Quantcast
Channel: Ethio Andinet ኢትዮ አንድነት
Viewing all 931 articles
Browse latest View live

አጀንዳን እያስቀደሙ ማዘናጋት ከተጠያቂነት አያድንም!

$
0
0

አልፎ አልፎ የጉዞን ጎዳና መመርመር ከብዙ ስህተት ያድናል። ግምገማ -እንደሚሉት የ”ለምን አልታዘዝክም” -“ለምን የብዝበዛው አካል/አፋኝ አልሆነክም”…. ውጠራ ሳይሆን የሕዝቡን የእርምጃ መስመር በተቻለ ለመጠበቅ- ከላስፈላጊ—–ፍጆታም ለመላቀቅ የሚበጅ መሆኑን በማጤን ነው።

በቀደመ መጣጥፍ ስርአቱ አሁን ሞቷል የሚንቀሳቀሰው በበበድኑ ነው የሚል ታማኒ የሆነ ሓሳቦች ተጨብጦ ነበር። ስርአቱ በቁሙ ሙት ነው ግን ዘለቀ ስንል ሊያዘልቁት ያበቁትን ጥቂት ነጥቦች በጥቅሉ ተቀምጠውም ነበር።

አንድ ሀቅ ይፋ መውጣት አለበት ከተባለ መነገር ያለበት አብይ ጉዳይ-የሆነውስ ሆነ- ትላትናና ዛሬ የህዝቡን ትግል የሚመራው ማነ ነበር-ዛሬስ ማነው ብለን መጠየቅ የግድ ነው። እንደ አነጋገርም ስልት “እርሱ አጀንዳ አለው” “የአንተ አጀንዳ ምንድር ነው” “እርሱ የሚያራምደው የራሱን አጀንዳ ነው” ይባላል። በእርግጥም የዚህ ጥቆማ አጀንዳ “አጀንዳ” እንደመሆኑ ሁሉም የራሱ አጀንዳ አለው። የሚያራምደውም አጀንዳውን ነው። የራስን አጀንዳ የሁሉ ማድረግ ደግሞ በክፉም በደጉም አንድ እርምጃ አስቀድሞ ማስተዋልን ያመለክታ። አጀንዳን አጀንዳ አድርጎ መነሳቱም ትርጉሙ እዚህ ላይ ነው። ብዙ እንደታዘብነውና አሁንም እየተካሔደ እንዳለው የህዝቡን አረማመድ ትግልም ትንቅንቅ የሚመራው ማን ነበር ስንል የምናገኘው ምላሽ በእውነቱ-ባብዘኛው የህዝቡ እንቅስቃሴ ይመራ የነበረው አሁንም የሚመራው የመሰሪው ስርአት እንጂ በሕዝቡ እንዳልነበረ መተማመን መልካም ነው። እድሜ ለእከሌ እንዳንል ሞቷልና የተንኮሉ ምንጭ እንዴት እያንዳንዲቷን እርምጃ በቅጥ እያስተዋለ ሲሸርብ እንደነበረ በቂ ግንዛቤ የወሰደ እዚህ ላይ ግር አይለውም። በመሰረቱ ሕዝብ ወይንም ድርጅቶች አጀንዳ አልነበራቸውም አልተባለም-ተጠለፈ እንጂ-እንቀጥል።

ከየት እንጀምር? ሰለቸን እስከምንል ያሰለቸንን አረማመድ መቃኘት ታሪክ መጻፍ አይነለምና -ይህ ሁሉ ሲሆን የት ነበሩ የሚያሰኝ ሂደት ሆኖ እናገኘዋለን። ትንሽ ትዕግስትን የሚጠይቅ ቁምነገር።

አጀንዳ ስንል አሳቻነቱን፤ጠላፊነቱን፤ሳይቀድሙኝ ልቅደም ባይነቱን፤ ጩኸቴን ቀሙኝነቱን፤መሰሪነቱን ብልጣብልጥነቱን ምን የማይባል አለ -የሚደረደረው የጨለማ አስተሳሰብ ሁሉ እውን የሚሆንበት አረማመዱን ለመጠቆም ነው። ትንሽ ወደሗላ መለስ ብለን የተቻለንን እንናዘዥ-ወይ ፍርጃ!በቁም ኑዛዜ! እስኪ እንደወረደ እንበል።

የኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት(ባጭሩ አራት አመታት)

የሕዝብ ትግል በጠነከረበት-በቅርብ ለሚያስታውሰው- ስርአቱ የሁለት ባላንጣዎችን ውክልናና ሀላፊነትን ይዞ ሕዝብን በሚሞግትበት ወቅት የኢትዮ-ኤርትራ የእልቂት ጦርነት ሲከሰት ሕዝብን በብሔራዊ ስሜት አንቆ አገር አድን አጀንዳ ተሰመረለት። በዚህ ጊዜ “ከባደሜ መለስ ወደመለስ” -በቀላሉ ይችን ጦርንተ ጨርሰን አናንቀዋለን ተባለ። ሁሉም በተቀየሰለት ቦይ መፍሰስ ጀመረ። እዚህ ላይ ብዙ አርቆ አስተዋዮች-የማያዋጣ-የትግልን ስልት አጨናጋፊ”አጀንዳ” ለመሆኑ አበክረው ቢመክሩም አፈ ጮሌው ባገር ክህደት ከመወንጀል አልተቆጠበም ነበር። የአሰብንም ጉዳይ ያነሱ “ጦረኞች—“ ተባሉ-ለራሳቸውም መከፋፈል መሰረትን ጣሉ-ስንተ አመት?-ባጭሩ አረት አመታት ተሸመቱ። ሕዝብም አለቀ። ከወንጀልም ነጻ!!ያልጄርስን ውዝግብና የህዝብን “ድል አደረግን ሰልፍ ውጡን” ማሞኘት ጨምሮ።

ምርጫ-(ሶስት አማተት ከፊት -አራት አማታት ከሗላ)

ይህ በእንደዚህ እንዳለ ነብረ የ2005 ምርጫ አጀንዳ ሆኖ ሶስት አመት ከምርጫው በፊቱ -ሁለት አመት ከሁዋለው ሲያራኩት የከረመው። ባናሳው አምስት አመት። ከምርጫው ሶስት አመት አስቀድሞ፤ የምርጫ ቦርድን፤ ደንብና ህግን፤የሚዲያ አከፋፋልን፤ታዛቢ ወዘተ ወዘት፤ ምርጫ እንግባ አንገባም ሲባል ካለ በቂ ዝግጅትና የሁሉንም ፈቃደኝነት ባላካተተ መልኩ ወደ ምርጫ ዘው ተባለ። በጦርነቱ አንድ ሆነን ነበር እስኪ ተንፍሱ አይነት በተገኘችው ቀዳዳ የሕዝብ ድል ሲጠናቀቅ፤ በማግስቱ አሸንፌአለሁ ብሎ አውጆ ከዚየም ምድር ቀውጢ እንደሆነች አናስታውሳለን።

ነገሮች ተደማምረው አሁንም የሕዝቡ ድምጽ ይከበር በሚል አጀንዳ በተነሳ ውዝግብ ፤አስቀድሞም ሕዝብ እንዳለቀ፤ወደስር እንደተጓዘ ስናስብ አጀንዳዎችም መልክ እየቀየሩ አንደመጡ እናስተውላለን። ፓርላማ ለመግባት ቅድመ ሁኔታዎች ወዘተ። እዚህ ላይ ከሕዝቡ ድምጽ ይከበር ወደ ገዳዮቹ ለፍርደ ይቅረቡ ከዚያም የታሰሩት ይፈቱ የሚሉት ሁሉ በስርአቱ መሰሪነት የቀረቡ በየወቅቱ የሚፈለፈሉ የግፊት አጃንዳዎች እንጂ ሕዝቡ አስቦ ያቀዳቸው ጉዞዎች አልነበሩም። በቀላሉ አጀንዳዎች ተሰመሩለት።

የታሰሩት ይፈቱ-(አራት አመታት ሙግተ 2+2)

ይህ በዚህ እንዳለ አንድ ጊዜ ከታች ሕዝቡን ሁሉ እስር ቤት ለማስገባት ሞክሮ አንዳላዋጣው ሲረዳ፤ያሰረውን አስሮ አመራሩን በ አጠቃላይ ወደ እስር ሲከት ከላይ የተዘረዘሩት ሁሉ ተረስተው አገር ድፍን-አገር፤ ውስጥ ውጭ “የታሰሩት ይፈቱ” በሚል ሁለት አመት በላይ ሕዝብን በሙግት አጀንዳ ጸና። ምርጫው ተረሳ፤ድምጽ ተሰረቀ፤የተገኙትም ድምጾች ተነጠቁ፤ ነፍሰገዳይ በነጻነት ናኘ። አጀንዳ ተቀየረ።

የቅንጅት አመራርና ሕዝብ እስርቤት ባሉበት ጊዜ ነበር ድርጅቶችን መከፋፈል፤ ወደራሱ ማስጠጋት(ክሎኒንገ)አፋኝ ሕጎችን ማውጣት የተረፉትንም ድርጅቶች እንዳይነቀሳቀሱ ጠፍሮ የያዘበት ሁኔታ የተፈጠረው። የራሱንም ወንጀል አሳልፎ -ባገር ክህደትና -በዘር ማጥፋት ወንጀል ወዘተ አመራሩን ሌሎችንም ወነጀለ። ጩከቴን ቀሙኝ!-አሁን ማን አገርን እንደከዳ ማን ዘር እንዳጠፋ ሐቁ ገሀድ ሊወጣ!!

በጊዜው አጀንዳ ባጀንዳ እየለዋወጠ -ሲፈልገው ፍንጂ አፈንድቶ በማጯጯህ ሲያሰኘውም የፈጠራ ወሬውን እየደለቀ ለ2010 ምርጫ ከበቂ በላይ ዝግጅቱን አጠናቀቀ። በ2005 ስለ 2010 ምርጫ ማሰብ ወንጀል ነበር ማለት ማጋነን አይሆንም። የሶሟያ ጦርነት(ሁለት አመታት)

ድምጽ ሰረቆ፤ሕዝብን አፍኖ፤በቅንጅት አመራርና በሕዝብ መታሰር አገራቀፍና አለመቀፍ ውግዘት የተከናነበው የተንኮለ ስርአት በዚህ ወቅት ያደረገውና መዘንጋት የሌለበት ትልቅ ሸፍጥ-ቀልጠፍ ብሎ ከምእራቡና ተሰላፊዎቹ በበለጠ ግንባር ቀደም ሆኖ ሽብርተኝነትን እንዋጋለን ብሎ ወደ ሶማሌ መዝመቱ ነበረ። የሶማሊያም ጉዳይ ትልቅ አጀንዳ ሆነ! አንደገናም የብሔርን ስሜት ሊቀሰቅስ ሊያሰልፍም ሞከረ፤ሕዝቡ ተምሯልና ልጆቹም በእስር ላይ ናቸውና አልተሳካም። አላማና ውጤቱ ሲጤኑ-አላማው የታሰሩት እንዲረሱ ማዘናጋት ውጤቱ እልቂትና ውርደት ነበሩ። የገባበትን የወጣበትንም ታዝበላልና!። አገርን ካደጋ መከላከል ሌላ ወረራ ሌላ። የአገር ጉዳይ ሌላ፤ የሌሎችን ጥቅም በሕዝብ ልጆች ደም ማስከበር ሌላ። በወቅቱም የታሰሩት ለጊዜውም ቢሁን ተረሱ-ሁለት አመታትመ ተሰቃዩ። በሕዝብ ትግል ቢፈቱም የተነሱበትን አላመ አዳፍኖ ጥያቄው የህልውናና ከስር የመጀመር ጉዳየ ሆነ። እንደለመደው -በጎን ለሚቀጥለው እርምጃው ማውጠንተን መሸረቡን ቀጠለ።

በዚህ ወቅት ነበረ እህት ብርትኳንን ወደ እስር የሰደደዳት-ተከታይ አጀንዳ ይበሉ። ወ/ሮ ብርተኳንን ለማስፈታት እንዲሁ ሌላ ሙግት፤ እርሷን አፈነ፤ምርጫውም ደረሰ- እንደ ጩሉሌ ነጥቆ 99.6% ድል ተነገረ። ቤት ስራውን ጠንቅቆ በተገቢ ሠርቷል። ከስህተቱ ተማረ አምስ አመት ባፈና ደከመ፤ድሉን ነጠቀ አደባባይም ተደሰኮረ። አይን ያወጣ ፍጹም ለታሪክ ለተውልድ ለትዝብት የሚያበቃ ጭፍን ይሉኝታቢስ መሰሪነት።

ዘግይቶም ድርቅ ተከሰተ ብዙ ሙግት። በዚህም ህዝብን ለማትረፍ በሚደረገው ጥረት ዋና የተባሉ የሕዝብ የትግል መስመሮች ደብዝዘው ድርግቶች ታፍነው ተዳክመው- ደርግ ተቃዋሚዎቹን ጸት እንዳሰኘ -ለዚህም መሰሪ ስርአት አፈናው ሰራለት ትንሽ ተንፈስ አለ የተረፉትን ተቃዋሚዎች መለቃቀም ጀመረ።

ምንም የማያልቅበት ተንኮለኛ-ለስሙ መጠሪያ ግድብ ብሎ ተናሰ። ግድብ ሌላ አጀንዳ። ስንት አመት አለፈ በግድብ ሙግት። የሕዝቡ ልጆች ጸረ-ልማት የሆኑ ይመስል ካለአቅም በተጀመረው አወዛጋቢ የግድብ ስራ ብዙ ውጣውረድ ተነሳ፤ እስከ ውጭም ጎዳዩ ተዛምቶ የገንዘብ ቃርሚያው ተቃውሞ በዝቶበት አሁን ባለበት አለ። ሞተ አለ፤

ሰውየው ታመመ-ሌላ አጀንዳ። ሞተ አለ ብዙ ወራት ተወራ፤ ይቀበር አይቀበር ብዙ ወራት፤ሙዝየም-ሙዚሊየም ነው ምንድር ነው ይገባል አይገባል አሁንም ሌላ ሌላ የሙግት አጀንዳ ——ፍጆታ።

የስልጣን ክፍፍል ሙግት፤

ትንሽ ቆይቶ የሰውየው እሬሳ ሳይደርቅ የስልጣን ክፍፍል ሙግት-አዲስ አጀንዳ። አዲሱ ሰው መጣ፤ አዲስ መነጋገሪያ ሆነ። ሰውየውም በስርአቱ ተጠፍሮ ለውጥ የውሀ ሽታ ብቻ ሳይሆን አራሱ የ“ራኢአይ/ቅዠት” አራማጅ ተብሉ ተኮፈሰ።

ይህ በዚህ እንዳላ ነበር ቀደም ብሎም ስርአቱን እንደ ግለሰብም እንደሺህም ሆነው ለመብት ለነጻነት ቆመው ሲታገሉ የነበሩት አነ እስክንድር–አንዱአለም ወዘተ-የታፈኑት የቀሩት ሸሹ-ሌላ አጀንዳ። አኔም አጃንዳ ማለቱ ደከመኝ፤አሰልቺ ነው። ከአንድ ወጥመድ ወደሌላ ወጥመድ ካንድ አዘቅት ወደ ሌላ አዘቅት-በተለያየ መለኩ። አሁንም ካለፈ ልምዱ -ብዙም መነጋገሪያና ተስፋ ሰጭም ባይሆን -የክልል ምርጫ ተባለ እንደተለመደው ተጠለፈ። ሐይማኖትንም በሚመለከት-ያመራሩንና ገዳማትነ አያይዞ ለብዙ ጊዛ ውጣውርደ እስካሁን እየቀጠለ ያለ መሆኑን ስንመለከት-ሌላው አነጋጋሪ የሐይማኖት ሙግት አጀንዳ እንደሆነ መጣዘብ መልካም ነው።

የሕዝብ ማፈናቀል፤

የሰውየውን ማጣጣር-ሞት አመላክቶ የሕዝቡ መነሳሳት ግልጽ በሆነበት ወቅት፤አደገኛ አካሄድ ቢሆንም -ለጊዜውም ሕዝብን በማንጫቻት የሰራላቸው አንድ አስከፊ ነገር ተከሰተ። ባገሪቱ አደገኛ አዝማሚያን የቀሰቀሰ ከሶስቱም ማእዘናት ሕዝብ ማፈናቀል። ሌላ መዘዘኛ አጀንዳ። በሔደቱም አዲሱ ሰው እግሩን ተከለ የመሰለውን መስሎ ወጣ። የመረጋጋት ስሜትን የፈጠሩ መሰላቸው ነገር ግን ምን ምሰው እንዳወጡ በቅጡ የተረዱት አይመስልም። በዚህም እስከዛሬ ሲያራምዱት የቆዩት የዘረኝነት ደባ ገሃድ ወጣ። አራስን የሚለበልብ አጀንዳ። ሟች ይህን እንዴት እንዳመለጠ ትዝብት ይወሰድ። ጭልጥ ያለች ውሸትን እወነት አድርጎ መናገር ይችልበት ነበር። በዚህም ከዚህ የቀደመውም የሕዝብ መሰረታዊ ጉዳይ ሁሉ ተረሳ።

ሙስና፤

አሁን ደግሞ የተያዘው አጀንዳ ሙስና ሆኗል። ሟቹ- የስርአቱ አማራማጆች በሙስና የተዘፈቁ መሆናቸውንና ከ50% በላይ ስለሆኑ መዋጋቱ አንደማያዋጣው ስለተረዳ -አልፎም ስርአቱ የቆመበትን ምሰሶ የሚያናጋ በመሆኑ ሳይነከው ተሰናበተ። የብልጠት አረማማድ ነበረ። የሚያዋጣውንና የማያዋታውን ያውቃል። አዲሱ ሰው ምን ውስጥ ተዘፈቀ? ሙስና የስርአቱ ስም እንጂ የአንድ ግለሰብ ወይንም የተወሰነ ባለስልጣን መስሪያቤት ችግር ብቻ አይደልም። ከሙስና ለመጽዳት ወይ 50ዎቹን ስርአቱ ይጨርስና ለሕዝቡ የቀረውን ይሰጥ ወይም ይሰናበቱ። እዚህ ላይ ምን ተረሳ -የሕዝብ መፈናቀል። ጥሩ ሙከራ።

ይህን ስርአት ከሙስና አጸዳለሁ ማለት ዘበት ከዘበትም ዘበት ነው-አያችሁ አጀንዳ -በል በል የሚያሰኝ፤ አጀንዳ ማለት ይህች ነች።በተግባር።

ይሀን ሁሉ ሲያደርግ ሶስት አነኳር ቁም ነገሮች መጠቀስ አለባቸው። ለዚህ ሁሉ -አላማው ግልጽ ነው፦

1. ማዘናጋት-አላማን ማሳት፤ 2. ከተጠያቂነት ማምለጥ-በእያንዳንዱ አጀንዳን መቀያየር ከስንት ወንጀልና ተጠያቂነት እንዳመለጠ ግልጽ ነው፤ 3. ተቃዋሚን /ሕዝብን ማዳከም፤ 4. ፈጥኖ ጥቅምን ማግበስበስ፤ 5. ብሎም የስልጣን እድሜን ማራዘም። ከሆነው ሁሉ፤የቱ እንተሳካለትና የቱ እንደከሸፈበት አንባቢው ይፍረድ።

እንዲህ እንዲህ ሲል ነበር 22 አመታት ሕዝብን ሲሞገግት ሲመሰጥር ሲያምስ የከረመው። መቃወምም አጀንዳ ሆነ- ሁሉም የታየውን ዘርዘር አድርጎ ማስቀመጥ ሀላፊነት አለበት- በዚህ ረገድም ብዙ ተብሏል። ባንድ መልኩ የስርአቱ ምንነት የተረጋገጠው ይህን ንቅዘቱን በማጋለጥ ረገድም ነበር፡

ለማጠቃለል ከዚህ ምን እንማራለን? በዚህችው በመጨረሻ የእስትንፋስ ጊዜው፦

1. የ ስርአቱን አዘናጊ አጀንዳ ጠንቅቆ መረዳት፤ 2. ይህ ያንተ አጀንዳ እንጂ የሕዝቡ አይደለም ማለት፤ አለማጀብ፤በመንገዱም አለመሔድ፤ማምከን፤ 3. ትኩረት ባለው የሕዝብ አጀንዳ ላይ መንቃሰቀስ፤ 4. የህዝብን የመሰረታዊ የዲሞከራሲ፤የነጻነት፡የመብት ጥአቄዎችን፤የአገርን ሉአላዊነት አንድነትና ዘላቂነት የሚመለከቱትን ጉዳዮች በማጉላት-የለውጥን ባቡር ጉዞ ማፋጠን።

ከዚህ -ከምናውቀው ከተማርነውና ካስተዋልነው አንድ ተጨማሪ ግንዘቤ እንደወሰድን ይገመታል። በዚህም የስርአቱን የወደፊት አጀንዳ አስቀድም መተንበይ ይቻላል። በሚገርም ሁኔታ የ2015 ምርጫን አንስተው ሕዝን ሊያንጫጩ እንደሚሞክሩ መገመት አያዳግትም። አንድ ታምር -እንበለውና- አንድ ነገር ካልመጣ ስርአቱ እንዲሁ በድኑን እየተንቃሰቀሰ፤ ሙቱን አየተንገዳገደ፤ አደጋ አያንዣበበበት እዚያ ሊደርስ አንደሚሞክር መገመት አያዳግትም። ለነገሩ መሰሪነት ጨርሳ ባትጠፋም ሳትሞት አልቀረችም። ለእነርሱም ሰዎች -ጊዜአቸው አስቀድሞ ያበቃ፤ በተዋሰ ጌዜ እንደሚንቀሳቀሱ፤ ጊዜና ሕዝብ እንደከዳቸው ሀይልም ትምክህትም ሸፍጥም አንደማያዋጣ ቢረዱና መንገዳቸውን ቢፈልጉ ከባሰ ሁለገብ ቀውስ መዳን ይሆናል ።

ይህም ሆኖ በየወቅቱ አዘናጊና አደናቃፉ አጀንዳዎች ቢደቀኑበትም -ሕዝቡ እንደተባለውም፦

በሰራው ወጨፎ በሰራው እርሳስ፤ ጥልያን ጠፈጠመ ዳግመኛ እንዳይደርስ!

