Quantcast
Channel: Ethio Andinet ኢትዮ አንድነት
Viewing all articles
Browse latest Browse all 931

በአማራ ክልል ሰሜን ወሎ ዞን በ11 ቀበሌዎች የተሰበሰበ የሰብል ክምር ላይ ከፍተኛ የእሳት ቃጠሎ ደረ

$
0
0

በዋድላ ወረዳ በተለያዩ ቀበሌዎች ምክንያቱ ባልታወቀ የእሳት ቃጠሎ የ154 አርሶ አደሮች የሰብል ክምር ከታህሳስ 5 ቀን 2017 ዓመተ ምህረት ጀምሮ መቃጠሉ ተነገረ። በወረዳዉ ነዋሪ የሆኑ አንድ ግለሰብ ለዶቼ ቬለ እንደተናገሩት « ትናንት ከእኩለ ቀን በኃላ ምክንያቱ ባልታወቀ ሁኔታ እሳት በመነሳቱ አዉድማ ላይ የነበረ አራት እህል ተቃጠለብኝ » ብለዋል።

በዋድላ ወረዳ 770የሚደርሱ አባዉራ እና እማዉራ አርሷደሮች በቃጠሎዉ ጉዳት እንደደረሰባቸዉ ተነግሯል። በሰሜን ወሎ ዞን ዋድላ ወረዳ ምክንያቱ ባልታወቀ የእሳት አደጋ በሰብል ላይ ጉዳት የደረሷል ከ4560 ኩንታል በላይ ምርት ደግሞ እንደወደመ ተነግሯል።

ትናንት ከእኩለ ቀን በኃላ የደረሰዉ ቃጠሎ እስከዛሬ ከደረሱት አደጋዎች ከፍተኛዉ መሆኑን የወረዳዉ ግብርና ጽህፈት ቤት ኃላፊ ተናግረዋል።


Viewing all articles
Browse latest Browse all 931

Trending Articles



<script src="https://jsc.adskeeper.com/r/s/rssing.com.1596347.js" async> </script>