ፍሪሜሶኖች ስርዓት የአፍሪካ የወደፊት እጣ መሆን የለበትም፣ ዓይኑን ያወጣ ብልሹ ስርዓትን ለማስጠበቅ ሰራዊት እየላኩ ንጹሐንን መግደል ማንም ቢሆን ዲሞክራስያዊ ሂደት ማስጠበቅ ነው ብሎ አያስበውም፡፡
እየሆነ ያለው እውነት ይህ ነው፡፡ ዓረቦች፣ ህንድና ቻይና ህዝባቸውን ሊቀልቡ ሰፊ የእርሻ መሬት ከአፍሪካ ፈልገው መጥተው ካፒታል ሲያፈሱ ምእራባውያኑ (ያለፈውን አሳፋሪ የባርያ ስርዓትና የቅኝ አገዛዝ ውጊያቸውንና ጭፍጨፋቸውን እና አሁን ያስቀመጡትን አሳፋሪ ውል ዘንግተው)ኢንቨስትመንቱን (ህጸጽ ቢኖርበትም) “አዲሱ የደቡብ-ደቡብ (የድሃ-ድሃ) ኢኮኖሚያዊ ግንኙነት አዲስ ቅኝ አገዛዝ ነው፣ መሬት ወረራ ነው ወዘተ.” ብለው የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች፣ የስነ ምህዳር ተቆረርቋሪዎች ወዘተ. ለማዝመትና በሚድያቸው ለማስተጋባት የሚቀድማቸው የለም፡፡
አዲሱ ቅኝ አገዛዝ ግን አሜሪካ ሰራዊቷን በክፍለ ዓለሙ ማሰማራቷ፣ ከአሸባሪዎችና ሙስሊም ወንድማማችነት ጋር ሁና ችግር የምትፈጥረው እና እንደ ፈረንሳይ ያለው አሳፋሪ ውሎችና ደባዎችን አያወሩም (የአሜሪካውን በቀጣይ እመለስበታለው)፡፡ አሜሪካና አጋሮቿ አፍሪካን ቀጣይ አፍጋኒስታን ማድረግ እንጂ በሞኖፖል ሊይዙት የሚፈልጉትን የክፍለ ዓለሚቱን ተፈጥሮ ሃብት መነካካት እንደ ብሔራዊ ደህንነት ስጋታቸው ነው የሚቆጥሩት (በአፍሪካውያን ለአፍሪካውያን ቢሆንም)፡፡ የቀድሞ የአሜሪካ የደህንነት አማካሪው የኪሲንጀር ሪፖርት፡ የብሔራዊ ደህንነት ጥናት ሜሞራንደም 200 (NSSM 200) ይመልከቱ፡፡
ፍሪሜሶን መሪዎች ከምእራባውያን “ወንድሞቻቸው” ጋር በመጣመር የአፍሪካን ሕዝብ ነጻነት እንዳያገኝና ከተፈጥሮ ሃብቱ ተጠቃሚ እንዳይሆን ላለፉት ሃምሳ ዓመታት በላይ ሲበዘብዙት ኑረዋል፡፡ አሁንም አፍሪካ በውጭ እዳ እና ጭቆና ተቆልፋ ትገኛለች፡፡ ሜሶኖቹ የባንክ ሂሳባቸውን እያደለቡ ለአፍሪካውያን አምባገነን “ወንድሞቻቸው” መዓርጎች እያከፋፈሉ ቅኝ አገዛዙን አስቀጥለዋል፡፡ ጆሞ ኬንያታ ነጮች መጽሐፍ ቅዱስ ለአፍሪካውያን ሰጥተው አይናችንን ጨፍነን ስንጸልይ መሬቱን ሁሉ ወሰዱት ብሏል ይባላል (ኢትዮጵያውን ቀድመን መጽሐፉን ስለያዝነው ሰጥተው የነጠቁን መሬት የለም፣ ያደረጉትም ሙከራ ከሽፏል)፡፡ ሆኖም ግን ለአፍሪካውያኑ የሜሶን ሽርጥ፣ ሜዳልያና ምልክቶች እያሸከሙ በእጅ አዙር እየገዟቸው ይገኛሉ፣ ይህን ይመስላል ፓን-አፍካዊነት፡፡ ይህን በመሰለ ሁኔታ ነው አንድ አፍሪካ እንዲመጣ ድጋፍ የሚያደርጉት ይህ ደግሞ ለነጻነት ሳይሆን ለባርነት ነው፡፡
“ሃራምቤ”መዝፈን ለመከልከልና የመበደል ስሜት ያወዳጃቸው አፍሪካውያንን ለማጣጣልና አትተባበሩ፣ በጠረጴዛ ዙርያ አትመካከሩ ለማለት አይደለም ይህ የአደባባይ ሚስጥር በግልጽ የቀረበው፣ ይልቁንም በፕሮፖጋንዳ የታወረውን ሕሊናችንን ክፍት አድርገን ሁኔታውን እና አስተሳሰባችንን እንድንፈትሽና መጪውን ትውልድ ለባርነት ሰንሰለት አሳልፈን እንዳንሰጥና ሙት ወቃሽ እንዳናደርገው እንድንጠነቀቅና አካሄዳችንንና ምርጫችንን እንድናርምና መሪዎቻችንንና ፖለቲከኞቻችንን ደግሞ ይህንኑ እንድናሳውቅ ነው፡፡