ብሎ በገዛ አጀንዳው እተመታና እፍረትን ውርደትን እየተከናነበ እዚህ የድል ምእራፍ ላይ እንደደረሰ መጠቀስ አለበት። ሕዝቡ ምንጊዜም ባለድን ነው። ሕዝብን ዘለአለም ለማታለል መሞከርና -ለጊዜውም ቢሆን- ተላላነት ነው።

ለማጠቃለል-የኤርትራ ጦርንተ ተባለ ትረፉ እልቂት፤ውርደት። የአልጄርስ ስምምነት ድለ ነሳን ተባለ ባዶ ኳካታ ውርደት። ምረጫ ተባለ ሽንፈት። ወደእስር በሐሰት ክስ የገቡትመም ተፈቱ–ውርደት። የሶማሌ ጦርነትም ትረፉ እልቂት-ያለቀው ቁጠሩ እነኳ ሳይነገር-አሊ-ሽባውም አግር አውጠቶ ተጠናከሮ ጦርነቱን ቀጠለ። ድርቅ ተከሰተ-ድርቅና ረሃብ የቋንቋ አቃቂር መጣ-አንድም ሰው አልሞተም-ተባለ በቅርቡ በሶማሊያ ከ260፣000 ሕዝብ በላይ ማለቁን ተነገረ። አሁንም የምስራቁ ኢትዮጵያ ጉድ ተዳፍኖ አለ-ትልቅ መጪ ውርደት። ዳግም ምርጫ ተባለ-99.6% ውርደት። ሰውየው በሕይወት አለ ሲባል ተከረመ-ሰውየውም ሞተ። የሕዝብ ማፈናቀል ተሸረበ-የባሰ ውርደት የዘረኝነት ሴራ መጋለጥ። አሁን ደግሞ ሙስና ተባለ-ሲወተወት የነበረው የስርአቱ በዝርፊያ መንቀዝ በራሱ ኮሚሽን ይፋ መውጣት የባሰ ዝቅተት። ብዙ ሊጻፍ ሊነገር ይቻላል። ሕዝቡ ስርአቱን በአጀንዳው ካጠናቀቀው፤በራሱ አጀንዳ ቢራመድ ምንኛ የመከራው ጊዜ ባጠረች። ይህም ሲባል በሕዝቡ አጀንዳ ላይ ሳያሰልሱ ሲታገሉ በመጨረሻም የተናገሩት እውነት መሆሉን በተግባር በብቃት ያስመሰከሩ ብዙዎች እንዳሉ መጠቀስ አለበት።

ለቀባሪው አረዱት አይሁንና-ቁምነገሩ ሕዝቡ በስርአቱ አጀንዳ ሳይሆን በራስ አጀንዳ ስር መንቃሰቀስ አስፈላጊና ወሳኝ መሆኑን ማመልከት ተገቢ ነው። ስርአቱ ከእንግዲሕ የቀረው የቅዠት አጃንዳ ብቻ ነው። በዚህ መሄድ ደገሞ -በሌላው ቅዠት መቃዠት ነው የሚሆነው! ከእንግዲህም ቀልጠፍ ብሎ -አጀንዳህ ምድረ ነው ብሎ መጠየቅ ተገቢ ይሆናል። አግባብነት ያለው ተመራጭ አጀንዳ-የተባበረ የተቀናጀ እንቅስቃሴ ነው ቢባል ተገቢ ይሆናል! አጀንዳዎችን አጥንቶ መጓዝ ተገቢ ነውና!! እንቅስቃሴውም -ሲፈለግ የነበረውን አንድነት ቅንጅትና ሕብረት ሊያመጣ ይችላል።አንድነት ለእንቅስቃሴ፤እንቅስቃሴም ለአንድነት።

አጀንዳን እያስቀደሙ ማዘናጋት ከተጠያቂነት አያድንም!!!

ኢትዮጵያ በእግዚአብሔርና በጠንካራ ታጋሽ በሕዝቧ ተጠብቃ ትኑር!



ታሪክን የኋሊት፤ የአቶ መለስ ድንጋጤ!

$
0
0

እንግዲህ ይህ ከሆነ አመቱ ሆነ አይደለ… ቅዳሜም ቅዳሜ፣ እሁድም እሁድ ነው እና ምናልባት ካልተገናኘን… እንዳንረሳው፤ ከወዲሁ ቀኑን እንደሚከተለው እንዘክረው… (በቅንፍም ኤድያ እነ እንትናዬ ደግሞ ሊበሳጩብኝ ነው… (በሌላ ቅንፍ እንግዲህ ይቻሉት እኛ ስንቱን ችለነው የለ…))

e18aa0e189a0e189a0-e18c88e1888be18b8d-2

በመጀመሪያም፤ብስጭቴ

እኔ እኮ የምለው ሰው አይኑ እያየ የሰራውን ስራ እያወቀ ወደ አሜሪካ ለዛውም ወደ ዋሽንግተን ዲሲ ይሄዳል እንዴ!? እውነቱን ለመናገር እኔ አቶ መለስ ዜናዊን ብሆን ኖሮ ዲቪ እንኳ ቢደርሰኝ ሀገር ይቀየርልኝ እላለሁ እንጂ አሜሪካ አልሄድም። እነ ቻይና ባሉበት አለም እነ ሰሜን ኮሪያ በሚኖሩበት ምድር ሰው እንዴት ወደ አሜሪካ ይሄዳል? (ይቅርታ ሰው በሚል የተጠቀሱት ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትራችንን ነው)

ዋናው ወሬ፤

የሆነው ሆኖ ትላንት በዋሽንግተኑ ስብሰባ አቶ መለስ ዜናዊ ሲመጡ ከውጪ ያለውን የተቃውሞ ድምፅ በመከራ አልፈው የስብሰባ አዳራሽ ውስጥ ከገቡ በኋላ ደግሞ ጋዜጠኛ አበበ ገላው ተሰብሳቢው ፊት፤ ከውጪ ያለው ህዝብ በሰላማዊ ሰልፍ፣ እንዲሁም አዲሳባ ያለው ህዝብ ደግሞ በሰላማዊ ዝምታ በሆዱ ምን እያላቸው እንደሆነ ነጥብ ነጥቡን ነግሯቸዋል። እንደው ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነውብኝ እንጂ “እስከ ዶቃ ማሰሪያቸው ድረስ ነግሯቸዋል!” ብል የበለጠ ይገልፀዋል መሰል!

የጋዜጠኛ አበበ ገላው ድርጊት ከዚህ በፊት ጆርጅ ቡሽ ላይ ጫማ ከወረወረው ጋዜጠኛ ጋር የሚቀራረብ ይመስላል። እንደውም በቪዲዮ እንዳየኋቸው ጠቅላይ ሚኒስትሩ ላይ የደረሰው የቅስም ስብራት “በጫማ መመታት በስንት ጣዕሙ!” ያሰኛል።

ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ በስፍራው የተገኙት በባራክ ኦባማ ጋባዥነት ከቡድን ስምንት ሀገሮች ጋር ስብሰባ ሊቀመጡ እንደሆነ ባለፈው ግዜ አውርተናል፤ ከቡድን ስምንቱ ስብሰባ አንድ ቀን ቀደም ብሎ ታድያ  “ግሎባል አግሪካልቸር ኤንድ ፉድ ሴኪዩሪቲ” በተባለው ስብሰባ ላይ ቁጭ ብለው እንደተለመደው ፐርሰንታቸውን እየጠቀሱ ሳለ ድንገት አበበ ገላው፤ “መለስ ዜናዊ…” ብሎ ሲጠራ ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትራችን “የደነገጡት መደንገጥ… ከአንድ ታጋይ የሚጠበቅ አይደለም” ሲሉ አስተያየት የሰጡ አሉ። እኔም እንዳየሁት ጆሯቸውን ማመን አቅቷቸው “የድርጅቴን ብቅል እየፈጨሁ ነው…” ብለው ሊያልፉት የከጀሉ ሁሉ መስሎኝ ነበር።

ብቻ በጣም ክው ማለታቸውን ፊታቸው አሳበቀባቸው። ከዛ እንደምንም ተረጋግተው…“ሰበንቲ….ፐርሰንት” ብለው ንግግራቸውን ሊቀጥሉ ሲሉ የጋዜጠኛ አበበ ገላው ድምፅ ከመጀመሪያው ከፍ ብሎ “መለስ ዜናዊ ኢዝ ኤ ዲክታተር…” ማለቱን ቀጠለ አሁን ትንፋሽም ቃልም አጠራቸው። አስተያየታቸው “ምነው ዛሬ እግሬን በሰበረው!?” የሚሉ ይመስላሉ። ግን እንደምንም ብለው ለመቀጠል ሞከሩ። ድምፃቸውን ከአበበ ድምፅ ከፍ ለማድረግ እየጣሩ “ሰበንቲ…ፐርሰንት” አልቻሉም። “ምን ላይ ነበር ያቆምኩት…?” ለማለት የፈለጉ ይመስላሉ ባልንጀሮቻቸውን ቃኘት ቃኘት አደረጉ። እነርሱቴ “ራስህ ተወጣው!” ሳይሏቸው አይቀሩም… አበበ ቀጥሏል። “መለስ ዜናዊ ኢዝ ኤ ዲክታተር….” አሁን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከኛ በላይ ድምፅ ላሳር በሚመስል መልኩ ከአበበ በላይ ጮክ ብለው እና ድፍረታቸውን አሰባስበው፤ “ሰበንቲ ፐርሰንት ኦፍ ዘ ፖፕሌሽን ኢን አፍሪካ….” አሉ። ብሽሽቅ ነው የሚመስለው እንጂ የንግግራቸው አካል አይመስልም!

ድጋሚ አቋረጡ አበበ ግን የሚያቋርጥ አይመስልም በእንግሊዝ አፍ “እስክንድር ነጋ እና ሁሉም የፖለቲካ እስረኞች ይፈቱ፤ ምግብ ያለ ነፃነት ዋጋ የለውም! መለስ ዜናዊ አምባ ገነን ነው!” ብሎ እንቅጩን ነገራቸው። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ቁና ቁና ሲተነፍሱ ኮምፒውተሬን አልፎ ሁሉ ይሰማ ነበር። በሆዴ “ይበልዎት አይሂዱ አላልኮትም ነበር!?” ብልም እውነቱን ለመናገር ግን አንጀቴን በልተውታል።

አቶ መለስ ከትላንትናው የበለጠ  ቅዳሜ ደግሞ ሌላ ተቃውሞ እንደሚጠብቃቸው ጭምጭምታ ሰምቻለሁ። ከዋሽንግተን ዲሲ ወጣ ብሎ የሚገኘው ካምፕ ዴቪድ ድረስ ህዝቡን ለማመላለስ የተሰናዱ አውቶቡሶች መኖራቸውን የደረሰኝ ጭምጭምታ ያስረዳል።

እኔማ የሚሰማኝ አጣሁ እንጂ ቀድሞውኑም ይሄ ስብሰባ ይቅርብዎ ብዬ ነበር። ይሄን ግዜ እርሳቸውም በሆዳቸው “ምነው ምነው ምነው በቀረብኝ” የሚለውን ሙዚቃ ሊያዜሙ እንደሚችሉ እጠረጥራለሁ። ምንም ጠቅላይሚኒስትር ቢሆኑ ሰው አይደሉ እንዴ…!? ምክሬን ባለመስማታቸው መፀፀት ካልቻሉ እውነትም ሰውየው ጠቅላይ ሚኒስትር እንጂ ሰው አይደሉም ማለት ነው!

ይህንን የጠቅላይ ሚኒስትሩን ቅስም ስብራት የሰማ አንድ ወዳጄ “ይሄኔ ጥሩ አዝማሪ ቢገኝ ይቺን ግጥም በል እስቲ ተቀበል ብሎ ማቀበል ነበር” ብሎኛል…

“አፄ መለስ ዜና እጅግ ተዋረዱ

ምግብ ብለው መጥተው አንጀት በልተው ሄዱ

አንተ አበበ ገላው እንደምን ቻልካቸው

መለስ ቀለስ ሲሉ ጎንበስ አረካቸው”

(አረ ጎበዝ ዜማ ፈልጉና ይችን ነገር ነጠላ ዜማ አደርገን እንልቀቃት በስንት ግዜ የተገኘ የግጥም አዚምን እንጠቀምበት እንጂ!)

በነገራችን ላይ ከዚህ ጋር በተያያዘ አንዳንድ የህብረተሰብ ክፍሎች እንደሚሰጡት አስተያየት ከሆነ አቶ መለስ አዲሳባ ሲገቡ ወይ በጭፈራ ሞቅ ደመቅ አድርገን ካልተቀበልናቸው ወይ ደግሞ ለጥ ብለን ተኝተን ካልጠበቅናቸው በብስጭት ሊጨርሱን ይችላሉ ሲሉ ስጋታቸውን ገልፀዋል።

በመጨረሻም

ኦባማ ግን አራዳ መሆናቸው ነው ሰውየውን ጠርተው ልክ ልካቸውን የሚያስነግሯቸው!? የምር ሽምቅቅ አደረጓቸውኮ! (እኔ ልሸማቀቅ… ልላቸው ነበር አሁንማ አንዴ ጀምረውታል… ይወጡት እንግዲህ!)

source. abetokichaw.com


የኔልሰን ማንዴላ ፊልም የመጨረሻ ቀረፃ ኢትዮጵያ ውስጥ ሊደረግ ነው

$
0
0

‹‹ዘ ማንዴላስ ገን›› በሚል ስያሜ የሚሠራው ዘጋቢ ፊልም በደቡብ አፍሪካው ‹‹ዲቪ8›› እና በእንግሊዝ ‹‹ቢር ኸርት ሊሚትድ›› የፊልም ኩባንያዎች ትብብር በእንግሊዝና በደቡብ አፍሪካ ቀረፃው ከተገባደደ በኋላ…፣ የዚህ ፊልም ታሪክ እምብርት በሆነችው በኢትዮጵያ የመጨረሻው ቀረፃ ሊደረግ ነው፡፡

ቀረፃውን ለማከናወን የሚያስችለውን የዳሰሳ ጥናት ለማድረግ የፊልሙ ፕሮዳክሽን ማኔጀርና የፕሮዲዩሰሮች ቡድን ኢትዮጵያ ውስጥ ከሚመለከታቸው የመንግሥት አካላት፣ ከፖሊስ ኮሚሽን ባለሥልጣናት፣ ከታሪክ ምሁራን፣ ከአርቲስቶች፣ ከታዋቂ ሰዎችና ከኪነ ጥበብ ባለሙያዎች ጋር ውይይት አድርገዋል፡፡

ቡድኑ ባለፈው ሳምንት ከፌዴራል ፖሊስ ምክትል ኮሚሽነር ሐሰን ሺፋ ጋር በመሆን የደቡብ አፍሪካ የፀረ አፓርታይድ ታጋይ ኔልሰን ማንዴላ ወታደራዊ ሥልጠና በወሰዱበት ኮልፌ በሚገኘው የፖሊስ ማሠልጠኛ ተገኝተው ጉብኝት አድርገዋል፡፡

በጉብኝቱም ወቅት ማንዴላ ሥልጠና ሲያደርጉበት የነበረበትን ሜዳ፣ የሚያርፉበትን ክፍልና የቦክስ ልምምድ የሚያደርጉበትን ሥፍራ አይተዋል፡፡

ማንዴላ ያርፉበት በነበረበት ክፍል ውስጥም የቡና ማፍላት ሥርዓት መካሄዱን ‹‹ዘ ማንዴላስ ገን›› ፊልም በኢትዮጵያ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ሥራ የሚሠራው የርዕዮት ኪነ ጥበብና ፕሮሞሽን የራዲዮ ፕሮግራም ዝግጅት ባልደረባ አቶ ቴዎድሮስ ፀጋዬ ለሪፖርተር ጋዜጣ ገልጸዋል፡፡ በተለይ ደቡብ አፍሪካውያንና እንግሊዛውያንን ያቀፈው ቡድን አባላት ቅዳሜ ዕለት በሒልተን ሆቴል የታሪክ ምሁራን፣ የኪነ ጥበብ ባለሙያዎች፣ አርቲስቶች፣ ጋዜጠኞች፣ የባህልና የቅርስ ኤክስፐርቶችና ትምህርታቸውን በደቡብ አፍሪካ የተከታተሉ ኢትዮጵያውያን ተጋባዥ እንግዶች በተገኙበት ውይይት አድርጓል፡፡

ማንዴላ ለወታደራዊ ሥልጠና በኢትዮጵያ ውስጥ በነበሩበት ወቅት የነበሩ፣ ታሪኩን የሚያውቁ፣ ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸውና ይህን በተመለከተ ማንኛውም ዓይነት የምስል፣ የጽሑፍና የድምፅ መረጃዎች ያሉዋቸው መንግሥታዊ አካላትና ግለሰቦች ትብብር እንዲያደርጉ የተጠየቀ ሲሆን፣ በውይይቱም ወቅት በፊልሙ ላይ ኢትዮጵያና ኢትዮጵያውያን እንዴት ነው መገለጽ ያለባቸው የሚለው የታሪክ ባለሙያዎችንና ሌሎች ተሳታፊዎችንም አወያይቷል፡፡

‹‹ማንዴላስ ገን›› ፊልም በኢትዮጵያ አስተባባሪና ተወካይ የሆኑት የታይኮን ሪል ስቴት ባለቤት አቶ አሰፋ ገብረ ሚካኤል በውይይቱ ወቅት፣ ‹‹በተቻለ መጠን የታሪክ ሽሚያና መፋለስ ሳይኖርበት፣ ያሉንን መረጃዎች በጥንቃቄ በመመርመርና በማጠናቀር ኢትዮጵያ በደቡብ አፍሪካ በፀረ አፓርታይድ ትግል፣ በአፍሪካ፣ በአፍሪካ አሜሪካውያንንና በአጠቃላይ በሰው ልጆች ነፃነት ትግል ታሪክ ውስጥ የነበራት አዎንታዊና ታላቅ የሆነ ታሪካዊ ሚና በሚገባ በፊልሙ ውስጥ እንዲገለጽ ትልቅ ጥንቃቄ እንደርጋለን፤›› ሲሉ ለውይይቱ ተሳታፊዎች አስረድተዋል፡፡

አቶ አሰፋ በአንድ ወቅት ቢቢሲ ባዘጋጀው ‹‹ዘ ብሉ ናይል›› በሚለው ጥናታዊ ፊልም ውስጥ በኢትዮጵያ በኩል አስተባባሪና ተወካይ መሆናቸውን አስታውሰው፣ በዚህ ፊልም ውስጥ የናይል ወንዝ መነሻና ከውኃው ከ85 በመቶ በላይ ድርሻ በማበርከት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ካላት ኢትዮጵያ ይልቅ፣ ጉልህ ድርሻ የተሰጣት ግብፅ መሆኗን እንዳላስደሰታቸው ቅሬታቸውን በመግለጽ፣ በዚህ ወቅት ግን እንዲህ ዓይነቱ ስህተት ዳግም እንዳይከሰት ከፍተኛ ጥንቃቄ ይደረጋል ብለዋል፡፡

የውይይቱ መሪ የነበሩት የኢትዮጵያ ጥናትና ምርምር ተቋም ወዳጆች ማኅበር አስተባባሪ ዶክተር ብርሃኑ ግዛው፣ ‹‹የዚህ ውይይት አስፈላጊነትም እንዲህ ዓይነቱ የታሪክ ሽሚያና ኢትዮጵያችንን ለተቀረው ዓለም አኮስሶ የሚያሳይ ስህተት እንዳይኖር ከወዲሁ ሁላችንም የበኩላችንን ጥረት ለማድረግ የተጀመረ ውይይት ነው፡፡ ይህ ውይይትና የሐሳብ ልውውጥ ወደፊትም ፊልሙ ተቀርፆ እስኪያበቃ ድረስ የሚቀጥል ይሆናል፤›› በማለት ገልጸዋል፡፡ ባለፈው ቅዳሜ በሒልተን ሆቴል በተካሄደው ውይይት የታሪክ ምሁራን፣ የኪነ ጥበብ ባለሙያዎች፣ አርቲስቶች፣ የፊልም ባለሙያዎች፣ ሙዚቃ አቀናባሪዎች፣ የባህል ኤክስፐርቶች፣ ታሪክ አዋቂ የሆኑ የዕድሜ ባለፀጋዎችና ሌሎችም በፊልሙ ሥራ ላይ የራሳቸውን የሆነ ሙያዊ ድርሻቸውን በመወጣት ፊልሙ በትክክል የኢትዮጵያን ታሪክ፣ ቅርስ፣ ባህል፣ ሥርዓትና ትውፊት በጠበቀና በሚያንፀባርቅ ሁኔታ እንዲሠራ ከወዲሁ ጥረት እንደሚያደርጉ ቃል ገብተዋል፡፡ ማክሰኞ ዕለትም በብሔራዊ ቴአትር ለዚሁ ፊልም ፕሮዲዩሰሮችና ማኔጀሮች፣ በኢትዮጵያ የፊልሙ አስተባባሪና ተወካይ የሆኑት አቶ አሰፋ ገብረ ሚካኤል ለአገር ውስጥ ጋዜጠኞች መግለጫ ሰጥተዋል፡፡ የዚህ ፊልም ፕሮዲዩሰሮች ቡድን በኢትዮጵያ በተደረገለት አቀባበልና እንዲሁም የሚመለከታቸው የመንግሥት አካላት፣ ድርጅቶችና ሌሎችንም ማመስገኑን ገልጸዋል፡፡

በኢትዮጵያ የፊልሙ ቀረፃ ታሪካዊ ጥናቶች ዳሰሳ የመጀመሪያ ሥራው አመርቂ መሆኑን የገለጹት የቡድኑ አባላት እንግሊዛዊው የፊልም ዳይሬክተር ጆን አርቪን፣ ፕሮዲዩሰር ክሌሬ ኢቫንስና እንዲሁም ደቡብ አፍሪካዊው ፕሮዲዩሰር ጄረሚ ናታን ይህ ፊልም እስከሚቀጥለው ዓመት መጀመሪያ ድረስ ይጠናቀቃል ተብሎ እንደሚጠበቅ ገልጸዋል፡፡ ፊልሙ በዋሽንግተን ዲሲ በሚቀጥለው ዓመት ሚያዝያ ወር ላይ ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ በሚገኙበት ለኔልሰን ማንዴላ ክብር በሚቆመው ሐውልት ምረቃ ላይ እንደሚቀርብ አስታውቀዋል፡፡

ኢትዮጵያ ከማንዴላ የነፃነት ትግል ሕይወት ጋር ያላትን ቁርኝት በሚመለከት እየተሠራ ባለው ፊልም ላይ አስተባባሪ የሆነችው ወጣቷ ደቡብ አፍሪካዊት ሞሮባ ናካዌ ከሪፖርተር ጋር ባደረገችው ቆይታ እንዲህ ነበር ያለችው፡፡ ‹‹… እኔም ሆንኩ አብዛኛው ወጣት ደቡብ አፍሪካዊ ትውልድ የዛሬውን የነፃነት አየር እንድንተነፍስ፣ ለዚህ ክብርና ነፃነት ያበቁን አባቶቻችን የከፈሉትን የመስዋዕትነት ታሪክና ተጋድሎ እምብዛም አናውቅም፡፡ ስለዚህ በረዥሙ የፀረ አፓርታይድ የነፃነት ትግልና በዚያን ቀውጢ ወቅት አብረውን የቆሙ አገሮችና ሕዝቦች ታሪካቸው መነገር ስላለበት ነው ይህን ፊልም መሥራት አስፈላጊ ሆኖ የተገኘው፤›› ስትል አስረድታለች፡፡

Source: Ethiopian Reporter


ፍርድ ቤቱ በአቶ መላኩ ፈንታ ያለመከሰስ መብት ላይ እልባት ሰጠ

$
0
0

አዲስ አበባ ግንቦት  9  2005 – ዛሬ  የዋለው የፌደራሉ ከፍተኛ  ፍርድ ቤት ሁለተኛ  ወንጀል  ችሎት በሙስና  ወንጀል ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር የዋሉትን የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር… አቶ መላኩ ፈንታን  ያመለከሰስ  መብት ጉዳይ  ተመልክቷል ።

 

ፍርድ ቤቱ ባለፈው ማክሰኞ  በዋለው ችሎት  የተጠርጣሪው ጠበቃ ደንበኛቸው የአዲስ አበባ  ከተማ  ምክር ቤት አባል ናቸውና ያለመከሰስ መብታቸው ተጥሷል  የሚል አቤቱታ  አቅርበው ነበር ።

ፍርድ ቤቱም  አቶ መላኩ  ፈንታ  ያለመከሰስ መብታቸውን የሚያረጋግጥ ማስረጃ  ይዘው  ለዛሬ እንዲቀርቡ  አዞ ነበር ።

በዚህም መሰረት  አቶ መላኩ ፈንታ  ሚያዚያ 16 ቀን 2000 ዓመተ ምህረት በአዲስ አበባ  የምክር ቤት አባል  ሆነው መመረጣቸውን የሚገልፅ  መታወቂያ  አቅርበው ነበር ።

የፌደራል  የስነ ምግባርና  ፀረ ሙስና  ኮሚሽን የመርማሪ ቡድን  በጉዳዩ ላይ  ምላሹን እንዲሰጥ  ተደርጓል ።

በዚህም  መሰረት  የመርማሪ ቡድኑ  እንዳስረዳው በኢትዮጵያ የምርጫ  ቦርድ አሰራር  መሰረት የአቶ መላኩ ፈንታ  ያለመከሰስ መብት  የቆይታ ጊዜ አብቅቷል ።

ግንቦት 2005 ዓመተ ምህረት የምርጫ ሂደት ያሸነፉ የከተማዋ ምክር ቤት አዲስ አባላት ስም ዝርዝርን  የምርጫ ቦርድ ይፋ በማድረጉ ጥቂት የሽግግር ቀናት ካልሆነ በስተቀር አቶ መላኩ ፈንታ ያለመከሰስ መብት አላቸው የሚል አሰራር የለም ብሏል ።

ፍርድ ቤቱም ግራና ቀኙን ተመልክቶ የአቶ መላኩ ፈንታ  ጉዳይ በመዝገቡ በተጠረጠሩ ሌሎች ስድስት ግለሰቦች ላይ የተጠየቀው የ14 ቀን የጊዜ ቀጠሮ ፀንቶ ለግንቦት 19 ቀን 2005 ዓመተ  ምህረት እንዲቀርቡ ወስኗል ።

በጥላሁን ካሳ

source shegar


የአውስትራሊያው ኤስ ብ ኤስ ራዲዮ ከሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ኢንጂነር ጌትነት ይልቃል ጋር የተደረገ ቃለ መጠይቅ

$
0
0

አውስትራሊያው ኤስ ብ ኤስ ራዲዮ ከሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ኢንጂነር ጌትነት ይልቃል ጋር የተደረገ ቃለ መጠይቅ..


“የሞቱት ሁሉም ትውልዶች ልማዶች/ባሕሎች፣ እየኖሩ ባሉት ሰዎች ጭንቅላት ላይ እንደ ቅዠት ይጫኗቸዋል፡፡” –ካርል ማርክስ፣ 1852[1

$
0
0

ሉላዊ ሴራ – የተሸሸጉ ታሪኮች  the first blog in Amharic የተወሰደ ነው::

ጋርዮሻዊነት የተባለው ከጥንት ሲንከባለል የመጣና ከሰው ተፈጥሮ የማይታረቅ በመሆኑ ተቀባይ ያጣ፣ ግለሰቡን ከነጻነት አምዶች አንድ የሆነውን ንብረት የማፍራትና የመያዝ መብቱን እና ሌሎችም ሰብአዊ መብቱን ከላይ በእቅድ…. በሚመሩቱ ብቻ በሞኖፖል መያዝ አለበት የሚል ዘመናዊ ስሙ ኮሚዩኒዝም የተባለ ፍስፍና ነው፡፡ አንዳንድ ሰዎች በውጭም በሃገራችንም “ኮሚኒዝም ይመጣል” የሚል መልእክት ከወቅቱ ኢኮኖሚያዊ ቀውስ ጋር በማያያዝ የሞተው ትንቢትን ዳግም እያስተጋቡ ይገኛሉ፡፡ እንዲህ ሳነብ ሁሌም፡- “ከዚህ ቀደም በመላው ዓለም በተግባር ተፈትሾ አውዳሚነቱን አስመስክሮ የከሸፈው ኮሚኒዝም ተመልሶ ገና ወደፊት እንዳይመጣ እንደማስጠንቀቅ ምነው ያሟርታሉ፡፡” እላለው፡፡  ጽሑፋቸውን ሳነበው “ካፒታሊዝም አበቃለት፣ ሰርቶ-አደሩ ኮሚኒዝምን ሊቀበል ነው፡፡” የሚል ሐሳባቸውን ያለ በቂ ትንተና ስሜት ቀስቃሽ አድርገው ይጽፋሉ፡፡

 በጽሁፋቸው መሰረት ካፒታሊስቶች በቃኝ ስለማያውቁ ትርፋቸውን ለማብዛት ሲሉ አብዝተው በማምረት በተረፈ ምርቶቻቸው ዓለም ከተጥለቀለቀች በኋላ ቀውስ ይከተላል፣ ይህን ለመታደግም ካፒታሊስቶቹ ኢምፐርያሊስት ፖሊሲ በማራመድ የድሃውን አገር ጥሬ ሃብትና ገበያ ይበዘብዛሉ፣ መጨረሻ ላይ የሰርቶ-አደሩ ንቃተ ሕሊና ሲዳብር ሶሻሊስት (ሕብረተሰባዊ) አብዮት ይከተላል ይህም በኮሚኒዝም (ጋርዮሻዊነት) ይገባደዳል ይላሉ፡፡
ይህ ነገር ይሆናል የተባለው አሁን የገጠመው ዓለም አቀፋዊ ቀውስ ተከትሎ ሳይሆን ቀድሞ ማርክስ ይሆናል ብሎ ተንብዮ ከከሸፉት ውስጥ ያለ ንድፈ ሃሳብ ነው፡፡ እንግዲህ በዚህ ጽሑፍ 2 እንዲህ ያለው ሃሳብን በዝርዝር መረጃዎች ላይ ተመርኩዘን ለቀውሱ ትክክለኛ ምክንያት በመዳሰስ በርእዮተ ዓለማዊ እምነት ሳንታወር እውነቱን እናያለን፡፡ ከላይ ያስቀመጥነው የማርክስ ጥቅስ በ19ኛው ክ/ዘመን ሙታንን ለመቅበር ሲታክት የነበረውን ሊያሳይ ያለው ሲሆን ዛሬ ደግሞ ይህ ጥቅስ እራሱ በሚገርም መልኩ፣ ሃሳቦቹ በተግባር ተሞክረው ያለፈ ትውልድ ሙታን ልምድ ሁነው አሁን በተራቸው ምድርን እያስጨነቋት ይገኛሉ፡፡

ማርክስ ምን አለ?

ማርክሳዊ ትንታኔ ቁሳዊ ሁናቴዎችን በመተንተን ይጀምራል፡፡ የማህበረሰብ ኢኮኖሚያዊ አወቃቀሩ ወይም የአመራረት ዘይቤው ሌሎች ማህበራዊ ሁናቴዎች የታነጹበት መሰረት ተደርጎ ይወሰዳል፡፡ ሌሎች ማህበራዊ ሁናቴዎች የሚባሉት እንደ ፖለቲካዊና ሕጋዊ ስርዓቶች፣ ስነ ምግባር እና ርእዮተ ዓለም ወዘተ. ሲሆኑ ላእላይ-ቅርጽ ይባላሉ፣ ለነዚህ ኢከኮኖሚያዊው ስርአት መሰረት ይሆናቸዋል፡፡ የምርት ኃይሎች በተለይ ቴክኖሎጂ በተሻሻለ ቁጥር ማህበራዊ አወቃቀሩ ካልተቀየረ እድገትን አንቆ ይይዛል፡፡
ይህ ማነቆ እራሱን በማህበራዊ ግጭት አድርጎ ይገልጻል፣ ይህም በመደቦች መሃከል በሚደረገው ትግል የሚታይ ነው፡፡ በካፒታሊስት የአመራረት ዘይቤ ይህ ግጭት የማምረቻ መሳርያውን በተቆጣጠሩ በአናሳዎቹ (ብርዡዋ)እና ምርት እና አገልግሎቱን በሚሰሩ በብዙሃኑ (ሰርቶ አደሮች) መሃከል የሚደረግ ይሆናል፡፡ በዚህ ስሌት መሰረት ካፒታሊዝም ሰርቶ አደሩን የሚጨቁን ሲሆን ይህ ደግሞ ወደ ሰርቶ አደሩ አብዮት እንዲሄዱ ያደርጋል ይላል፡፡
የዚህ ንድፈ ሃሳብ መሰሩት የሆኑትን ነጥቦች ዝርዝርን አንድ በአንድ እንመልከታለን፣ እኚህ ሃሳቦች ሁሉም በተግባርም በንድፈ ሃሳብም ስህተት መሆናቸው ታይቷል ሆኖም ግን ነገርን ከስሩ … እንደሚባለው በቅድሚያ ለብቻ ልንመለከታቸው ይገባል፡-

ማርክሲስታዊ ንድፈ ሃሳብ

ኢኮኖሚያዊ መሰረት

ከላይ እንዳየነው ማርክስ የአመራረት ዘይቤው ለማህበረሰቡ ከሌሎች ነገሮች በላይ ዋናው መሰረቱ መሆኑን ይገልጻል፡፡ በዚህም ምክንያት ማርክስ“ቁሳዊ” ነው ይባላል፡፡ ማርክስ የሄግል ተማሪ እያለ የታሪክ ወሳኝ አምድ ሃሳብ (አይዲያ) እንደሆነ የተማረውን አልተቀበለም፡፡ የበላይ የሆኑ ሃሳቦች የቁሳዊ ወይም ኢኮኖሚያዊ ሁኔታ ውጤቶች ናቸው በማለት ሃሳብ ብቻ ማህበረሰቡን ሊቀይር ይችላል የሚለውን ተቃወመ፡፡

አምራች ኃይል እና አመራረት ዘይቤ

በአምራች ኃይል እና በአመራረት ዘይቤ ማሃከል ያለው መስተጋብር ምን አይነት ሕብረተሰብ እንደሚኖርና ምን አይነት ማህበራዊ ለውጥ እንደሚመጣ ወሳኙ ግብአት አድርጎ ይቆጥራል፡፡  አምራች ኃይል የባርያ ጉልበት፣ የማሽን ቴክኖሎጂ ወዘተ. ሊሆን ይችላል፡፡ የአመራረት ዘይቤ ደግሞ አምራች ኃይሉ በማን ባለቤትነትና ቁጥጥር ስር መሆኑን የሚገለጽበት ነው፡፡ በባርያ ስርአት ጌቶች ባሮችን አስገድደው ያሰራሉ፣ በፊውዳል (ባላባታዊ) ስርአት ጭሰኞች በባላባቶች ስር ናቸው፡፡ በካፒታሊስታዊ ህብረተሰብ ካፒታሊስቶች የማምረቻ ምንጮችን በመቆጣጠር በደሞዝ ሰራተኞች ቀጥረው ያሰራሉ፣ ትርፍ እናገኛለን ብለው ካመኑ፡፡
ሲጀምር መጀመርያ ላይ አዲስ አምራች ኃይሎችና አዲስ የአመራረት ዘይቤ ለሕብረተሰቡ የሚጠቅም ወይም ተራማጅ ነው፡፡ ግዜ እየገፋ ሲሄድ ግን ጥቅሙ እየቀነሰ ይመጣል፡፡ አዲሱ ማሕበረሰባዊ የአመራረት ዘይቤ የአዲሶቹን አምራች ኃይሎች ሙሉ እድገትን መግታት ይጀምራል፡፡ ለምሳሌ ፊውዳሊዝም ወደ መጨረሻው ሲደርስ ሰራተኞች በነጻነት ለፈለጉት ሰው መስራታቸውን መፍቀድና መሬት መሸጥ ባላባቶችን የሚጠቅም ነገር አልነበረም፡፡ እኚህ ተግባሮች ይከለከሉ የነበሩ ቢሆንም በኋላ ላይ የካፒታሊስት አመራረት ዘይቤ አካል ሁነዋል፣ ይህም ካፒታሊዝም ላስገኘው የምርት እና ጥቅም እድገት ጠቅሟል፡፡ በዞህ መሰረት አሁን ደግሞ ዛሬ ላይ በካፒታሊስት ምርት ዘይቤ ምክንያት ረዥም እድሜ ያላቸው ምርቶችና፣ የተራቡትን ማብላት ወዘተ. የሚቻል አልሆነም፡፡ እኚህን ማህበራዊ ትርፍ ያላቸውን ነገሮች ማድረግ የካፒታሊስቶቹን ጥቅም የሚያስጠብቅ አይደለም፡፡
ስለዚህም በማርክስ ንድፈ ሃሳብ በአምራች ኃይሎች እና በማሕበረሰባዊ አመራረት ዘይቤ መሃከል ያለው መስተጋብርና የሚያስከትለው ውጤት የማሕበራዊ ለውጥ ቀዳሚ መንስኤ ነው፡፡

መደብ እና የመደብ ግጭት

የማሕበራዊ አመራረት ዘይቤ የተለያዩ መደቦችን ያሳተፈ ነው፡፡ መደብ የሚወሰነው ግለሰቡ ከማምረቻ መሳርያዎች ጋር ባለው ግንኙነት ነው፡፡ ለምሳሌ በመጨረሻው የካፒታሊስት ማሕበረሰብ ሁለት መሰረታዊ መደቦች ይኖራሉ፡ የማምረቻ መሳርያዎች ባለቤቶች ማለትም ካፒታሊስቶች እና የጉልበታቸው ብቻ ባለቤት የሆኑት ማለትም ሰርቶ አደሮች፡፡
ስለዚህ በየትኛውም የታሪክ ዘመን የበላይ እና አገልጋይ የሆኑ መደቦችን ማግኘት እንችላለን፡፡ ለማርክስ ሃብት ክፍፍልና ስልጣን ዋናው የስነ ምግባር (ሞራል) ጥያቄው ነበር፡፡ የማርክስ የመጨረሻ ህልሙ መደብ አልባ ሕብረተሰብ ነው፡፡ ለማርክስ ታሪክ ማለት የመደቦች የግጭት ታሪክ ማለት ነው፡፡ ማርክሲስታውያን ሁሌም የሚይቁት ጥያቄ የትኛው መደብ የበላይ ሆነ የሚለውን ነው፡፡ በካፒታሊስት ማሕበረሰብ ካፒታሊስቱ ይጠቀማል፡፡

ታሪክ

እስካሁን ካየነው ማርክስ የታሪክ ምልከታ ንድፈ ሃሳብ እንዳቀረበ መገመት ይቻላል፡፡ በዚህ ሃሳቡ መሰረታዊው ጭብጥ የሄግሊያዊ የሆነው “ዲያለክቲካል ሂደት” ነው፡ መጀመርያ አንድ ሃሳብ ወይም ሁኔታ – ተሲስ ይኖራል፤ ቀጥሎ የዚህ ተቃራኒ – አንቲተሲስ ይነሳል፤ የሁለቱ ግጭት ውህደታቸውን – ሲንተሲስ ይፈጥራሉ፤ ይህ ሲንተሲስ ደግሞ አሁን በተራው ተሲስ ይሆናል …፡፡ ለምሳሌ በታሪክ ባላባታዊ ስርዓቱ በውስጡ ተቃራኒ መደቦችን ይዞ ነበር፣ የበላይ የነበሩት የመሬት ባለ ቤት ባላባቶችና አዲስ ተነሱት ነጋዴዎች መደብ፤ እነዚህ ሁለቱ ሲጋጩ ውህደታቸው የሆነውን የካፒታሊስት ዘመን አመጡ፡፡
ስለዚህም ታሪክ መቀዳሚነት የቁሳዊ ወይም ኢኮኖሚያዊ ሁናቴዎች መገለጫ ነው፡፡ ለዚህም ነው “ታሪካዊ ቁሳዊነት” እና “ዲያለክቲካል ቁሳዊነት”በመባል ሃሳቡ የሚጠራው፡፡ የማምረቻ ቴክኖሎጂ ደረጃ/ ዓይነት እና የነዚህ ቁጥጥርና ማህበራዊ ግንኙነት ነው የአንድ ሕብረተሰብ አደረጃጀትን ምንነት ማለትም ጥንታዊ (ጋርዮሽ)፣ ባርያ፣ ፊውዳል (ባላባታዊ) እና ካፖታሊስት መሆኑን እና ከአንዱ ወደ ሌላው መሸጋገሩን የሚወስነው፡፡ ማርክስ ይህ የታሪክ እይታው እንደ ዋና ግኝቱ ይቆጥው ነበር፡፡ ይህም እይታው ከዋጋ ንድፈ ሃሳቡ ጋር በጋራ ነበር ማርክሲስታዊነትን እንደ ሳይንስ ያስቆጠሩት፡፡ (ለነዚህ የተሰጠውን ምላሽ እንደርስበታለን፡፡)
ይህ የግጭት ዲያለክቲክ ሂደት ግን መጨረሻ አለው፡፡ ተሲስ የሆነው ካፒታሊዝም እና አንቲተሲስ የሆነው ሰርቶ አደር ወደ ውህደት የሚመጡ ሲሆን የዛኔም መደብ አልባ ሕብረተሰብ ይገኛል፡፡ የለውጥ ምንጩ የመደብ ልዩነት እንደመሆኑ መደብ አልባ ማሕበረሰብ ሲመጣ ዲያለክቲካል ሂደቱ መጨረሻው ይሆናል፣ ከዚህም በኋላ ፖለቲካዊ ለውጥ አይኖርም፡፡

የካፒታሊስት ምርት ዘይቤ

በካፒታሊስት ማሕበረሰብ የሚገኙት የምርት ኃይሎች የፋብሪካ ዘዴዎች (ቀድሞ በቤት በግል ይመረት ከነበረው በተለየ መልኩ) እና የከባድ ማሽን ቴክኖሎጂ ዘዴን ያካትታል፡፡ ይህ ዘይቤ ሰፊ የካፒታል ሃብት ማፍሰስን ይጠይቃል፡፡ እዚሕ ያለው ማህበራዊ ግንኙነት የማምረቻ መሳርያውን በያዙት ወይም በሚቆጣጠሩትና ትርፍ በሚገኝበት ብቻ የሚያውሉት ጥቂቶቹ ካፒታሊስቶች እና በሥራ ቦታ ምንም ድምጽ የሌላቸው ጉልበታቸውን ለካፒታሊቶቹ የሚሸጡ ብዙሃን ሰርቶ አደሮች መሃከል ያለው ነው፡፡
ማርክሲስታውያን ሥራ ብቻ ነው ገንዘብ ማስገኘት ያለበት እንጂ ገንዘብ፣ ገንዘብ ማስገኘት የለበትም ይላሉ፡፡ ማለትም ሃብታሞች ባስቀመጡት ገንዘብ ወለድ ወይም ባፈሰሱት ሃብት (ኢንቨስትመንት) ገቢ ማግኘት የለባቸውም ይላሉ፣ በተለይም ይህ አንድ ሰው ሃብታም በሆነ ቁጥር ስራ ሳይሰራ ይበልጥ ገቢ እንዲያገኝ የሚያደርገው እንደመሆኑ … ሃብታሞች ገቢያቸውን ተጠቅመው፣ ለማግኘት መስራት ያለባቸው ሰዎች ያመረቱት ምርት ተጠቃሚዎች ይሆናሉ፡፡

ትርፍ እና ፍላጎት

ሌላው የኢኮኖሚክስ አስተምህሮ ምርት እና እድገት በትርፍ መመራቱ ጥሩ ነው ይላል፡፡ ይህ የሚባለው ካፒታሊስቶች ሰው የሚፈልገውን ምርት ሲያመርቱ ትርፋቸውን ያሳድጋሉ፣ በዚህም አዋጭ የሃብት አጠቃቀም ይፈጠራል ከሚለው እሳቤ ነው፡፡ ማርክሲስታውያን ግን ለትርፍ በሚደረግ ምርት እና ፍላጎትን ለማሟላት በሚደረግ ምርት መሃከል ሰፊ ልዩነት አለው ይላሉ፡፡ ይህ ሃሳብ ጥሩ ቢሆንም ለመተግበር ሲሞከር ትርፍን አማክለው ከሚሰሩት የባሰ ጥፋት ይከተላል፣ ተግባራዊም አይደለም፡፡ (እንመለስበታለን፡፡)

የሰራተኛ ዋጋ ንድፈ ሃሳብ

ማርክሲስቶች የምርቶች ዋጋ ለማምረት በፈጀው ሰራተኛ (ኃይል) ነው መሰላት ያለበት ይላሉ፡፡ ሌላው ይህን የሚወስነው ገበያው እንዳቀረበለት ነው፡፡