የአለም ባንክ እና ኢትዮጵያ ውዝግብ ውስጥ ገቡ

$
0
0

ላለፉት 20 አመታት ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር ከሞላ ጎደል ጥሩ የሚባል ግንኙነት የነበረው የአለም ባንክ በሀይል ከሚፈናቀሉ ዜጎች ጋር በተያያዘ ከፍተኛ ውዝግብ ውስጥ መግባቱ ታውቋል….

ሂውማን ራይትስን ጨምሮ ሌሎች አለማቀፍ የሰብአዊ መብቶች ተከራካሪ ድርጅቶች የኢትዮጵያ መንግስት በጦር ሀይል በመታገዝ ከ45 ሺ በላይ የጋምቤላ ተወላጆችን በግዴታ ማስፈሩን ተቃውመው ነበር።

የአለም ባንክ አንድ ገለልተኛ ቡድን በማቋቋም ክሱን ለማጣራት ባለፈው ጥቅምት ወር እንቅስቃሴ የጀመረ ሲሆን፣ የኢትዮጵያ መንግስትም ከአጣሪ ቡድኑ ጋር እንደማይተባበር ይፋ አድርጓል።

የጠቅላይ ሚ/ር ሀይለማርያም ደሳለኝ ቃል አቀባይ የሆኑት አቶ ጌታቸው አረዳ ከአጣሪ ቡድኑ ጋር እንደማይተባበሩ ዘገባውን ላወጣው ብሉምበርግ ገልጸዋል። “ከአለም ባንክ ጋር እንተባበራለን

ነገር ግን አለም ባንክ ካቋቋመው አጣሪ ኮሚቴ ጋር አንተባበርም” ብለዋል ቃል አቀባዩ።

የአለም ባንክ አጣሪ ቡድን በመጀመሪያ ሪፖርቱ ባንኩ የሚሰጠው ገንዘብ ዜጎችን በሀይል ከማፈናቀል ጋር የሚያያዝ መሆኑን ማመልከቱ የኢትዮጵያን መንግስት ሳያስቆጣ አልቀረም።

የኢትዮጵያ መንግስት አጣሪ ቡድኑ በኢትዮጵያ ላይ የፕሮፓጋንዳ ዘመቻ ከጀመሩት ከእነ ሂውማን ራይትስ ጋር ግንኙነት አለው ይላል።

አንድ የሰብአዊ መብት ድርጅት ተከራካሪ የአለም ባንክ አባል የሆነ አገር ባንኩ ካቋቋመው አካል ጋር አልተባበርም ማለቱ ያልተጠበ ነው በማለት ለብሉምበርግ ገልጸዋል።

የአለም ባንክ ” አትጠይቁኝ” የሚለውን የኢትዮጵያን መንግስት ከዚህ በሁዋላ ሲረዳ አይታየኝም በማለት ባለስልጣኑ አክለዋል።

አትዮጵያ አምና ብቻ 3 ቢሊዮን 5 መቶ ሚሊዮን ዶላር ወይም ከ60 ቢሊዮን ብር ያላነሰ ገንዘብ በእርዳታ አግኝታለች።


ይድረስ ለዶ/ር ፍቅሬ ቶለሳ ጂግሳ፦ “ዘመድ መስላ ቀርባ አሞራ ዶሮ በላች”

$
0
0

???????????????????????????????

ያጀማል (B.B)  ሰሞኑን ለአንዱ የኦዲኤፍ አመራር አባል ብለው የጻፉትን ደብዳቤ በአንድ ድረ-ገጽ (ዘ-ሐበሻ) ላይ ለማንበብ እድል ገጥሞኝ ነበር። ደብዳቤውፕ የተላከለት ባለቤት ቢኖረውም የደብዳቤው ይዘት ግን በኦሮሞ ህዝብ ላይ ያነጣጠረ በመሆኑ እንደ አንድ የኦሮሞ ታጋይና ብሄረተኛ ምላሽ ልሰትዎት ተገድጄ ብእሬን አነሳሁ።(ሙሉውን በPDF ለማንበብ እዚህ ይጫኑ) Short URL: http://www.zehabesha.com/amharic/?p=3758


Viewing all 931 articles
Browse latest View live