ትርፍ እና ብዝበዛ

የማርክሲስታዊነት ዋናው አምድ በካፒታሊስቶች ያለው የትርፍ ማግኘት ዘዴ የሰራተኞች ብዝበዛ ነው የሚለው ሃሳብ ነው፡፡ ካፒታሊስቱ ለሰራተኛውና ሌሎች ግብአቶች ያወጣውን ጨምሮ ምርቱን በትርፍ ሲሸጥ ሰራተኛው የፈጠረውን እሴት እየወሰደ ነው፡፡ በመሸጫ ዋጋው ላይ የታየው የሰራተኛው ሥራ የፈጠረው ነው፣ ሆኖም ግን ሰራተኛው የተቀበለው ከዚህ የሚያንስ ነው፣ ስለዚህም ካፒታሊስቱ እየበዘበዘው ነው፣ ምርት ማምረቱ ላይ በስራ ሳይሳተፍ የምርት ሁናቴ ተቆጣጣሪ በመሆኑ ምክንያት ይላሉ፡፡

የካፒታሊዝም መጣረስ

ማርክስ በመጀመርያ ላይ ካፒታሊዝም ተራማጅ እድገቶችን ያስመዘግባል፣ በተለይ በምርት መጨመርና ከዚህም በሕብረተሰቡ ቁሳዊ ሐብት መካበት ያስገኛል ይላል፡፡ ግዜ በሄደ ቁጥር የምርት ኃይሎች እና የማሕበራዊ ምርት ዘይቤ ወደ ግጭት ይገባሉ፣ እናም ማሕበራዊ የምርት ግንኙነቶች የቴክኖሎጂና የምርታማነት ሙሉ አቅሞችን ለማሕበራዊ ፋይዳ እንዳይውል ያደርጋል፡፡ እኚህ ውስጣዊ ግጭቶች እየከረሩ ሂደው ከግዜ ሒደት በኋላ የካፒታሊስታዊ ስርዓትን ያጠፉታል፡፡
በካፒታሊዝም ስርአት ውስጥ እራሱን እንዲያጠፋ የሚያደርገው ስርአቱ የቆመበት ካፒታሊስቶቹ ትርፍ የሚያከማቹበት ሒደት ነው፡፡ ካፒታሊስቶች እርስ በእርስ ይፎካከራሉ፣ ሁሌም አዋጭ አመራረት ዘዴ እና የተሻለ ቴክኖሎጂ ለማግኘት ይፋካከራሉ፡፡ ይህም ካፒታሊስቶቹ ሃብታቸውን ይበልጥ ወደ ማሽን (ቋሚ ካፒታል) እንዲያፈሱ እና ሰራተኛ ለመግዛት የሚያወጡትን እንዲቀንሱ ያደርጋል፡፡ ይህን ይበልጥ ለካፒታል ወጪ መብዛቱና ለሰራተኛው መቀነሱን ማርክስ የካፒታል “ተፈጥሯዊ ውህደት” / “organic composition” ይለዋል፡፡ በዚህ የካፒታል ሂደት ምክንያት የሰራተኛው ስቃይ እየባሰ ይሄዳል፣ የካፒታሊስቱ ሃብት እየጨመረ ሲሄድ፡፡ በዚህ የሰራተኞቹ መዳከም ምክንያት የካፒታሊስቶቹን ምርት የሚገዛ ስለማይኖር በረዥም ግዜ ሂደት የካፒታሊስት ትርፎች እየቀነሱ ይሄዳሉ፡፡ በካፒታሊዝም ውስጥ የተገነቡት እኚህ ተፈጥሮው ምክንያት በግዜ ሂደት ካፒታሊዝም ይከስማል፡፡ አብዮት እንዲነሳ በሚያደርግ ደረጃ የካፒታሊስቱ ትርፍና የሰርቶ አደሩ ሕይወት ደረጃ ይወርዳሉ፡፡

ማከማቸት

ማርክሲስቶች በካፒታሊስት ማሕበረሰብ የሚገፋው ሃይል ማለቅያ የሌለው ትርፍ የማከማቸት ሩጫ ነው ይላሉ፡፡ ይህ ለለውጥና ፈጠራ ይመቻል፡፡ ካፒታሊስቱ የውድድሩ እስረኛ ነው ወደ ኋላ ከቀረ ይጠፋል፡፡ ይህ ገዳይ ፍክክር ደግሞ ማርክሲስቶች አይወዱትም፡፡

የትርፍ ምርት ችግር

ካፒታሊዝም ሁሌም እየተከማቸ ላለው ካፒታል ትርፋማ የማድረግ ፈተና አለበት፡፡ የትርፍ ምርት ችግር ወደ ሉላዊነት (ግሎባላይዜሽን) እንዲኬድ ያደረገው ዋናው ምክንያት ነው፣ ምክንያቱም ሉላዊነት ትርፋማ መስኮች ላይ ሃብታቸውን የሚያፈሱበት አዳዲስ በሮች ይከፍትላቸዋልና፡፡

የተነጠለ ሰራተኛ

ካፒታሊዝምን ከወቀሰበት ሌላው ብዝበዛ ሰራተኛው እንዲነጠል ያደርገዋል የሚል ነው፡፡ ለአዋጭ ምርታማነት ሲባል ሰራተኛው በአንዲት ሙያና ተደጋጋሚ ተግባር ያለው ሥራ ላይ እንዲያተኩር ስለሚደረግ፣ የሥራውን የመጨረሻ ውጤት አያዩም፣ ሥራ ይታክታል፣ ምርቱም የሰራተኛው ስላልሆነ ምን መሆን እንደሚገባው መወሰን አይችሉም፣ የመሣሪያዎቹ ባለቤት አይደሉም፣ በሥራ እቅድና አደረጃጀት ድምጽ የላቸውም፣ የተባሉትን ብቻ ይሰራሉ፣ መመሪያዎችን መጣስ የለባቸውም በተለይ ሰዓት በሚመለከት፣ ይህ በሰፊ የሥራ ክፍፍል ውስጥ ሁነው ይሸከሙታል፡፡ የግል መነሳሳታቸውን ለመፈጸም እድል የላቸውም፡፡ በስራው ሂደት ያላቸው ብቸኛው ግንኙነት የሚቀበሉት ገንዘብ ብቻ ነው፡፡ (እኚህ ሁኔታዎች ማርክስ በነበረበት ግዜ የነበሩ የፋብሪካ ሰራተኞችን እንጂ የዘመናዊውን የቢሮ ሰራተኞች አይገልጽም)
ማርክስ የሚያረካ ስራ የሰው ልጆች ስሜታዊና መንፈሳዊ ደህንነት ወሳኝ መሆኑን አጽንኦት ይሰጠዋል፡፡ ካፒታሊዝም ሰራተኞች የሚያስደስታቸው እና ማሕበረሰባቸውን የሚጠቅም ስራ ላይ እንዳይሰማሩ ያደርጋል ይላል፡፡ (በተግባር የሆነው ተቃራኒው ነው፡፡)

የማሕበረሰብ መውደም

ማርክስ ካፒታሊዝም ኢኮኖሚያዊ ወይም ትርፍ-ተኮር ያልሆኑ እሴቶችን በማጥፋት ገንዘብ ነክ በሆኑት ይተካቸዋል ይላል፡፡ ገበያ እና ካፒታሊስቶች በሚፈልጉት ተንቀሳቃሽ ሰው ሃይል ምክንያት ሰራተኞች ከቦታ፣ ቡድኖች፣ ሰዎችና ባህሎች ጋር ያላቸው ጠንካራ ስሜታዊ ግንኙነቶችን አጥፍቷል፣ ይህ ማሕበረሰባዊ ትስስር እንዲቀንስ አድርጓል ይላሉ ያሁኖቹ ማርክሲስቶች፡፡ አሁን ግለሰቡ ከማሕበረሰቡ ተነጥሎ ይኖራል ያለ ማሕበራዊ ግዴታና ትስስር፡፡ በዚህም ሳቢያ ጭንቀት፣ ብቸኝነት፣ ግለኝነትና የቤተሰብ መፍረስ፣ ራስን ማጥፋት፣ ወንጀል፣ ሱሰኝነት ወዘተ. ተከትሏል፡፡
በሌላ አገላለጽ ካፒታሊዝም ሁሉን ነገር ወደሚሸጥ ሸቀጥ ቀይሮታል፣ በተለይ ሥራን፡፡ ሥራ፣ መሬት እና ገንዘብ በፊውዳል ዘመን የሚሸጡ ሸቀጦች አልነበሩም፡፡

መንግስት

ማርክሲስታውያን መንግስት በማሕበረሰቡ የበላይ የሆነውን መደብ ያገለግላል ይላሉ፡፡ በካፒታሊስታዊ ማሕበረሰብ መንግስት የካፒታሊስት መደብን ያገለግላል፡፡ ለምሳሌ መንግስት ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴን መጨመር ቅድሚያ የሚሰጠው ስራው ይሆናል፣ ይህ የኑሮ ጥራት መውረድና ስነ ከባቢያዊ ቀውስ ቢያስከትልም፡፡ የመንግስት ዋና ባሕርይ የሕብረተሰቡን አባሎች መስገደድ፣ መቅጣት እና ጦርነት መክፈት መቻሉ ነው፡፡ ይህን አቅሙን የሚጠቀምበት የበላይ የሆነውን መደብ ለመጥቀም ነው፡፡ መደብ አልባ ማሕበረሰብ ሲመጣ መንግስት አስፈላጊ አይሆንም፡፡

ርእዮተ ዓለም፡ የተሳሳተ ንቃተ ሕሊና

የሚበዘበዙ መደቦች ሁኔታቸውን ወይም የሚጠቅማቸውን ባግባቡ አይረዱም፡፡ ነባራዊው ሁናቴ ፍትሃዊ ነው ብለው እንዲቀበሉ ይደረጋሉ፡፡ ለምሳሌ በባላባታዊ አስተዳደር ንጉሱ እግዚአብሔር የሾመው ነው ብለው ያምናሉ፣ ምድራዊ ድህነታቸውም ወሳኝ እንዳልሆነና በቀጣይ ሕይወት ለመካስ ማሰብ እንዳለባቸው ያምናሉ፡፡ በእኛ ዘመን ደግሞ ትላልቅ ሚድያዎች የበላይ የሆነውን ርእዮተ ዓለም ያሰርጻሉ ይላሉ ማርክሲስቶች፡፡
በየትኛውም መደባዊ ሕብረተሰብ የበላይ የሆነውን መደብ የሚመች ርእዮተ ዓለም ይኖራል፡፡ ሰራተኛው መደብ ለካፒታሊስቱ የሚመቹ እሴቶችን ሲቀበል “የቡርዥዋ የበላይነት” ይበላል፡፡ ማርክስ በካፒታሊዝም ማብቅያ ሰራተኞች ስለሁኔታቸውና ጥቅማቸው የበለጠ መረዳት ያዳብራሉ፣ የመደብ ንቃተ-ሕሊና ይመጣል፡፡

አብዮት

ማርክስ ካፒታሊዝም በውስጡ ያሉ ችግሮችን እስኪያጠፉት ድረስ የሚያደርሱ ኃይሎችና ሂደቶችን ይዟል ብሎ ያምናል፡፡ በምርት ኃይሎችና ዘይቤ መሃከል ያለው መስተጋብር እየተሸረሸረ ሲሄድ ግጭቶች እየባሱ ይመጣሉ፣ ካፒታሊስትና ሰርቶ አደር መደቦች መሃከል ያለው ልዩነት እየሰፋ፣ የሰርቶ አደሩ መከራ እየበዛ፣ የሰርቶ አደሩ ንቃተ ሕሊና ሲጨምር፣ መጨረሻ ላይ አብዮት ይፈነዳል፡፡
ከአብዮት በኋላ መጀመርያ የሰርቶ አደሩ አምባገነን መንግስት የሚመሰረት ሲሆን፣ ይህ የካፒታሊዝም ቅሪቶችን በተለይም የብርዥዋ ርእዮተ ኣለምን የሚያንጹት እሴቶችን ማጥፋት ላይ ይሰማራል፡፡ አምባገነናዊው መንግስት እየሳሳ ይሄዳል፣ ሰፊ የሥራ ክፍፍልና ሙያ ተኮርነት ይጠፋል፣ የግለሰቦች አመለካከት ማሕበራዊ ይሆናል፡፡

ማርክስ ምን ሳተ?

ማርክስ ምን እንደሚል በዝርዝር ማቅረብ ያስፈለገው አንድ ስለእርሱ ሂስ ስናቀርብ ስለምንናገረው እንደምናውቅ ለማሳየትና ሁለት አንባቢው ተጫዋቾቹን ሁሉንም በሚገባ እንዲረዳ በሚል ነው፡፡ ማርክስ ያቀረባቸው ሁሉ ትንተናዎች ስህተት ናቸው፡፡ ስህተት መሆናቸውን እናያለን፤ ቀጥለን ደግሞ እንዲህ ስህተት ከሆነ ሰዎችን ለምን ይስባል የሚለውን እናያለን፡፡

ኢኮኖሚያዊ ሂስ

ማርክሲስታዊ ኢኮኖሚክስ በካፒታሊዝም ትንታኔው ስህተት እና ማርክሲስታውያን በሚያቀርቡት መተግበር የማይቻል ኢኮኖሚያዊ ስርአት ላይ በመመርኮዝ ይተቻል፡፡

የሰራተኛ ዋጋ ንድፈ ሃሳብ

በሉድዊግ ቮን ሚዝስ የተመሰረተው የኦስትርያ ኢኮኖሚክስ አስተምህሮ የማርክስ ኢኮኖሚያዊ ስርአት በክላሲካል የሰራተኛ ዋጋ ንድፈ ሃሳብ ላይ በመመስረቱ ይወቅሰዋል፣ ምክንያቱም ንድፈ ሃሳቡ ስህተት ነውና፡፡ ይህ ንድፈ ሃሳብ የሚለው እንዳየነው የአንድ ምርት መለክያ መሆን ያለበት የፈሰሰበት የሰራተኛ ጉለበት ብቻ ነው፡፡ ይህ ቀድመውት በነበሩ ክላሲካል ኢኮኖሚስቶች እንደ አዳም ስሚዝ እና ዴቪድ ሪካርዶ ይጠቀሙበት የነበረ ነው፡፡[3] ማርክስ ክላሲካሎቹ ትርፍን ሙሉ ለሙሉ ማብራራት እንዳልቻሉ የተናገረው ልክ ነው፣ ሆኖም ግን እርሱም ትርፍን በትክክል አላብራራም፡፡ ማርክስ ክላሲካሎቹ ሃሳቡን ማድረስ ከፈሩበት ቦታ አድርሶ የካፒታሊዝም በዝባዥነት ማሳያ ያደርገዋል፡፡ እንደማርክስ አባባል ዋጋ በሰራተኛ ጉልበት ብቻ መለካት ስላለበት ካፒታሊስቱ ገበያ ላይ ለጉልበት ካወጣው ዋጋ በላይ ሲሸጥ ያገኘው ትርፍ የብዝበዛ ውጤት ነው ይለዋል፡፡ ማርክስ የሰራተኛ የዋጋ ንድፈ ሃሳብን ለጥጦ ካፒታሊዝምን ለመውቀስ ሲጠቀምበት የራሱን አጠቃላይ ሃሳብ ድክመት ነበር ያሳየው፡፡
ከ19ኛው ክ/ዘመን ማገባደጃ ጀምሮ የሰራተኛ የዋጋ ንድፈ ሃሳብን የሚቀበል ቁም ነገረኛ ኢኮኖሚስት የለም፣ ከዚህ ይልቅ እንደ ኦስትርያ ኢኮኖሚክስ አስተምህሮ የምርት ዋጋ በሰው ምርጫ የሚወሰን በመሆኑ“እንደአመለካከት የዋጋ ንድፈ ሃሳብ” (subjective theory of value) ያራምዳል፡፡ የፈለገው ግብአት ቢጨመር ዋጋው በምርጫ ይገደባል የሚል ነው፡፡ ዛሬ ትርፍ ብዝበዛ ሳይሆን ስራ ፈጣሪ ካፒታሊስቶች የዛሬ ፍጆታ ላይ ማዋል የሚችሉትን ገንዘብ ለፍጆታ ባለማዋል፣ የሚሆነውን በመቀበል ወይም ሪስክ በመውሰድ ገንዛብ በማፍሰስ፣ እና ምርት በማደራጀት የሚያገኙት ዋጋ ነው፡፡

የዋጋ አንቴናዋችን ማዛባት፡ የስሌት ችግር

ይህ የሶሻሊስት ኢኮኖሚ እቅድ አወጣጥን የሚወቀስበት ነጥብ ነው፡፡ መጀመርያ በሉድዊግ ቮን ሚዝስ በ1920 የተነሳ[4] ሲሆን በኋላ በፍሬደሪክ ሃይክ[5] ተብራርቷል፡፡ የተነሳው ችግር ግብአቶችን እንዴት በትክክል በኢኮኖሚው ውስጥ ማሰማራት ይቻላል የሚለው ነው፣ ምክንያቱም ያለ ዋጋ ፍላጎትን ማወቅ አይቻልምና፡፡ በነጻ ገበያ ውስጥ የዋጋ ስርአት ይፈታዋል፣ ሰዎች ሊከፍሉለት ዝግጁ የሆነ ነገር ግብአቱን ይጠቀምበታል፡፡ በግለሰቦች ደረጃ ዋጋ ለማውጣት በሚወስኑት ውሳኔ መሰረት እጥረት እና ተረፈ ምርት ክስተቶችን እንዲታረሙ ያደርጋል፡፡ ሚዝስ እና ሃይክ ይህ ብቸኛው መፍትሄ እንደሆነና ያለዚህ ርቱእ በሆነ መንገድ ጥሬ ሃብት በቅጡ ማከፋፈል አይቻልም ይላሉ፡፡ ይህ የሶሻሊስት የታቀደ ኢኮኖሚ ሊሰራ እንደማይችል ማሳያ ነው፡፡ ክርክሩ በ1020ዎቹና 30ዎቹ የጦፈበት ዘመን ነበር፡፡[6] በ1990ዎቹ በሶሻሊስት ኢኮኖሚዎች ክስመት ማን ልክ እንደነበር ታይቷል፡፡

ተነሳሽነትን ማኮላሸት

ሰርቶ አደሩ የማምረቻ መሳርያዎች ባለቤት ሲሆን ገቢውን ይከፋፈላል ይላል ማርክስ፣ ገቢ በግል የሚወሰን ካልሆነ የሥራ መነሳሳትን ያጠፋል፡፡[7] ማንም የተሻለ ሥራ ቢሰራ የተሻለ ስለማያስገኝለት ለተሻለ ስራ የሚነሳሳበት ምክንያት አይኖርም፡፡ ጆን ኬንዝ ጋልብረይዝ የተባለው ኢኮኖሚስት እንደሚከተለው ይላል፡
“ይህ ከማርክስ አልፎ ብዙዎችን ያዳረሰው [እኩልነትን መሰረት ያደረገ ማበረታቻ የላቀ ተነሳሽነት ያስገኛል] የሚለው ተስፋ፣ በታሪክና በልምድ ከንቱ መሆኑ ታጥቷል፡፡ ለበጎም ሆነ ለክፉ የሰው ልጆች ከዚህ የላቀ መዓረግ ደርሰው አያውቁም፡፡ የሶሻሊስ አመራር የተለያዩ ትውልዶች ይህን ሃቅ በውድቀታቸውና በሚያሳዝናቸው መልኩ ተምረውታል፡፡ መሰራታዊው እውነት ግልጽ ነው፡ መልካሙ ሕብረተሰብ ወንዶችና ሴቶችን ከነምንነታቸው ሊቀበል ይገባል፡፡”[8]

ትርፍ እና ብዝበዛ

ማርክስ ካፒታሊዝም በብዝበዛ ላይ ተመሰረተ ስርዓት በመሆኑ እራሱን ማጥፋቱ አይቀርም የመጨረሻው ደረጃ ላይ ሲደርስ በአብዮት ተወግዶ በሶሻሊዝም ይተካል ብሎ ነበር፡፡ ሆኖም ግን ይህ ድምዳሜ ላይ የደረሰው ከክላሲካል ኢኮኖሚስቶች የተዋሰው የተሳሳተ የዋጋ ንድፈ ሃሳብ ላይ ተሞርኩዞ ነበር፡፡ የሥራ ዋጋው ደሞዝ ሲሆን የካፒታል ዋጋው ደግሞ ትርፍ ነው፣ በሥራ ብቻ ያለካፒታል ምርቱ ስለማይገኝ የጋራ ዋጋ ነውና፡፡
ማርክስ በተጨማሪም ካፒታሊስቶች ትርፍ ማሳደድ ብቻ ስለሆነ ተግባራቸው፣ ይበልጥ ወጪ ለካፒታል እያወጡ ለሰራተኛው እየቀነሱ በሚሄዱበት ግዜ የሰራተኛው ኑሮ እየከፋ ሲሄድና፣ የካፒታሊስቶቹም ምርት የሚገዛ ሲጠፋ አብዮት ይነሳል ብሎ ገምቶ ነበር፡፡ በእውን የታየው ግን የቀዝቃዛው ጦርነት መጨረሻ የሆነው የሶሻሊስት ሃገሮች ኢኮኖሚ መክሰምና ከብረት መጋረጃው (አይረን ከርተይን) መፍረስ በኋላ እና እንደ ራሽያ እና ቻይና ሳይቀሩ ነጻ ገበያ ስርአት መቀበላቸውና (በቻይና ፖለቲካው ነጻ አልሆነም) ማርክሲስታዊ ስርአቶች መክሸፍ ተከትሎ ይህ ግምቱ ስህተት እንደሆነ ታይቶ ነበር፣ ዛሬ ላይ ግን ካፒታሊስቱ ዓለም ቀውስ ውስጥ ሲገባ ከዚህ ግምቱ ጋር የሚያገናኙት አሉ፡፡ ሆኖም ግን እንዲያውነም መንግስት ያለአግባብ ጣልቃ መግባቱ ነው (በሌላ አነጋገር ማርክሲስታውያን) ያመጡት ችግር ነው እንጂ ከካፒታሊዝም ጋር ግንኙነት እንደሌለው የሚያሳዩ ማስረጃዋች አሉ፣ እንመለስበታለን፡፡ ፍልስፍናዊ ትንታኔ ስላደረግነው ማርክሲስት ሳቦታጆችን አሁን አንጽፍም፡፡
አሁን የምናያቸው የኢኮኖሚ ከፍና ዝቅ ማለት ማርክስ እንዳለው የካፒታሊዝም መጣረስ ሳይሆን ከመንግስት የተሳሳተ ፖሊሲ የሚመነጭ ነው፡፡ ቮን ሚዝስ ነበር ለመጀመርያ ግዜ ሃሳቡን ያሳየው የቢዝነስ ኡደት ተብሎ የሚጠራ ሲሆን፣ የኡደቱ ምክንያትም የብድር ኡደት ነው፡፡ በኋላ ላይ ሃይክና ሌሎችም በስፋት አብራርተውታል፡፡ ይህ የሚከሰተው የገንዘብ አቅርቦቱን ለመጨመር በሚወሰዱ ፖሊሲዎች ሳቢያ ተገቢ ያልሆነ ኢንቨስትመንት እንዲደረግ ያደርጋል፡፡ ኢኮኖሚስቶች ንድፈ ሃሳቡ ልክ አይደለም ቢሉም ጄምስ ፒ. ኬለር በ2001[9] እና ሮበርት ሙሊጋን በ2006[10]ባደረጉት ጥናት ንድፈ ሃሳቡ ካለው የቁጥር መረጃ ጋር የሚገጥም መሆኑን አሳይተያዋል፡፡ ማእከላዊ ወይም ብሔራዊ ባንክ ባንኮች ሕግ እና ደንብ አክብረው መንቀሳቀሳቸውን እንደማረጋገጥ ከዚህ ውጪ የሆነ ስራ ሰርተው ኪሳራ ሲደርስባቸው ይደጉማቸዋል፣ ችግሩ ከመቀረፍም እየከበደ እንዲሄድ ያደርገዋል፡፡ ተጠያቂው ማእከላዊ ባንክና በገበያ ሕግ የማይገዛ የገንዘብ ፖሊሲ ናቸው፡፡[11] ይሄ ሁሉ ስሕተት ማረም አቅቷቸው ሳይሆን ለፖለቲካዊ ግን ዓለምን አንድ አድርጎ ለመግዛት ስለሚፈልጉት ነው፡፡
ከዚህም ቀጥሎ ስለተነጠለ ሰራተኛ እና ሕብረተሰብ መውደም ያለውም ስህተት ሁኖ እናገኘዋለን፡፡ ይህ ሃሳቡ ወሳኝና ግን ደግሞ ጽኑ ባልሆነ መሰረት ላይ የቆመ ነው፡፡ እርሱም ሰዎች ገበያ መር የሆነ ውስብስብ ሕብረተሰባዊ ትስስርን አፍርሰው ዲሞክራሲያዊና ሁሉን አቀፍ የሆነ በእቅድ የሚመራ ሕብረተሰብ መተካት ይችላሉ በሚለው እምነቱ ነው፡፡ ማርክስ የሚለው የፉክክርና ትርፍ አሳዳጅ ማህበረሰብ በመሆናችን ብቻ አይደለም መነጠል የሚደርስብን፡፡ የሥራ ወይስ ደስታ ፍጥጫም አይደለም፡፡ ውድድር፣ ትርፍና ኪሳራ፣ ገንዘብ፣ የግል ንብረት ባለቤትነት ወዘተ. የሌለው ሙሉ በሙሉ በእቅድ እና ቁጥጥር የሚመራ ሕብረተሰብ ባለመፍጠራችን ነው ይላል፡፡ ከዚህ ከመነጠል ንድፈ ሃሳብ ጋር አንድ ችግር አለ፡ እንዲህ የተራቀቀ የኮምፒውተር ቴክኖሎጂ ባለበት ዘመን እንኳ እጥረት እና ጥርጥርና የሚያስወግድ ሁሉን አቀፍ የሆነ የእቅድ ስርዓት መፍጠር አልተቻለም፡፡ ካፒታሊዝም መነጠል ይፈጥራል ከተባለ ያለካፒታሊዝም ስኬታማ የሆነ በእቅድ የሚመራ ዓለም እውን ማድረግ ያስፈልጋል፡፡ ማርክስ በካፒታሊዝም የጋራ ዕጣ ፈንታችንን በእቅድ ከመወሰን ተነጥለናል ይላል፡፡ ሚዝስ እና ሃይክ እንዳሳዩን በእቅድ የተመራ ሕብረተሰብ መቅረጽና ስኬታማ መሆን የማይቻል ከሆነ እንግዲህ ከምንም ነገር አልተነጠልንም ማለት ነው፡፡
መንግስትን በተመለከተ የበላይ መደቦች መሳርያ ነው ያለውም ልክ አልሆነም፡፡ የነጻ ገበያ ባስገኘው ዲሞክራሲ የሚኖሩ ህዝቦች ከማንም በላይ መብቶቻቸውና ጥቅሞቻቸው መንግስት እያስጠበቀላቸው ነው፡፡ አሁንም ይህን ለመቀልበስ የሚደረገውን ዓለም አቀፋዊ ሴራ አንዳስስም፣ ሆኖም ጨቋኝ ሁኖ የተገኙት እንዲያውም ማርክሲስት መንግስቶች ናቸው፡፡ የማርክሲስት መንግስቶች በዓለም ዙርያ መቶ ሚሊዮን ለሚሆን ሕይወት ሊያጠፉ ችለዋል፡፡[12]
በነዚህ እስካሁን ባየናቸው ግምቶቹ መክሸፍ ምክንያት ይመጣል ያለው አብዮት አልመጣም፣ ይመጣል ያለባቸው በሰለጠኑት ወይም በኢንድስትሪ የበለጸጉ አገሮች ውስጥ ሳይሆን በይበልጥ ግብርና ውስጥ ባሉ እንደ ራሽያ፣ ቻይና፣ ሃገራችን ጨምሮ የአፍሪካ ሃገራትና ድሃ የምስራቅ አውሮፓና ላቲን አሜሪካ አገሮች ነው፡፡ በነዚህም ቢሆን በፍስፍናው የተማረኩ ልሂቃን ያደረጉት የከሸፈ ሙከራና አምባገነኖች ጠቃሚ ሁኖ ስላገኙት የሰሩበት ነው፡፡

ታሪካዊ ቁሳዊነት

የማርክሲዝም ምሁራዊ መሰረት ተደርጎ የሚወሰደው ይህ ታሪካዊ ቁሳዊነቱ ነው፡፡ የህብረተሰብ አደረጃጀት የሚወሰነው በኢኮኖሚያዊ መሰረቱ ነው፣ ላእላይ ቅርጽ ያልናቸው (ፖለቲካ፣ ርእዮተ ዓለም፣ ሕግ፣ ኪነ ጥበብ፣ ስነ ጽሑፍ፣ ስነ ምግባር፣ ሐይማኖት) በዚህ ኢኮኖሚያዊ መሰረት ተጽእኖ ስር ናቸው ይላል፡፡[13] ስለዚህም በሰው ልጆች ታሪክ የለውጥና እድገት መንስኤዎችን ከኢኮኖሚያዊ፣ ቴክኖሎጂያዊ እና ባጠቃላይ ከቁሳዊ ምክንያቶች እና በጎሳዎች፣ መደቦች፣ ሃገሮች መሃከል በቁሳዊ ምክንያት የሚደረጉ ግጭቶችን ውስጥ ይፈልጋል፡፡
ብዙ ሃያስያን ይህ ሲበዛ የተቃለለ ምልከታ ነው ይላሉ፡፡ ማርክስ ላእላይ ቅርጽ ያላቸው ሃሳቦች፣ ባሕሎችና ሌሎችም ነጥቦች የህብረተሰቡን መስመር በመቀየስ የኢኮኖሚያዊ መሰረቱን ያክል ወሳኝነት አላቸው፡፡ እንዲህ ካልሆነ ለምን ማርክስ ሃሳቦቹን አምርሮ ለማስፋፋት ይሰራል ብለው ይጠይቃሉ፡፡
ለዚህ ምላሽ የማርክስ አጋር የሆነው ፍሬደሪክ ኢንግልስ የሚከተለውን ይላል፡
“እንደ ቁሳዊ የታሪክ ምልከታ ከሆነ የመጨረሻው (ዋናው) የታሪክ ወሳኙ ነጥብ የእውነተኛ ሕይወት መመረትና መራባት ነው፡፡ ከዚህ በዘለለ እኔም ማርክስም አልተናገርንም፡፡ እናም ማንም ይህን ጠምዝዞ ኢኮኖሚያዊ ነጥቡ ብቻ ነው ወሳኙ ቢል፣ ሃሳቡን ትርጉም ወደሌለው፣ ረቂቅ እና የማይገባ ሐረግ ቀየረው ማለት ነው፡፡”[14]
ሆኖም እንዲህ ከተባለ ደግሞ ማርክሲዝም ሌላ እንከን ይመጣበታል፡፡ ላእላይ ቅርጹ መሰረቱ ላይ ተጽእኖ የሚያሳድር ከሆነ ማርክስ ደጋግሞ የማህበረሰብ ታሪክ የኢኮኖሚያዊ መደቦች ግጭት ነው የሚለው ላያስፈልግ ነው፡፡ ይህ መላምቱም ተቀባይነት የለውም፡፡

ታሪካዊ ወሳኛዊነት

የማርክስ የታሪክ ንድፈ ሃሳብ የታሪክ ወሳኛዊነት (Historical determinism)[15] እና ከዲያለክቲካል ቁሳዊነት የማህበራዊ ለውጥ መንገድ ነው ከሚለው ጋር ተሳስሮ የሚገኝ ነው፡፡[16]ይህን በአንድ እድገት ደረጃ የምርት ኃይሎች ካለው የምርት ዘይቤ ግንኙነት ጋር ግጭት ይፈጥራሉ፣ ይህም የማህበራዊ አብዮት ዘመንን ያስጀምራል፡፡ የኢኮኖሚያዊ መሰረቱ ላይ የተከተለው ለውጥ ረዘመም አጠረም ከግዜ በኋላ ወደ አጠቃላይ የላእላይ ቅርጽ ለውጥ ያመራሉ፡፡[17] ስለዚህም ሁሉ ነገር ቀድሞ በዚህ መልኩ የተወሰነ ነው ማለቱ ነው፡፡
ይህ ሃሳብ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ተቀባይነቱን አጥቷል፡፡ ካርል ፖፐር ታሪካዊ ወሳኛዊነትን የታሪክ መጪው እርምጃን ማወቅ የማይቻል በመሆኑ ይህን ንድፍ ሃሳብ አጣጥሎታል፡፡ ጌሪ ሃበርማስም በበኩሉ ኸርነስት ናጄልን በማጣቀስ ታሪክ ቀድሞ የታወቀ ነው የሚለው የታሪካዊ ወሳኝነት ንድፈ ሃሳብን ስህተት ያሳየናል፡
“በመጀመርያ በታሪክ የእድገት (የለውጥ) ህጎች ወይም መስመሮች የሉም፡፡ የሆኑ ክስተቶች ከመሆናቸው በፊት በትክክል ልንገምትበት የምንችልበት መርሆዎች ወይም መሰረታዊ ጭብጦች የሉም፡፡ ሁለተኛ መጪውን ታሪክ መተንበይ አይቻለም፣ ምንም እንኳ ተደጋግሞ ተቃራኒው ቢባልም፡፡ ያለፉ ክስተቶች ወይም እንዲህ የመሰሉ መረጃዎች መጪውን ግዜ አይወስኑም፡፡ አራተኛ ያልተጠበቁ ወይም ከተለመደው ወጣ ያሉ ክስተቶች የታሪክ አካል ናቸው፡፡ አምስተኛው መከራከርያ የወሳኛዊነት ዓለም ጭብጥን ከሰው ልጆች ነጻነትና ሞራላዊ ኃላፊነት ጋር እንዲሄድ አድርገው ሊጠቀሙበት ሲሞክሩ የሚፈጠረው ግጭት ነው፡፡ እንዲህ አይነቱ ነጻነት ከሰው ልጆች ምርጫ የሚመነጭ የታሪክ የፈጠራ ገጽታ ያስፈልገዋል፡፡ … ናጄል በድጋሚ ወሳኛዊነት በዘመናዊ ፊዚክስ የገጠመው ተቃውሞ የታሪክ ምሁራን ላይ ተጽእኖ በማሳደር ቁልፍ ሚና ተጫውቷል፡፡”[18]

የግለሰብ መብችን መጨፍለቅ

በኮሚዩኒስት ማኒፌስቶ ላይ 10 መደረግ ያለባቸው ነጥቦችን ብሎ ያስቀመጣቸው የግለሰብ መብቶች ጥሰት ናቸው፡፡ የመሬት ባለቤትነትን መብት ማጥፋት፤ በደሞዝ ልክ እየጨመረ የሚሄድ ግብር፤ የውርስ መብት ማጥፋት፤ ሃብት መውረስ፤ ገንዘብ ነክ የሆኑ ድርጅቶችን (ባንኮችን) በመንግስት ቁጥጥር ስር ማድረግ፤ መገናኛና ትራንስፖርት አገልግሎትን በመንግስት ቁጥጥር ስር ማድረግ ወዘተ. የሚሉ ይገኙበታል፡፡ ነጻ ትምህርት እና ሕጻናትን ከፋብሪካ ሥራ መከልከል የሚለው ጥሩ ነገር ከተናገረ በኋላ ትምህርትን ከኢንዱስትሪ ጋር ማዋሃድ ይላል፣ ሌላ ትምህርት የፈለገስ ምን ሊሆን ነው?
ኢኮኖሚ የነጻነት አምድ እንደመሆኑ ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነትን መነጠቅ ሰብአዊ መብትህንም ማጣት ነው፡፡ ብዙ ኢኮኖሚስቶች የገበያ ልውውጥ መሪ ባልሆነበት አገር ጨቋኝ ፖለቲካዊ መሪዎች ማስገደጃ ኃይል ባለቤት እንዲሆኑ ያደርጋል ይላሉ፡፡ ተጠቃሹ ፍሬደሪክ ሃይክ ነው፡፡[19]ሶሻሊስት የሚባለው ጆን ማይናርድ ኬንስም ሳይቀር ይስማማበታል፡፡[20]ሁለቱም በአንዲት ሃገር ነጻነት እንዲያብብ ካፒታሊዝም ወሳኝ ነው ብለው ያምናሉ፡፡ በተጨማሪም ሃገራችንን ጨምሮ ማርክሲስታዊ አመለካከት እንዴትና የት እንደሚያደርስ በተግባር የምናውቀው ስለሆነ ተጨማሪ ማለት አያስፈልግም፡፡

የጋርዮሻዊነት ትግበራ

በተለይ አናርኪስቶች (መንግስት አያስፈልግም፣ በሰፈርና በሕብረት ስራ ተደራጅቶ ሕብረተሰቡ እራሱን በራሱ ያስተዳድር የሚሉ) ማርክሲስታዊ ኮሚውኒዝም መጨረሻ ላይ ወደ ማስገደድና የመንግስት የበላይነት ያመራል ብለው ይወቅሱት ነበር፡፡ ሚካኤል ባኩኒን የተባለው ታዋቂ አናርኪስት ማርክሲስታዊ መንግስታት ሕዝቡን አዲስና ቁጥራቸው ብዙም ባልሆኑ ባላባቶች አምባገነናዊ አገዛዝ ስር ወደ ማስገባት ነው የሚያመሩት ብሎ ነበር፡፡ በተጨማሪም እኚህ አዲስ ባላባቶች ከሰርቶ አደሩ ቢገኙም አዲስ የጨበጡት ኃይል ለሕብረተሰብ ያላቸውን ምልከታ በአብዩ እንደሚቀይርና ብዙሐኑን ሰርቶ አደሮች ዝቅ ዘድርገው እንዲያዩ እንደሚያደርጋቸው ባኩኒን ገልጾ ነበር፡፡[21]ስለዚህም በተግባርም እንደታየው የሰርቶ አደሩ አምባገነንነት የሚወልዶው ጋርዮሻዊነት (ኮሚውኒዝም) ተግባራዊነት የማይኖረው የከሸፈ መላ ምት ነው፡፡

ስነ ምግባራዊ ሂስ

ግብ አካሄድን ያፀድቃል የሚለው፣ ማለትም ለመልካም ግብ እስከሆነ ደረረስ ክፉ ማድረግ ጥሩ ነው በሚል እምነት ማርክሲስታውያን ተወቅሰዋል፡፡ ሆኖም ግን ይህ ከማርክስ የመነጨ አይደለም ብለው የሚከራከሩ አሉ፣ ማርክስ እንደሚከተለው ጽፏል በማለት፡
“ፍትሐዊ ያልሆነ አካሄድ የሚጠይቅ ግብ ፍትሐዊ ግብ አይደለም፡፡”[22]
ሊዮን ትሮትስኪም በበኩሉ ዲያለክቲካል ቁሳዊነት የአካሄድና የግብ ጥንዳዊነት የለውም፡፡ ግቡ በተፈጥሮ ከታሪካዊ እንቅስቃሴ የሚመነጭ ነው፡፡ በተፈጥሮ አካሄዱ የግቡ ታዛዥ ነው ብሎ ነበር፡፡[23]
ቃላት የተደረደሩት እንዲህ ቢመስሉም ፍትሃዊ ነው የሚሉት እስከምን ይደርሳል የሚለው እንዳለ ሁኖ ተከታዮቻቸው ካሳዩት አካሄድ ወቀሳ ነጻ አያወጣቸውም፡፡

ስነ እውቀታዊ (Epistemological) ሂስ

መደብ ወይስ ሕብረተሰባዊ ቅርጽ (ካስት)?

አንዳንዶች የማርክሳዊ የሕብረተሰብ አመለካከት መሰረታዊ ስህተት አለበት ይላሉ፡፡ ለምሳሌ መደብ እያለ የሚለየው በምእራቡ ህብረተሰብ የሌለ እና ከምስራቁ (ሕንድ) በዘር የሚወረስ የህብተረሰብ ቅርጽ (ካስት) ስርአት ጋር አንድ አድርጎ አቅርቦታል፡፡ በማርክስ ስሌት አንዱ መደብ ሌላው መደብ ላይ በማያሴሩ ምክንያት ወደ ግጭት ይሄዳሉ ሲል እውነቱ ግን በዛው መደብ ያሉ ሰዎች ከለሌላኛው መደብ ላይ ለመድረስ ከመደባቸው ውስጥ ካሉት ጋር ነው የሚፎካከሩት፡፡ ማርክስ በካፒታሊስት ማሕበረሰብ ያስቀመጣቸው የሚለዩ ናቸው፡፡ አባሎቻቸው ከፍና ዝቅ የሚሉ ናቸው፡፡ የመደብ አባልነት በዘር የሚወረስ አይደለም፡፡ የሚመደበው በግለሰብ ደረጃ የእለት ክንውኑ በሚያስገኝለት ተቀባይነት አንጻር ነው፡፡ ሕዝቡ ምርት በመግዛትና በመሸጥ ማን የፋብሪካዎች ኃላፊ መሆን እንዳለበት ይወስናል፣ ማን በቲያትር መተወን እንዳለበት ይወስናል፣ ማን በፋብካ መስራት እንዳለበት ይወስናል፡፡ ሃብታሞች ድሃ፣ ድሆች ሃብታም ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ ባርነት መወገዱ ላይ ሁሉም ባሮች ተጠቃሚነት አላቸው፣ ሆኖም ግን እንዲህ ያለ ግጭት ከሕግ በፊት ሁሉም እኩል በሆነበት ማሕበረሰብ አይኖርም፡፡[24]

ሳይንስ ወይስ ዶግማ?

ፖፐር እንደሚሞግተው ከሆነ ታሪካዊ ቁሳዊነት ሱዶሳይንስ (ሳይንሳዊ ዘዴዎችን ሳይከተል እንደ ሳይንስ የቀረበ የተሳሳተ እምነት) ነው ይለዋል፣ ምክንያቱም ደግሞ የሐሰት መሆኑን ማሳየት አይቻለምና፡፡ ፖፐር ማርክሲስታዊነት መጀመርያ ላይ ሳይንሳዊ ነበር፣ ማለትም ማርክስ ተንባይ የሆነ ንድፈ ሃሳብ አቅርቦ ነበር፡፡ ግምቶቹ (ትንቢቶቹ) እውን ሳይሆኑ ሲቀሩ ንድፈ ሃሳቡ ውድቅ መደረጉ (የሐሰት መሆኑን ከመታየት)ያወጣው ለእርሱ ሁኔታ ብቻ የሚሰሩ መላምቶች (አድ ሆክ ሃይፖተሲስ) በመጨመር ከእውነታው ጋር እንዲገጥም ሙከራ ተደርጓል፡፡ በዚህም መልኩ መጀመርያ ላይ ሳይንሳዊ ንድፈ ሃሳብ የነበረው ወደ ሱዶ-ሳይንሳዊ ዶግማ ሊወርድ ችሏል፡፡[25]
ማርክሲስታውያን ለዚህ ሂስ የሚሰጡት ምላሽ ሁሉም ማህበራዊ ሳይንሶች እንደ አካላዊ ሳይንስ ሙከራዎች ስላልሆኑና የተወሳሰቡ ክስተቶች ትንተና ላይ ስለሚመሰረቱ ሐሰትነታቸውን ማሳየት አይቻልም ይላሉ፡፡ ሆኖም ግን ፓውፐር ይህን ተቀብሎ ይህንኑ መረጃ ማእከላዊ (መንግስታዊ) እቅድ አውጪነትንና ሁሉን አቀፍ ታሪክ ተንታኝ ርእዮተ ዓለሞችን ለማውገዝ ተጠቅሞበታል፡፡[26]

ማርክስ ለምን ይወደዳል?

ቅሉ እንዲህ ከሆነ፣ ማርክስ በተግባርም በንድፈ ሃሳብም እንደተሳሳተ ማየት ከቻልን ለምን ዛሬ ድረስ ጽሑፎቹና መልእክቶቹ የሰው ልጆችን ልብ ይገዛሉ ብለን መጠየቃችን አይቀሬ ነው፡፡ ምላሹን እራሱን ጸረ-ካፒታሊስት እንደሆነ የሚቆጥር ግን ማርክሲስት ያልሆነ ሰው ከሰጠው ማብራርያ እናገኘዋለን፡፡[27] ይህ ጸሓፊ ስለ ካፒታሊዝም ያለውን ምልከታ አልቀበልም፣ ሆኖም ግን ቀድሞ ማርክሲስት የነበረ በመሆኑ የማርክስ አማላይነትን ለመመስከር ብቁ ነው፡፡ ማርክስ በሶስት ዋና ምክንያቶች ይወደዳል፡ ትርጉም፣ ዓላማ እና ቅኔ ወይም ውበት፡፡
ማርክስ ለአንባቢዎቹ በታሪክ ትርጉም እና ቦታ ይሰጣቸዋል፡፡ የትልቅ፣ የዘመናት ጅረት አካል እንደሆኑ እንዲሰማቸው ያደርጋቸዋል፡፡ ለማንኛውም የሚደርስባቸው ተስፋ መቁረጥና እምነት ማጣት ምትክ ይሆናቸዋል፡፡ “እኛ ማን ነን?”፣ “ለምድን ነው እዚህ የመጣነው?” ለሚሉት ጥያቄዎች መልስ ይሆናቸዋል፡፡
በማርክስ ታሪክ የመደብ ትግል ሰንሰለት ነው በዚህ ትግል አካል መሆን ደግሞ ዓላማ ይሰጣል፡፡ መደብ አልባ ምድራዊ ገነት የመፍጠር ዓላማ፡፡
ሌላው የማርክስ ጥንካሬ ታሪክ አተራረኩ ነው፡፡ ስለ ፖለቲካ፣ ፍልስፍናና ኢኮኖሚክስ የሚጽፍ እንደመሆኑ ደረቅ አጻጻፍ መከተል ነበረበት፡፡ ሆኖም ግን ማርክስ ሲጽፍ ውበት አለው፡፡ ለምሳሌ ኮሚኒስት ማኒፌስቶ ላይ፡ “ብዙሃኑ የሚያጡት ምንም ነገር የለም ከታሰሩበት ሰንሰለት በቀር፡፡ ድል የሚያደርጉት ዓለም አላቸው፡፡” ይላል፡፡ በዚሁ ስራ ብቻ እንኳ ሌላ ብዙ ምሳሌዎችን መጥቀስ ይቻላል፡፡
ሆኖም ግን ሰዎች ከዚ አሻግረው በስሜት ብቻ ሳይሆን በመሰረተ-እውነትም መመራት ነበረባቸው፡፡ ማርክስ “ሃይማኖት የሕዝቡ አደንዛዥ እጽ ነው፡፡” የምትል አባባሉ ይታወቃል፣ ፖል ሳሙኤልሰን የተባለ ኢኮኖሚስት ደግሞ “ማርክሲስታዊነት የማርክሲስታውያን አደንዛዥ እጽ ነው፡፡” ብሎ ነበር ከዚህ ሁሉ ትንተና እና ያደረሰው ውድመት በኋላ አሁንም ሲያመልኩት በመታዘብ፡፡
 አሁን ስንጀምር ያጣቀስነው የማርክስ አባባል ተገልብጦ እራሱ ላይ ሲሰራ ለማየት ችለናል ብዬ ተስፋ አደርጋለው፡፡
በዚህ ጽሑፍ ያሉ ዋና ጥቅሶች ከተለያዩ መጣጥፎች የተወሰዱ ናቸው፡፡

መኢአድና ሰማያዊ ፓርቲ በቤንሻንጉል ተፈናቃዮች ጉዳይ በመንግስት ላይ ክስ ሊመሰርቱ ነዉ

$
0
0

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በአማራ ተወላጆች ላይ በደረሰው መፈናቀል ተጐጂዎች ፍትህ እንዲያገኙ መኢአድና ሰማያዊ ፓርቲ ክስ ሊመሰርቱ ነው፡፡ ጠ/ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ በአስረጂነት ፍ/ቤት እንደሚቀርቡ ተጠቁሟል… የመኢአድ ፕሬዚዳንት ኢ/ር ሃይሉ ሻውል እና አለማቀፍ የህግ ባለሙያው ዶ/ር ያዕቆብ ሃ/ማርያም ከትላንት በስቲያ በጋራ በሠጡት መግለጫ፤ መረጃዎች ከተሰባሰቡና ከተደራጁ በኋላ በፌደራሉ ፍ/ቤት ወይም በክልሉ ፍ/ቤት ሁለት ዓይነት ክሶች እንደሚመሰረቱ ተናግረዋል፡፡ ክሱ የሚመሠረተው በዋናነት የዜጐች ከቦታ ቦታ የመዘዋወርና የመኖር መብት የሚደነግገውን የህገመንግስቱን አንቀጽ መነሻ በማድረግ ሲሆን በወንጀል እና በፍትሃብሔር ተከፋፍሎ ይቀርባል ተብሏል፡፡

JPEG - 24.2 kb

ጠ/ሚ ኃ/ማርያም በአስረጂነት ፍርድ ቤት እንዲቀርቡ እንጠይቃለን ብለዋል

በወንጀል ክሱ ላይ በተለይ ከዘር ማጥፋት ጋር የተያያዙ የሰብአዊ መብት ጥሰቶች እንደሚካተቱ የገለፁት ዶ/ር ያዕቆብ፤ ከተበዳዮች ከሚሰባሰቡት መረጃዎች በተጨማሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም ከዚህ ቀደም ፓርላማ ቀርበው በክልሉ ዜጐች መፈናቀላቸውንና ችግሩን የፈጠሩት ኪራይ ሰብሳቢዎች መሆኑን በይፋ በመግለፃቸው ሌላ ማስረጃ ሳያስፈልግ ራሳቸው ፍርድ ቤት ቀርበው አስረጂ ይሆናሉ ብለዋል – ዶ/ር ያዕቆብ ሃ/ማርያም፡፡ ወንጀሉ በሰው ዘር ላይ ከተፈፀሙ ከባድ ወንጀሎች ተርታ የሚመደብ መሆኑን ያመለከቱት የህግ ባለሙያው፤ በኢትዮጵያ የወንጀለኛ መቅጫ ህግ ላይ ድርጊቱን የፈፀሙ እስከሞት ቅጣት ሊቀጡ የሚችሉበት ሁኔታ መቀመጡን ገልፀዋል፡፡ በሁለተኛ ደረጃ የሚቀርበው የፍትሃብሔር ክስም በዋናነት ለወደመው ንብረትና ለደረሰው ሰብአዊ ቀውስ ካሣ የሚያስገኝ እንደሚሆን ተጠቁሟል፡፡

የክሱ አካሄድ በሃገሪቱ ያልተለመደ መሆኑን የገለፁት ዶ/ር ያዕቆብ፤ በአንድ ሰው ከሣሽነት ሌሎች ተመሳሳይ በደል የደረሰባቸው ወገኖች ፍትህ የሚያገኙበት አይነት ክስ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ ክሱ ከሚመሠረትባቸው የመንግስት አካላት መካከል የፌዴራል ጉዳዮች ሃላፊዎች፣ የፖሊስ አባላት እንዲሁም የክልሉና የወረዳው ሃላፊዎች ዋናዎቹ እንደሚሆኑ ተገልጿል፡፡ ክሱን መቼና እንዴት ይጀመር የሚለውን ገና ጉዳዩ እየመከርንበት ነው ያሉት ዶ/ር ያዕቆብ፤ በመጀመሪያ የተበደሉ ሰዎችን ውክልና ማግኘት እንደሚጠበቅባቸውና ከዚያም መረጃዎችን አሰባስበው በሁለት የህግ ባለሙያዎች በመታገዝ ክሱን እንደሚመሰርቱ ተናግረዋል፡፡

ከክሱ ምን ትጠብቃላችሁ ተብለው ለተጠየቁት ሲመልሱም፤ ውጤቱ ምን ይሆናል የሚለው በሂደት የሚታይ ጉዳይ መሆኑን የተናገሩት ባለሙያው፤ ክሱ ተቀባይነት ካጣ ወደ አለማቀፍ ፍርድ ቤት እንደሚያመሩ ዓለምአቀፍ የህግ ባለሙያው ገልፀዋል፡፡ በአማራ ተወላጆች ላይ በደቡብ ክልል በቤንቺ ማጅ ጉራፋርዳ አካባቢ እየደረሰ ያለው መፈናቀልና የሰብአዊ መብት ጥሰት ዛሬም አለመቆሙን ያስታወሱት የመኢአድ ፕሬዚዳንት ኢ/ር ሃይሉ ሻውል በበኩላቸው፤ በሀገሪቱ ዘረኝነት እየተስፋፋ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ መላው የኢትዮጵያ ህዝብ የዚህ ድርጊት ተባባሪ እንዳይሆንም ጥሪ አቅርበዋል – ኢንጂነሩ፡፡


የሰሞኑ ሙስና በፖለቲከኞች ዐይን ይሄን ይመስላል፡፡

$
0
0

የመንግስት መዋቅር በሙስና የተዘፈቀ ነው የሚል ትችት በተደጋጋሚ ትሰነዝራላችሁ፡፡ ኢህአዴግ ዋናዎቹን ትቶ በትናንሽ ሙሰኞች ላይ ነው የሚያተኩረው፣ይህ ደግሞ ሙስናን እየተከላከለ ነው አያሠኘውም ትላላችሁ…. ከዚህ አንፃር ሠሞኑን በገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን ከፍተኛ ሃላፊዎችና ባለሃብቶች ላይ የተወሠደው እርምጃ የዚህ ትችትና ምክር ውጤት ነው ማለት ይቻላል? ይህ እንግዲህ አንደኛ በጣም የገዘፈን ነገር እንዲሁ መነካካት ነው፡፡ ምክንያቱም ኢህአዴግና ስርአቱ፣ አባሎቼና ደጋፊዎቼ የሚላቸው አሉ፡፡ እነሡ ሃገሪቱን በሙሉ እንዲበዘብዙ ድጋፍ ይሰጣቸዋል፡፡

“ኢህአዴግም እንደ ድርጅት ሙሠኛ ነው” ፕ/ር በየነ ጴጥሮስ -የመድረክ አመራሮች አባል

ከዚህ አንፃር የሠሞኑ እርምጃ መነካካት ነው፡፡ ዋናውን የሙስና ሠንሠለት ለመበጣጠስ የጀመረው እንቅስቃሴ ነው ለማለት ገና ነው፡፡ እስካሁን ባሳለፈው 21 የስልጣን አመታት አንዳንዴ በፖለቲካውም በዲፕሎማሲውም ሲጨንቀው ከሹመኞቹ ውስጥ ጭዳ የሚያደርጋቸው አሉ፡፡ እነዚያን እየሠዋ ይሄው እርምጃ እየወሠድኩ ነው፤ በማንም ላይ ቢሆን መረጃ እስካለ ድረስ እርምጃ ለመውሠድ ዝግጁ ነኝ የሚል የፖለቲካ ጨዋታ አለው፡፡ በሽግግሩ ወቅት ከአቶ ታምራት ላይኔ አንስቶ፣ አቶ ስዬ፣ ሌሎቹንም ከህወሃት ጋር የተጋጩትን ሲያስር ሲፈታ ነው የኖረው፡፡ በዚያ ሠሞን ኢህአዴጐች ጉባኤ እያካሄዱ ነበር፡፡ ይህ እርምጃ ደግሞ ከጉባኤው ተከትሎ የመጣ ነው፡፡ ከዚህ አንፃር የፖለቲካ ጉዳይ እንዳለበት ምልክትም ሊሆን ይችላል፡፡ የፍትህ ሚኒስትሩ አቶ ብርሃንም እንዲነሡ ተደርጓል፡፡ የገቢዎች ባለሥልጣን እቃዎችን ከቀረጥ ነፃ የማስገባት ነገር ስላለው ከለጋሾች ጋር ያነካካል፡፡

እናም ጫናውን ትንሽ ለማስተንፈስም ጭምር ያደረጉት ሊሆን ይችላል፡፡ ስለዚህ ሁሉንም በሂደት የምናየው ይሆናል፡፡ እርምጃው በዚህ ላይ ብቻ የሚቆም ከሆነ በመሠረቱ የሚያደላው ፖለቲካዊ ፋይዳው ነው፡፡ ሙስና እንግዲህ አዲስ አበባንም ሆነ ሌሎች ከተሞችን ያጣበበ ነው፡፡ ሁሉም ጋ ሄደው እርምጃ የሚወስዱ ከሆነ እሠየው የሚያሠኝ ነው፡፡ በኛ እምነት ይሄ ሁሉ ከበርቴ ሚሊየነርና ቢሊየነር ዝም ብሎ እየፈላ ያለው፣ የሃገሪቱን ህዝብ ሃብትና ገንዘብ እየበዘበዘ ነው፡፡ ሙሰኝነቱ ነው አብዛኛውን እዚህ ያደረሠው፡፡ ኢህአዴግም እንደ ድርጅት ሙሠኛ ነው፡፡ ኪራይ ሣይከፍል የሚጠቀምባቸው ትላልቅ ህንፃዎች አሉ፡፡ እነሱ የህዝብ ንብረቶች ናቸው፡፡ ኢህአዴግ ከዋናው ፅ/ቤቱ አንስቶ ሌሎች ስራዎችን የሚሠራባቸውን ቢሮዎች እንደማንኛውም ፖለቲካ ፓርቲ ኪራይ እየከፈለ ነው የሚጠቀመው? ይህ እንግዲህ በምርመራ ጋዜጠኞች መጣራት ያለበት ነገር ነው፡፡

እኔ እስከማውቀው ድረስ ግን እንደማይከፍሉ ነው፡፡ በቅርብ ጊዜ የተለወጠ ነገር ከሌለ እያንዳንዱ የኢህአዴግ ካድሬ ገብቶ የሚኖርባቸው ያኔ ከደርግ የወረሣቸዉ ትልልቅ ቤቶች ኪራይ ይከፈልባቸዋል? እኔ እስከማውቀው ድረስ ሣይከፍሉ ነው የሚጠቀሙት፡፡ መረጃው በጋዜጠኞች ሊቀርብ ይገባዋል፡፡ ቦሌ ያሉ የድሮ ትልልቅ መኳንንት የሠሯቸውን ቪላ ቤቶች፣ ከትግሉ መልስ እየተሽቀዳደሙ እንደገቡበት ነው የምናስታውሠው፡፡ ከዚህ በላይ ሙሠኝነት አለ እንዴ? የህዝብ ንብረት እኮ ነው ወይ ለባለቤቶቹ አልተመለሠ? ኢህአዴግ ሙሠኛ ነው ልንል የሚያስችሉን እነዚህ ነጥቦችና ሌሎችም ናቸው፡፡ ሙሠኝነት በኢትዮጵያ ውስጥ መሠረቱ በጣም ሠፊ ነው፡፡ አደገ የሚባለው ኢኮኖሚ፣ ተሠሩ የሚባሉት ሠማይ ጠቀስ ፎቆች መሠረታቸው ሙሠኝነት ነው፡፡

ከበርቴ ነን ከሚሉት የአንዳንዶቹን መነሻ እናውቃለን፡፡ ራሱ ገዥው ፓርቲ የሚያንቀሣቅሳቸው የኢንዱስትሪና የንግድ ድርጅቶች ሣይቀሩ የሙስና ጉዳይ ያለባቸው ናቸው፡፡ አንዳንድ ወገኖች ዘግይቷል ቢሉም በገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣናት ላይ ሰሞኑን የተወሠደው እርምጃ ኢህአዴግ የሙስና ችግሮችን ለማፅዳት መቁረጡን አያመለክትም? በአሁኑ ደረጃ እርምጃ መውሠድ ጀምሯል ማለት አንችልም፡፡ ምክንያቱም አሁንም ትላልቅ አሣዎች አሉ፡፡ በዚህ ዘመን እኮ የኢህአዴግ አባል ወይም ደጋፊ መሆን ማለት ከበርቴ መሆን ነው፡፡ ብዙዎቹ በዚህ መሠረት ተጠቅመዋል፡፡ እንዳሁኑ ዓይነት እርምጃዎች ከቀጠሉ መሠረቱ ሊናጋ ነው ማለት ነው፡፡ ፓርቲው የህዝብ ሃብትን ለራሱ እየተጠቀመ ከመሆኑም በላይ ወዳጆቹን እንዴት እየጠቀመ ነው የሚለውንም ማየት ያስፈልጋል፡፡ ከዚህ አንፃር ኢህአዴግ ራሱን ማፅዳት ጀመረ ማለት ይቸግራል፡፡ እንዲያ ከሆነ ከውስጥ ትልቅ ቀውስ ተፈጠረ ማለት ነው፡፡

“ይሄ የዶሮ ትራፊ ነው፤ ትልቁ ገንዘብ የት ነው ያለው?” ኢ/ር ሃይሉ ሻውል -

የመኢአድ ፕሬዚዳንት በሙስና ተጠርጥረው የተያዙት ሠዎች ጉዳይ የፖለቲካ ግንኙነት ያለው ይመስላል፡፡ ይህ ደግሞ አምባገነን መንግስት ባለበት ሁሉ የሚደረግ ነው፡፡ በደርግ ጊዜም የማይፈለግ ሠው እንደዚህ ይደረግ ነበር፡፡ በእርግጥም የተያዙት ሠዎች የተጠረጠሩበት ጉዳይ እውነት ከሆነ እርምጃው ይቀጥላል ብዬ አምናለሁ፡፡ በሙስና የደለቡትን አንስተው ያሣዩን ይሆናል፡፡ ይህ ካልሆነ ግን ነገሩን ሙስና ብቻ ብሎ ለመቀበል ይቸግራል፡፡ በቅርቡ ለፓርላማ በቀረበው ሪፖርት ላይ፣ የፌዴራል ኦዲተሩ በመንግስት መስሪያ ቤቶች ከፍተኛ የገንዘብ ጉድለት መኖሩን ጠቁሟል፡፡ ዛሬ እነዚህ ሠዎች ቤት አንድ መቶ ሺህ ብር ተገኘ፤ ሲባል ይሄ የዶሮ ትራፊ ነው፤ ትልቁ ገንዘብ የት ነው ያለው? ከዚህ ቀደም የአለም ሚዲያዎች ብዙ ቢሊዮን ዶላር ከሃገር እንደወጣ ነግረውናል፤ እኔ ቁጥሩን አላስታውሠውም፡፡ ይህንንና አሁን የተነገረውን ስናስተያይ ገና ጫፉም አልተነካም፡፡

“አሣ ማጥመጃው ትልልቅ አሣዎችን የሚያጠምድ ከሆነ እንተባበራለን” ዶ/ር ያዕቆብ ኃ/ማሪያም -

አለማቀፍ የህግ ምሁር በሙስና በተጠረጠሩት ላይ መንግስት በወሠደው እርምጃ ምን አስተያየት አለዎት? የተወሠደው እርምጃ የሚቀጥል ከሆነ በእውነት የሚመሠገን ነው፡፡ የተወሠደው እርምጃ ግን ካለው ሁኔታ ጋር ሲመዛዘን ኢምንት ነው ማለት ይቻላል፡፡ አሁን የታየው ኢምንቱ ነው፡፡ ይህ ተጠናክሮ የሚቀጥል ከሆነ እሠየው የሚያስብል ነው፡፡ ለዚህ ሁሉም ኢትዮጵያዊ መተባበር አለበት፡፡ ለፖለቲካ ጥቅም ወይም በፖለቲካ ግጭት ምክንያት የተፈጠረ ከሆነ ግን ለኢትዮጵያ ህዝብ የሚጠቅመው ነገር የለም፡፡ ዝም ብሎ ጊዜ ማባከን ነው፡፡ መዘንጋት የሌለበት ግን ከእነዚህ የበለጡ ትላልቅ አሣዎች ዛሬም አሉ፡፡ እነዚህ አሣዎች እስካሁን ድረስ አልተነኩም፡፡ አሣ ማጥመጃው እነዚህን ትልልቅ አሣዎች የሚያጠምድ ከሆነ፣ እኛም እሠየው ብለን እንተባበራለን፡፡ አንዳንዶች የጉምሩክ አሠራር በራሱ ለሙስና ምቹ ነው ይላሉ፡፡ እርስዎስ? በእርግጥም ጉምሩክ አሠራሩ በራሱ ለሙስና በር ከፋች ነው፡፡ ራሱ ከሣሽ ነው፣ ዳኛ ነው፡፡ መጀመሪያውኑ ለሙስና አመቺ ሆኖ የተዋቀረ ነው፡፡ ያዋቀሩት ሠዎች ግልፅ ባልሆነ መንገድ የህዝቡን ሃብት ለመንጠቅ ያደረጉትም ሊሆን ይችላል፡፡ እርግጥ ነው አሁን መንግስት ይህን ነገር ማጥፋት ከፈለገ መዋቅራዊ ለውጥ ማድረግ አለበት፡፡ መዋቅሩን በሙሉ መለወጥ አለበት፡፡ አንድ ሁለት ሠው በመክሠስ ብቻ ችግሩ የሚወገድ አይደለም፡፡ ሃገራችን ከዚህ ቀደም ሙስናን በተመለከተ በአለማቀፍ ደረጃ በጣም ጥሩ ሪከርድ ነበራት፡፡ አሁን በትራንስፓረንሲ ኢንተርናሽናል አመዘጋገብ ወደ 3ኛ ደረጃ ተጠግታለች፡፡ ይሄ በጣም አሣፋሪ ነው፡፡

“ገቢዎች ከመንግስትም በላይ ስልጣን የተሰጠው አካል ነው” አቶ ሙሼ ሠሙ – የኢዴፓ ሊቀመንበር

ፀረ ሙስና ኮሚሽን ሰሞኑን በሙስና በጠረጠራቸው ትላልቅ ባለስልጣናትና ባለሃብቶች ላይ የወሠደውን እርምጃ እንዴት ይመለከቱታል? ለኛ ይሄ ነገር የተለየ እውቀት የሚጠይቅ አይደለም፡፡ ስቴት ካፒታሊዝም ወይም መንግስታዊ ከበርቴ የምትለው ስርአት አይነተኛ መገለጫው ነው፡፡ ነጋዴውን ህብረተሠብ የሚያሸማቅቅ፣ የመንግስትን ሚና የሚያጐለብት ነው፡፡ የንግዱን ማህበረሠብ የመንግስት ባለስልጣን ጥገኛም እንዲሆን ያደርገዋል፡፡ ጉዳዩን ለማስፈፀም፣ ስራውንም ለመስራት ሣይወድ በግዱ የመንግስት ባለስልጣናት አሽከር ይሆናል፡፡ ነጋዴውና የንግዱ ማህበረሠብ እየተዳከመ መንግስት እንዲተካው ነው ጥረት እየተደረገ ያለው፡፡ መጨረሻ ላይ ይህ ስርአት ወዴት ነው የሚሄደው? ሂደቱ የመንግስት ባለስልጣናትን ከበርቴ የሚያደርግ ነው፡፡

ምክንያቱም ነጋዴው ችግሮቹን የሚፈታበትን መንገድ የሚያመለክት አይደለም፡፡ ባለሃብቱ በጥርጣሬ ነው የሚታየው፡፡ ታማኝ አይደለም፣ ብቁ አይደለም፣ ስርአት የለውም እየተባለ ነው፡፡ ግለሠብ ነጋዴውን በጥርጣሬና በስጋት የማየት አዝማሚያ አለ፡፡ ስግብግብ፣ ሌባ፣ ወንበዴ ወዘተ— ተደርጐ ነው የሚታየው፡፡ አሁን የተያዙት ባለስልጣኖች ይሄ ሁሉ ጉድ እያለባቸው ነው ነጋዴውን ሲያስፈራሩት፣ ሲዝቱበትና ኪራይ ሠብሣቢ ሲሉት የኖሩት፡፡ ስርአቱ ለእነዚህ ባለስልጣኖች መደራደሪያ በር ከፍቶላቸዋል፡፡ የፈለጉትን ነጋዴ በፈለጉት ጊዜ ጠርተው እያሸማቀቁና ስሙን እያጠፉ ህገወጥ በሆነ መንገድ መጠቀሚያ አድርገውታል፡፡ ይሄ ለኔ ሠዎችን የማሠርና ያለማሠር ጉዳይ ብቻ አይደለም፤ የስርአቱን የአስተሣሠብ ለውጥ የሚፈልግ ነው፡፡

የመንግስት ሹመኞችና ባለስልጣኖች የነጋዴውን ማህበረሠብ እንደ ሌባ፣ አታላይ፣ አጭበርባሪ፣ ኪራይ ሠብሣቢና ጠላት አድርገው የሚያዩበት ሁኔታ እስካልተለወጠ ድረስ ሙስናው ይቀጥላል፣ የመደራደሪያ በር ነው የሚከፍተው፡፡ አሁን የወሠዱት እርምጃ የሚደነቅ ነው፡፡ በሂደት ግን ውሣኔውንም የምናየው ይሆናል፡፡ አሁን የተደረገው “የበረዶ ጫፍ ነው” (Tip of the ice burg) እንደሚሉት ፈረንጆቹ፡፡ ትልቁ ጫፍ ገና ውሃው ውስጥ ነው ያለው፡፡ እንጀራ ጋግራ ከምትሸጥ ሴት ጀምሮ ገንዘብ የሚሠበሰብ መስሪያ ቤት፣ በዚህ ደረጃ መርከስና መበስበስ ውስጥ ከገባ፣ ሥርዓቱ ለአደጋ መጋለጡን ነው የሚያሳየው፡፡ በአጠቃላይ ስርአቱ የተጋረጠበት አደጋ መገለጫው ይሄ ሊሆን ይችላል፡፡ ከዚህም በፊት ሙስና ነበረ፤ ግን በመቶ ሚሊዮኖች አልነበረም፡፡ ነጋዴው አቤት የሚልበት ነፃና ገለልተኛ አካል ነበረው፤ አሁን ግን መስሪያ ቤቱ የራሱ ፖሊስ አለው፡፡

ዳኛ ነው የፈለገውን ነገር ይፈርዳል፡፡ አቃቤ ህግ ነው፡፡ ታዲያ እንዴት ከዚህ መስሪያ ቤት ጋር መስራት ይቻላል? ይሄ እኮ ከመንግስትም በላይ ስልጣን የተሠጠው አካል ነው፡፡ እነዚህ ሠዎች ዳኛ ናቸው፣ ፍርድ ቤት ናቸው፣ አቃቤ ህግ ናቸው፣ ፖሊስ ናቸው፡፡ ስርአቱ እንደፈለጉ እንዲፈልጡ እንዲቆርጡ ስልጣን ስለሠጣቸው፣ የድፍረታቸው ድፍረት ቤታቸው በሚሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ ማስቀመጣቸው ተነግሮናል፡፡ ስርአቱን እንዳለ በገንዘብ፣ በጉቦ መቆጣጠር የሚችሉበት ደረጃ ላይ መድረሣቸውን ነው የሚያመለክተው፡፡ አንድ ሌባ የሠረቀውን ነገር ቤቱ የሚያስቀምጠው እኮ በጣም ደፋር ሲሆን ነው፡፡ ይህ እንግዲህ የስርአቱ መገለጫ ነው፡፡ የተወሠደውን እርምጃስ እንደ መልካም ጅማሮ ማየት ይቻላል? ልትወስደው ትችላለህ፡፡ ግን ዋናው ችግር ግለሠቦቹ ላይ አይደለም፤ ሥርዓቱ ላይ ነው፡፡ ማህበረሠቡ ሙስናን የሚፀየፍ ፣ የመንግስት ባለስልጣናት ደግሞ ተገቢውን ክፍያ እያገኙ ስራቸውን እንዲሠሩ ማድረግ ነው ጠቃሚው፡፡ ይሄን ሠውዬ ብታስረው ገና የእሡ ርዝራዦችና መሠሎቹ በየመስሪያ ቤቱ አሉ፡፡

ይሄ ነገር እኮ ሲባል የከረመ ጉዳይ ነው፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩም አንድ እጄን ታስሬ እየሠራሁ ነው እስከማለት ደርሠው ነበር፡፡ ይሄ የሚያሣየው ምን ያህል ስር የሠደደ ችግር እንደሆነ ነው፡፡ ግለሠቦችን ማሠር ሙስናን ለመዋጋት አንድ መገለጫ ነው፤ ዋናው ነገር ግን የአስተሣሠብ ለውጥ ነው፡፡ ፍትሃዊ የሆነ የህግ ስርአት ሊበጅ ይገባል፡፡ ለአንድ መስሪያ ቤት የእግዚአብሔርን ያህል ጉልበት ተሠጥቶት እንዴት ሙስናን መዋጋት ይቻላል፡፡ ህገ ወጥ ነገር ለመስራት ሁሉም ነገር ተመቻችቶለታል፡፡ ይህ እያለ እንዴት ነው ሙስናን መታገል የሚቻለው፡፡ እርግጥ ስርአቱ በሽታውን ተረድቶ እርምጃ ለመውሠድ መነሣሣቱ የሚበረታታ ነው፡፡ ነገር ግን ጉዳዩ እየተጋነነ እየተወራ ነው፡፡ አንዳንድ ነጋዴዎችም እንዲበረግጉ እየተደረገ ነው፡፡

በዚህ ጉዳይ መንግስት ጥንቃቄ ሊያደርግ ይገባል፡፡ ሠዎቹ እንደየጥፋታቸው ፍትህ ፊት ቀርበው ተመጣጣኝ ቅጣት የሚያገኙበትን መንገድ መከተል ነው እንጂ ድራማ መስራት አይጠቅምም፡፡ ማጋነን፣ ነገሩን ከሚገባው በላይ መለጠጥ፣ ማህበረሠቡ በዚህ ጉዳይ የተዛባ መረጃ ኖሮት ያልተገባ ነገር እንዲናገር ማድረግ ተገቢ አይደለም፡፡ እነዚህ ነጋዴዎች ተገደው የገቡ ሊሆኑም ይችላሉ፡፡ ሌሎች ደንግጠውና በርግገው ሃገር ጥለው እንዲሄዱ የሚያደርግ መሆን የለበትም፡፡ እነዚህ ሠዎች አሁንም ገና ተጠርጣሪ ናቸው፡፡ ስርአት ባለው መንገድ ተይዘው የሚቀጡ ከሆነም መቀጣት አለባቸው፡፡ አሁን ግን የሚወራው ያለቀ ጉዳይ ተደርጐ ነው፡፡ ቀድሞ በፕሮፓጋንዳ ግለሠቦቹን ወንጀለኛ አድርጐ ደምድሞ፣ ፍርዱ ትርጉም እንዲያጣ ማድረግ አይገባም፡፡ እነዚህ ሠዎች እኮ በአንድ ጊዜ ስማቸው ወርዷል፣ የፕሮፓጋንዳው ሠለባ ሆነዋል፡፡ ሌሎችም እንዲበረግጉ ሆኗል፡፡ ነገር ግን መንግስት “እነዚህ ግለሠቦች ተይዘዋል፣ ሌላው ነጋዴ ተረጋግቶ ስራውን ይስራ” ማለት ነበረበት፡፡ ጠቅለል ብሎ ሲታይ የዚህ ሁሉ መሠረታዊ ችግር ይሄ መስሪያ ቤት የተሠጠው ከእግዚአብሔር ያልተናነሠ ስልጣን ነው፡፡ መንግስት አሁንም በነጋዴው ላይ ያለውን የተዛባ አመለካከት ይለውጥ፡፡



የ8 ሚሊዮን 100 ሺህ ብር ካሳ የተጠየቀበት የህዝበ ሙስሊሙ የመፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴዎች ክስ መዝገብ እንዲዘጋ ተደረገ፡፡

$
0
0

ሰበር ዜና

የስምንት ሚሊዮን አንድ መቶ ሽህ ብር ካሳ የተጠየቀበት የህዝበ ሙስሊሙ የመፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴዎች ክስ መዝገብ እንዲዘጋ ተደረገ..

በያዝነው ሳምንት የፌዴራል ከፍተኛ ፍ/ቤት የህዝበ ሙስሊሙን የመፍትሔ አፈላላጊ ኮሚቴዎች ላይ በደረሰው የስም ማጥፋት ወንጀል የመንግስት አካላትና ባለስልጣናትን ጨምሮ የተከፈተው የክስ ፋይል መዘጋቱን የኮሚቴዎቻችን ጠበቆች አስታወቁ፡፡

የህዝበ ሙስሊሙ መፍትሔ አፈላላጊ ኮሚቴዎች ጠበቃ ዋና አስተባባሪ አቶ ተማም አባቡልጉ እንደ ገለፁት የ8 ሚሊዮን 100 ሺህ ብር የሞራል ካሳ ለኮሚቴዎቹ ይገባል በማለት በ83 ሺህ ብር የከፈቱት መዝገብ መዘጋቱ አግባብ እንዳልሆነ ጠቁመዋል፡፡

መዝገቡን ለመክፈት ከዚህ ቀደም የተለያዩ እንግልቶች እንደደረሰባቸው የሚናገሩት ጠበቃው ጉዳዩ የማይመለከታቸው የፍ/ቤቱ ፕሬዝዳንትና ምክትል ፕሬዝዳንት ባልታወቀ ምክንያት መዘገቡን እንደዘጉት ይገልጻሉ፡፡

ከዚህም በተጨማሪ መዝገቡ ለፍ/ቤቱ ዳኛ ቀርቦ ያስከስሳል አያስከስስም ሳይባል እኛም በፍ/ቤቱ ሳንጠራ መዝገቡ መዘጋቱ መነገሩ ፍጹም ህገወጥ ተግባር ነው በማለት አክለው ገልጸዋል፡፡

ፍትህ ባለበት ሀገር ይህንን መሰል ተግባር መፈፀሙ እጅጉን እንዳሳዘናቸው ጠበቃ ተማም አባቡልጉ ተናግረዋል፡፡

ፍትህ በኢትዬጲያ በቁሙ ተቀበረ!!!

አላህ ይድረስልን!!!

Abu Dawd Osman

ሰሞኑን በሙስና ተጠርጥረው ሲፈለጉ ከነበሩት አንዱ ከአገር ሊወጡ ሲሉ ተያዙ

$
0
0

አዲስ አበባ ግንቦት  10 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ሞኑን በሙስና ወንጀል ተጠርጥርጥረው ሲፈለጉ ከነበሩት ግለሰቦች መካከል በድለላ ስራ ላይ የተሰማሩት አቶ ዳዊት መኮንን በሻሸመኔ ከተማ በቁጥጥር ስር ዋሉ..

የፌደራል ፖሊስ ለኢትዮጱያ ሬድዮና ቴሌቪዥን ድርጅት እንዳስታወቀው ግለሰቡ በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው እንደሚፈለጉ ሲያውቁ ሸሽተው ወደ ኬንያ ለመግባት ጥረት ላይ ነበሩ፥ጉዳዩን ሲከታተል የነበረው የፌደራል ፖሊስ በደረሰው ጥቆማ መሰረት ተጠርጣሪው ሻሸመኔ ላይ በቁጥጥር ስር አውሎአቸዋል፡፡

ተጠርጣሪው  በአዲስአበባ እና አዳማ በሚገኙ የግምሩክ  ጣቢያወች የድለላ ስራ ሲሰሩ የነበሩ መሆናቸውን የፌደራል ፖሊስ መረጃ ያመለክታል፡፡

 


በድርድር 15 ሺህ ዶላር ተከፍሏቸው ወ/ሮ ትዕግስት ከታገቱበት ሲና በረሃ ተለቀቁ!!

$
0
0

የሱዳን፣ የኤርትራና የግብጽ ዜግነት ባላቸው ራሻይዳዎች ታፍነው ወደ ሲና በረሃ የተወሰዱት ወ/ሮ ትዕግስት ገብሬ ካይሮ መግባታቸው ታወቀ። ወ/ሮ ትዕግስት ቅዳሜ ረፋዱ ላይ ካይሮ የገቡት አጋቾቹ እንዲሰጣቸው ከጠየቁት 25 ሺህ ዶላር በድርድር 15 ሺህ ዶላር ተከፍሏቸው ነው… ዜናውን በሰሙ ማግስት “የወ/ሮ ትግስት የርዳታ እጆች” በማለት ተሰባስበው የነፍስ አድን ዘመቻውን ከጀመሩት መካከል አንዷ የሆኑት ወ/ሮ ሰብለ ደምሴ በተለይ ለጎልጉል እንደተናገሩት ወ/ሮ ትዕግስት ከአሰቃቂው የሲና በረሃ ወጥተው ካይሮ የገቡት ከአራት ወራት በኋላ ነው። አጋቾቹ ወ/ሮ ትዕግስትን በ10 ሺህ ዶላር እንደገዙ በመግለጽ 25 ሺህ ብር ካልተከፈላቸው እንደማይለቁና የሰውነት ክፍላቸውን በመሸጥ ያወጡትን ወጪ እንደሚሸፍኑ ይደራደሩ እንደነበር የገለጹት ወ/ሮ ገነት “አስቀድመን 10 ሺህ ዶላር ከፈልን። ቀሪውን 5 ሺህ ዶላር ወ/ሮ ትዕግስት አገር ቤት ያሏቸው ከብቶች ተሽጠውና ከያለበት ተለቃቅሞ እንደሚከፈል በመግለጽ ተደራድረን ከተስማማን በኋላ ክፍያውን ፈጸምን” ብለዋል። ሱዳን ሸገራብ በሚባለው ሰፊ የስደተኞች ጣቢያ ከባለቤታቸውና ከሁለት ልጆቻቸው ጋር ይኖሩ የነበሩ ወ/ሮ ትዕግስት ገብሬ ጥር 22 ቀን 2005 ዓ ም ቤተ ክርስቲያን ለመሳለም በካምፕ ውስጥ ከሚገኘው ቤታቸው  በግምት ሰላሳ ሜትር ሳይርቁ ራሻይዳዎች አፍነዋቸው እንደወሰዷቸው ጎልጉል መዘገቡ ይታወሳል

ወ/ሮ ሰብለ ደምሴ፣ ወ/ሮ አዜብ ሮባና ወ/ሮ ኢየሩሳሌም ጸጋዬ ሰብዓዊነት ረፍት ነስቷቸው ባካሄዱት ዘመቻ ከተለያዩ ቤተክርስቲያናት፣ በጉዳዩ ሃዘን ከገባቸው ወገኖች፣ በተሰበሰበ ገንዘብ ወ/ሮ ትዕግስት ህይወታቸው ሳያልፍ ከዕገታው ነጻ መሆናቸው ልዩ ደስታ እንደፈጠረ ያስረዱት ወ/ሮ ሰብለ፣ “ነፍስ ለማዳን በተደረገው ጥሪ የተባበሩ ሚዲያዎች፣ ድርጅቶች፣ ግለሰቦችና ሁሉም ዓይነት የህብረተሰብ ክፍል በህብረታችን ስም ታላቅ ምስጋና እናቀርባለን። ወ/ሮ ትዕግስትና ባለቤታቸውን አግኝተናል። ሃዘናቸው በወገኖቻቸው ርዳታ ተለውጦ የደስታ እንባ አንብተዋል። እኛም ተደስተናል” የሚል መልዕክት አስተላልፈዋል።

“ግን” አሉ ወ/ሮ ሰብለ “ግን ብዙ ወገኖች በተመሳሳይ ችግር ላይ እንዳሉ ስናስብ አሁንም እረፍት የለንም። በምንኖርበት ሁሉ በተለያዩ መንገዶች ድርጊቱ የሚፈጸምበት ቦታ ላይ ያሉ ባለስልጣኖች እንዲህ ያለውን አስነዋሪና ሰብአዊነት የጎደለው ድርጊት እንዲያስቆሙ ትግላችንን መቀጠል አለብን” ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል። ወ/ሮ ትዕግስት አሁን ህክምና እየተደረገላቸው ስለሆኑ ሲያገግሙ ለሌሎች ትምህርት ይሆን ዘንድ፣ በቀጣይ በትብብር ድምጻችንን ለማሰማት የሚያተጋንን ቁምነገር እንዲካፍሉ እንደሚደረግ አስታውቀዋል።

ወ/ሮ ትዕግስት ከሲና በረሃ መልስ ያጋጠማቸውንና በትክክል የተመለከቱትን ለወገኖቻቸው እንደሚያካፍሉ የገለጹት ወ/ሮ ሰብለ ህብረታቸው ዝርዝር ጉዳይ የያዘ የምስጋና መልዕክት አዘጋጅቶ እንደሚያሰራጭ ገልጸዋል።

አፋኞቹ ራሻይዳዎች ናቸው። ራሻይዳ የቆዳቸው ቀለም ጠየም ያለ የሱዳን፣ የኤርትራና የግብጽ ዜግነት ያላቸው ሲሆኑ ቀደም ሲል ከሶስት እስከ አራት ሺህ ዶላር እየተቀበሉ በደላላ አማካይነት ስደተኞችን በሲና በረሃ ወደ ግብጽ ያሻግሩ ነበር። እስራኤል በሲና በረሃ ወደ ድንበሯን ዘልቀው የሚገቡበትን የስውር መንገድ ስትዘጋው ራሻይዳዎቹ የገቢ ምንጫቸው ተዘጋ። ገንዘብ የለመዱት ወንበዴዎች የንግዱን ስልት ቀየሩና ሰው ማፈን ጀመሩ። አፈናውንም ከሚያካሂዱባቸው መንገዶች ጥቂቶቹ ድንበር አቋርጠው የሚጓዙትን አድፍጠው በመያዝ፣ ስደተኞችን ከስደተኛ ካምፕ አፍኖ በመውሰድ፣ ከሌሎች አፋኞች ስደተኞችን በአነስተኛ ገንዘብ በመግዛት እንደሆነ በወቅቱ መዘገባችን ይታወሳል።

በደላሎች እስራኤል ለመግባት ጉዞ ከጀመሩት ወገኖች መካከል ስንቶቹ በሲና በረሃ ሟምተው እንደቀሩ መረጃ የለም። ከሱዳን ምድር ወጥተው ግብጽ በመሻገር ሲና በረሃ እንደ ከብት ተበልተው የሚጣሉት ወገኖች ስቃይ ለሰሚው ግራ ነው። ወገኖቻችን ላይ የሚደርሰው አሰቃቂ መከራ ከቀን ቀን እየተባባሰ ነው። አሰቃቂ ዜናዎች መስማት ለየእለቱ የሚያስፈልገን መሰረታዊ ጉዳይ እስኪመስል ተለመዷል። ይህ አሳሳቢ ጉዳይ “እስከመቼ በዚህ ይቀጥላል” የሚለው የሁሉም ወገን “ዳር ቋሚዎች” ጥያቄ ነው፡፡

የ12 እና የ 1 ዓመት ከስምንት ወር ልጅ ያላቸው ወ/ሮ ትዕግስት ታፍነው በነበረበት ወቅት ባለቤታቸውን በስልክ እንዲያነጋግሩ ይደረጋሉ። ባለቤታቸውም ይሰቃያሉ። እግራቸውና እግራቸው መካከል ብረት ተደርጎባቸዋል። ይደበደባሉ። ይህ ሁሉ የሚደረገው ባለቤታቸው የተጠየቁትን ገንዘብ ባስቸኳይ እንዲከፍሉላቸው ለማስጨነቅ ነው። ባለቤታቸው እንደተናገሩት “ምንም አማራጭ የለኝም። የተጠየቀውን ገንዘብ ማግኘት አልችልም። ልጆቼ ወደፊት ሲጠይቁኝ ለምኜ አቃተኝ ለማለት እየለመንኩ ነው። ባለቤቴ ግን ምንም ማድረግ እንደማልችል ታውቃለች፤ ባይሳካልኝና ነጻ ባላወጣት አትቀየመኝም… ” በማለት ለቪኦኤ መናገራቸው ይታወሳል።

የ12 ዓመቷ ልጃቸው ሱፊ “እኛንም እንዳይወስዱን ስለምንፈራ ከቤት አንወጣም” በማለት  ከቪኦኤ ለቀረበላት ጥያቄ ልብ የሚነካ shagrabመልስ ሰጥታ ነበር፡፡ “እናቴን አፈኗት” ያለችው ህጻን የበርካታዎችን ልብ እረፍት ነስታ ነበር። ወ/ሮ ሰብለ “እንደዚህ አይነት አሳዛኝ ሲቃ የተሞላበት ጉዳይ እየሰማን በውጪ ያለን ወገኖች እንዴት 30 ሺህ ዶላር (በወቅቱ የተጠየቀው) ማዋጣት አቃተን” ሲሉ በመገረም ጠይቀው ነበር። ወ/ሮ ትዕግስት ገብሬ ቢተርፉ ለሌሎች በማስተማር ተመሳሳይ ችግር በሌሎች ወገኖቻችን ላይ እንዳይደርስ የማድረግ ስራ ይሰራል የሚል እምነት እንዳላቸው ወ/ሮ ሰብለ መናገራቸው የሚታወስ ነው።

ወ/ሮ ትዕግስት ከካይሮ ወደ ነበሩበት ሰፊ የስደተኞች ካምፕ ሸገራብ ይመለሳሉ። መቼ እንደ ሆነ ባይገለጽም ከታፈኑበት ምድር፣ በስደት ከሚኖሩበት ሸገራብ ቤተሰቦቻቸውን ተቀላቅለው ኑሮን ይቀጥላሉ ወይስ … ? (Photo: BBC)


የሙስናው አስር ምስጢር! (ማረ በላዎቹ ርስ-በርስ ተበላሉ!)

$
0
0

ለብዙዎች “ሙስና” የሚለው ቃል በ1989 ዓ.ም ወዲህ የተፈጠረ ሃይለ-ቃል ይመስላቸዋል፡፡ ነገር ግን አይደለም፡፡ ቃሉ ግዕዝ ነው፡፡ ትርጉሙም፣“ጥፋት” ማለት ነው፡፡ በአማረኛም የኖረ ሕዝባዊ ግጥም/አባባል አለ፤ እንዲህ የሚል ነው… “የከንሯ ለዛ፣ የጉንጯ ሙስና፤

“ዐርብ ሮብ ያስክዳል፣ እንኳን ዐሙስንና፡፡” ይላል አዝማሪም፡፡

በሰሎሞን ተሰማ ጂ.

foto

በዚህ አገባብም መሠረት “ሙስና” የሚለው ቃል ትርጉም “ፈራሹ፣ ረጋፊው-መልኳ፣ ውበቷ እንዳጠፋ ገፋፋኝ” ለማለትና ለማሳበብ ነው የፈለገው (ደስታ ተክለ ወልድ፣ ዐዲስ ያማርኛ መዝገበ ቃላት፣ 1962 ዓ.ም፣ ገጽ-822)፡፡

በቅርቡ የገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን ሃላፊዎችን ሰብስበው በ2006 ዓ.ም የበጀት ዓመት፣ አንድ መቶ ሁለት ቢሊዮን ብር በላይ እንሰበስባለን” እያሉ ይዝቱ የነበሩት አቶ መላኩ ፈንታና አቶ ገብረ ዋህድ ወልደ ጊዮርጊስ፣ በዚህ የብር ጮማና የንዋይ ብርንዶ ውስጥ ተቀምጠው የተጣለባቸውን ኃላፊነትና ታማኝነት ቢዘነጉት ምን ያስደንቃል? ኧረ! ጨርሶ በኢትዮጵያ ብር አንገበያይም ብለው፣ በአሜሪካን ዶላርና በእንግሊዝ ፓውንድ ወይም በስዊዝ ፍራንክ ብቻ እንጠቀም ቢሉ ምን ያስገርማል? (ጥፋቱን ሙሉ ለሙሉ እነርሱ ላይ ማላከኩ ተገቢም፤ ትክክልም አይደለም፡፡ እና የማነው? በወቅቱ የእርምት ርምጃ ያልወሰደባቸው አካል ነዋ!፡፡)

በርእሴ ላይ ንዑስ-ርእስ አድርጌ የተጠቀምኩበት ሌላው ነጥብ “ማረ በላዎች” የሚለው ሃረግ ነው፡፡ ሆን ብዬ ነው፡፡ “ሙሰኞች” የሚለውን ቃል ለመጠቀምም ሆነ ለማለት ቀፈፌሽን ስለያዘኝ ነው፡፡ የዘመኑ አላዋቂ ባለስልጣኖችና የእነርሱን ቃል እንደገደል ማሚቶ የሚደግሙት ሎሌዎቻቸው እንደፈለጋቸው ይበሉት እንጂ፣ “ሙሰኞች” የሚል የግዕዝም ሆነ የዐማረኛ አገባብ የለም፡፡ “ሙሰኞች” ማለት ራሱ “ሙሰኝነት” ነው፡፡ ስለሆነም፣ በአማረኛዬ እንዳልሞስን በማሰብ “ማረ በላዎች” የሚለውን የራሴን ሃረግ መርጫለሁ፡፡ ቃሉ፣ የደስታ ተክለ ወልድ መዝገበ ቃላት (በገጽ-804 ላይ) እንደሚፈታው ከሆነ የሚከተለውን ትርጉም አለው፤ “ማረ በላ” ማለት ይላሉ፣ ጠጉራም፣ ጥፍራም፣ ነጭና ጥቁር፣ ዐጪር ቁመት ያለው አውሬ ነው፣ ማር የሚበላ አውሬ ማለት ነው ሲሉም ይገልፁታል፡፡ “ቀይ ማር የሚበላ የቆላ ጉንዳንም” ማለት ነው ሲሉ ይገልጹታል፡፡ “ጉንዳን”ም ተባለ “ዐጪር ቁመት ያለው አውሬ” ለምንነጋገርበት ረእሰ-ጉዳይ ገላጭና ተስማሚ ሆኖ አግኝቸዋለሁ፡፡ ስለሆነም፣ ተጠቅሜበታለሁ፡፡ ያልደከሙበትን የሚወስዱና የሚዘርፉ ሁሉ፣ “ገፊ-ማረ በላዎች” ናቸው፡፡

ሙስናና ማረ በላነት በኢትዮጵያ የኖረ ተግባር ነው፡፡ ስሙን እየቀያየረ “ሙስና” የሚለው የዐማረኛ ቃል ከመሆኑ በፊት የተለያየ ስያሜ ነበረው፡፡ በነገሥታቱ ዘመን “እጅ-መንሻ” ወይም “መተያያ” እየተባለ ይታወቅ ነበር፡፡ በዘመነ ደርግ ደግሞ “ብዝበዛና ምዝበራ” የሚል ትርጉም ተሰጥቶት ሲንከባለል ከቆየ በኋላ፣ በ1975 ዓ.ም ገደማ “ጉቦ” የሚል ታርጋ ተለጥፎበት በ1976 ዓ.ም “የሠርቶ አደሩ ቁጥጥር ኮሚቴ” የሚባል የአሁኑ “የሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን” የመንፈስ አባት በዐዋጅ ተቋቋመ፡፡ ወያኔ/ኢህአዲግ አዲስ አበባን እንደተቆጣጠረ ሰሞንም የዛሬው “ሙስና” ደርግ ያወጣለትን “ጉቦ” የሚል ስሙን እንደያዘ ነበር፡፡ በነሐሴ 2/1983 ዓ.ም አቶ አሰፋ ደስታ የተባሉት የከፍተኛ 13፣ ቀበሌ 10 “የሰላምና መረጋጋት ኮሚቴ ሊቀመንበር” አንዲት አደጋ ካደረሰች ተሸከርካሪ ሹፌር ላይ ሃምሳ (50.00) የኢትዮጵያ ብር “ጉቦ” የተቀበሉትን የቀበሌው ሰላምና መረጋጋት አባላት አሳፍሰው፣ አሳስረዋቸው እንደነበር አዲስ ዘመን ዘገባ ያወሳል (ገጽ-1)፡፡

የወያኔ/ኢህአዲግ ታጋዮችና ተጋዳላዮች በ1984 እና በ1985 ዓ.ም በየመንግሥት መሥሪያ ቤቱም እየሄዱ “የደርግ/ኢሠፓ አባላት” ናቸው ብለው የጠረጠሯቸውን ሰዎች ከሥራ ለማባረር ይጠቀሙበት የነበረው የስም ማጥፊያና ከሥራ ማስወገጃ አጀንዳቸው፣ “ያላግባብ የሕዝብ ሃብት የዘረፉ” የሚለው ነበር፡፡ (ያኔ፣ የሕዝብ ሀብት ዘረፉ ይባሉ የነበሩትና በወያኔ/ኢሕአዲግ አባላት ይባረሩ የነበሩት “ደርግ/ኢሠፓዎች ቢበዛ ሠላሳ ሺህ ብር ቪላ ቤት የሠሩ፣ ወይም ደግሞ ባለሦስት ክፍል ዛኒጋባ የቀለሱት “ሚስኪኖች” ነበሩ፡፡) ዛሬ ታሪኩ ተቀይሯል፡፡ ከባለአምስት ፎቅ ሕንፃ በታች ያለው ሹም ካለ “ፋራና ፈዛዛ” ብቻ ነው፡፡

በጥቅምት 14 ቀን 1989 ዓ.ም “አቶ ታምራት ላይኔ ከመከላከያ ሚኒስትርነቱና ከምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርነቱም ሲወገድ፣” የጠቅላይ ሚኒስትር መለሰ ዜናዊ ጽ/ቤት የሰጠው መግለጫ እንደሚለው ከሆነ፣ “አቶ ታምራት በምግባረ-ብልሹነት ተወወግዷል” ነው፡፡ “ጥይት ያላንበረከከውን ታጋይ፣ ስኳር አንበረከከውም!” ተብሎ ነበር (አዲስ ዘመን፣ ጥቅምት 15/1989 ዓ.ም፣ ገጽ-1)፡፡ ከወራት በኋላ፣ አቶ ታምራትና ወይዘሮ ሻዲያ ሀሰን ከነግብረ-አበሮቻቸው ተከሰው ፍርድ ቤት ሲቀርቡም፣ የተከሰሱበት ወንጀል “ያላግባብ ሃብት በማጋበስ” የሚል ነበር፡፡ በዚሁ ወንጀልም መሠረት፣ አቶ ታምራት ላይኔ በ14 ዓመት ጽኑ እስራት እንዲቀጣ የከፍተኛው ፍርድ ቤት ወሰነበት ተባለ፡፡ (“ተባለ” የምለው ሆን ብዬ ነው፡፡) አቶ ታምራት እስሩን ሳይጨርስ በ2000 ዓ.ም (በቅንጅት ታሳሪዎች ግርግርና በነፕሮፌሰር ኤፍሬም ይስሃቅ ተለማማጭነት ተፈታ፡፡ በቅርቡ ደግሞ ሪፖርተር ጋዜጣ እንደዘገበው ከሆነ፣ በስዊዝ ባንክ አስቀምጦት የነበረው ከ5 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገንዘብ ለኢትዮጵያ መንግሥት ተመልሷል፡፡

ከላይ እንደገለጽኩት፣ በታኅሣሥ ወር 1989 ዓ.ም ለመጀመሪያ ጊዜ አቶ መለሰ ዜናዊና የገመናኛ ብዙኃኖቻቸው “ሙስና” የሚለውን ቃል ለፖለቲካ ፍጆታ መጠቀም ጀመሩ፡፡ “ሙስና” እና “የፀረ-ሙስና ኮሚሽን” የሚባሉት ቃላት ሕግ ተረቆላቸው፣ ጽሕፈት ቤት ከፍተው፣ “ኮሚሽነርም” የሚባል ሹም ታውቆላቸው መቀፍደድና ማስቀፍደድ ተከተለ፡፡ “ሙስና ሰበብ በቁጥጥር ስር” መዋል የተጀመረው በግንቦት 16/1993 ዓ.ም ነው፡፡ ለማቋቋም የሚያስችለው ውይይት በግንቦት 10/1993 ዓ.ም በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተካሂዶ፣ ሳምንት ሳይሞላው በግንቦት 16/1993 ዓ.ም ሕግ ሆኖ ፀደቀ፡፡ ወቅቱ በጥድፊያ የተሞላና “የሕወሀት/ወያኔ ስንጠቃ በመቐሌና በሂልት አዲስ አበባ በይፋ የታወቀበት ጊዜ ነበር፡፡ ወያኔ ለሁለት መከፈሉም አርግጥ ነበር፡፡ ይሄንን ሕግ ከሚያረቁትም ሰዎች መካከል የዛሬው የገቢዎችና ጉምሩክ አቃቤ ሕግ አቶ እሸቱ ወልደ ሰንበት ነበረበት፡፡ መቀሌና ባህር ዳር ላይ ምቹ ሆቴሎችን ይዘው “የስነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና” ሕጉን ማርቀቅ ጀመሩ፡፡(አቶ እሸቱ በ1999 ዓ.ም እንደነገረኝ ከሆነ፣ ሕጉ ባስቸኳይ የተረቀቀው በአቶ ወረደወልድ ወልዴ ትዕዛዝ ሲሆን፣ በአቶ መለሰ ዜናዊ ቀጭን መመሪያም እንደተከወነ ነግሮኛል፡፡ በዚህም መሠረት፣ ሕጉ በጥቂት ሳምንታት ውስጥ ተረቀቀና ወዲያው ጸደቀ፡፡ በግንቦት 19/1993 ዓ.ም የፍትሕ ሚኒስትሩና የፀረ-ሙስና ኮሚሽነሯ ወይዘሮ እንወይ ገብረ መድህን፣ “ሕዝቡ የሙስና ወንጀልን ያለፍርሃት እንዲያጋልጥ” ጥሪ ካቀረቡ በኋላ፣ “የፀረ-ሙስና ሕጉ በቂ ጥበቃ” የሚያደርግለትም መሆኑን መግለጽ ጀመሩ፡፡ ከሁለት ቀናትም በኋላ የሙስናው ቲያትር (ገቢር አንድ) መጋረጃው ተገልጦ መታየት ጀመረ፡፡

በዕለተ ዐርብ ግንቦት 21/1993 ዓ.ም፣ የፀረ-ሙስና ኮሚሽን፣ “ከፍተኛ የሙስና ሴራ ውስጥ እንደሚገኙ በተጠረጠሩት ባለሥልጣነትና ነጋዴዎች ላይ ርምጃ ወሰድኩ” ሲል ለፈፈ፡፡ የፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ መምሪያም በበኩሉ፣ በሙስና ወንጀል ተጠርጣሪ የሆኑትን የመንግሥታዊ ተቋማት ኃላፊዎችና ነጋዴዎችን በቁጥጥር ሥር ማዋሉን ገለጸ፡፡ በዚህም መሠረት፣ አቶ ስየ አብርሃ (ባለስልጣን)፣ አቶ አሰፋ አብርሃ (ባለሥልጣን)፣ አቶ ምህረትአብ አብርሃ (ነጋዴ)፣ አቶ ፍስሃ አብርሃ-ነጋዴ(አራቱን ወንድማማቾች) እና አቶ ቢተው በለይን፣ አቶ ኃይሉ ለገሠን፣ አቶ ሙሉጌታ ገብረ መድህንን፣ አቶ በለጠ አለማየሁን፣ አቶ ብርሃነ ጂጆን፣ አቶ ሶፊያ ኢብራሂምን (እነዚህ ሁሉ በአንድ ወቅት ስንቱን የሚያንጰረጵሩ የወያኔ ሹማምንት ነበሩ) በቁጥጥር ሥር ዋሉ፡፡

ከነጋዴዎቹም መካከል አቶ ምንውዬለት አጥናፉና አቶ አበባው ደስታ (የስታር ቢዝነስ ግሩፕ ባለቤቶች)፣ አቶ ወርቁ መግራ፣ አቶ አበባው ገላዬ፣ አቶ አስናቀ ጀምበሬ፣ ወ/ሮ አጀብነሽ ሳምሶን፣ ወ/ሮ የሺሃረግ ዘውዴ፣ ሚ/ር ገራርድ ማይክል ሞላይን እና ሌሎችም ነበሩ፡፡ አርብ ማታ በዜና ማሰራጫዎች ተነግሮ፣ ቅዳሜና እሑድን ተራው ሕዝብ እንዲሰልቀው አደረጉት፡፡ ሰኞ፣ ግንቦት 24/1993 ዓ.ም ደግሞ ፍርድ ቤት ቀረቡ፡፡ ማክሰኞ ግንቦት 25/1993 ዓ.ም ደግሞ ኮሚሽነሯ ወ/ሮ እነወይ ገብረ መድህን የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ድረስ ሄደው “የፀረ-ሙስና ምንጠራው ተጠናክሮ እንደሚቀጥል” ተናገሩ (አዲስ ዘመን፣ ግንቦት 17፣ 18፣ 22፣ 25፣ አና 27 ቀን 1993 ዓ.ም፣ ገጽ-1 ላይ ማግኘት ይቻላል)፡፡ የአሁኑም ክስተት፣ ትዕይነተ-ቲያትር ወሙስና (ገቢር ሁለት) እንደማለት ይመስላል፡፡

በሰኔ 1/1993 ዓ.ም በፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት 1ኛ ወንጀል ችሎት ክስ የተመሰረተባቸው አቶ ስየ አብርሃ፣ በመሃል ዳኛዋ ወ/ት ብርቱካን ሚዴቅሳ ውሳኔ መሠረት በዋስ እንዲለቀቁ ተደረገ፡፡ በዚያው ዕለትም፣ የፌዴራል ፖሊስ የምርመራ ማስተባበሪያ ዋና ክፍል የፍርድ ቤቱን ትዕዛዝ ጥሶ ተከሳሹን አቶ ስየ አብርሃን በድጋሚ አሠራቸው (አዲስ ዘመን፣ ሰኔ 2/1993 ዓ.ም፣ ገጽ-1 እና 5)፡፡ ይህንኑ የአቶ ስየ አብርሃንና የፌዴራል ፖሊስን ግብግብ ተከትሎ በተፈጠረው ውዝግብ የተነሳ፣ በወቅቱ የፍትሕ ሚኒስትር የነበሩት አቶ ወረደወልድ ወልዴ ተከሰው በሁለት ዓመታት “የፈተና ጊዜ ገደብ” ፍርድ ተጣለባቸው፡፡ ጉዳዩ ከከፍተኛው ፍርድ ቤት አልፎም ወደ ጠቅላይ ፍርድ ቤት በይግባኝ ተወስዶ ነበር፡፡ ጠቅላይ ፍርድ ቤቱም ከፍተኛ ውዝግብ ውስጥ ከብቶ ነበር፡፡ በሰኔ 16/1993 ዓ.ም ኮሚሽነሯ ወ/ሮ እንይ በመገናኛ ብዙኃን ቀርበው (አይናቸውን በጨው አጥበው) እንዲህ አሉ፤ “መንግሥት ባለፉት ሰባት ዓመታት ውሰጥ ሙስናን መዋጋት ሁኔታዎችን ሲያመቻች መቆየቱን” ገልጸው ሲያበቁ፣ “በሙስና ወንጀል የተጠረጠረና የተያዘ ሰው፣ የዋስትና መብት የለውም፤” አሉ፡፡ “ምክንያቱም፣” አሉ ኮሚሽነሯ፣ “ምክንያቱም፣ ተጠርጣሪው የዋስትና መብቱ ከተከበረለት፣ ተጠርጣሪው ሊያመልጥ ስለሚችል ነው፤” ሲሉ አከሉበት፡፡

አስከትለውም፣ “በሙስና የተከሰሰ ሰው የዋስትና መብት እዳይኖረው የሚከለክል ሕግ መረቀቁንና በቅርብም ሥራ ላይ ይውላል፤” ሲሉ ነበር ያለባበሱት (አዲስ ዘመን፣ ሰኔ 17/1993 ዓ.ም፣ ገጽ-1)፡፡

የአሁኖቹም ተጠርጣሪዎችና የታሰሩበት ዕለት፣ የፍርድ ቤት አቀራረባቸው፣ እንዲሁም ተከሳሾቹ እያሰሙት ያለው አቤቱታ በ1993 ዓ.ም አቶ ስየ አብርሃና ባለቤታቸው እንዲሁም ሦስት ወንሞቻቸው ያሰሙት ከነበረው እምብዛም ልዩነት የለውም፡፡ (ቀንቀሎ ስልቻ፤ ስልቻም ቀንቀሎ ነው፡፡) ይሄንን አባባል ይበልጥ የሚያጠናክረው የናዝሬት ጉምሩክ ኃላፊ የተባሉት የአቶ ተመስጌን ጉልላትን “በጋንቤላ በኩል ወደ ደቡብ/ሱዳን ሊሸሹ ሲሉ ተያዙ!” የሚለውን ዜና በሐምሌ 12/1993 ዓ.ም ከወጣው የአቶ ሳሚ ዩሱፍ አኳኋን ጋር ካስተያዩት ነው፡፡ በወቅቱ አቶ ሳሚ በርካታ ብርና ዶላር ይዘው በሶማሊያ በኩል አድርገው ጂቡቲ ከገቡ በኋላ በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን ፖሊስ ገልጾ ነበር፡፡ የአቶ ሳሚ ዩሱፍ ወንጀል እጅግ አስደንጋጭ ነበር፡፡ (ልክ የሌ/ኮሎኔል ሃይማኖት 61 ሚሊዮን ብር ግምት ያለው ሰነድ ይዛ ልታሸሽ ስትል ያዝናት እንደሚለው ዜና፣ የአቶ ሳሚም ወንጀል ለሰሚውም የሚቀፍ ነበር፡፡) አቶ ሳሚ ቤሳ-ቢስቲን ሳይኖረው/ሳያሲዝ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 22 ሚሊዮን ብር በሕገወጥ መንገድ ከተበደረ በኋላ፣ (ያን ጊዜ፣ “የስኳር ድጋፍ ሰጪ” ከሚባለው ተቋም) “156,000 ኩንታል ስኳር ያለጨረታ ገዝቶ አየር-ባየር ከሸጠ በኋላ ዕዳውንም ሳይመልስ በሶማሊያ በኩል ሊኮበልል ሲል ተያዘ፤” የሚል ነበር (አዲስ ዘመን፣ ሐምሌ 12/1993 ዓ.ም፣ ገጽ-1)፡፡ ዛሬም፣ አቶ ተመስገን የሚኮበልሉበት አቅጣጫ ተቀየረ እንጂ ኩብለላን ነው የመረጡት፡፡ ከሕግ ፊት ሸሽተው እንዳልሆነ ይታወቅልኝ፡፡

እና፣ አቶ ሳሚ ዩሱፍም ሆኑ አቶ ተመስጌን ጉልላት ከምንድነው የሸሹት? የሚል ጥያቄ መነሳቱ አይቀርም፡፡ በቀጥታ ወደ መልሱ ከመግባቴ በፊት፣ በግንቦት 4/2005 የወጣው ሪፖርተር ጋዜጣን ሳነብ ያገኘሁትን መረጃ ላካፍላችሁ፡፡ እንዲህ ይላል፤ “እነዚህ ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ከመዋላቸው በፊት ላለፉት ሦስት ዓመታት ክትትልና ምርመራ ሲደረግባቸው እንደነበረ የታወቀ ሲሆን፣ ከመያዛቸውሁለትቀናትበፊትበመቀሌከተማከሙስናጋርበተያያዘጠንከርያለውይይትመደረጉን ለማወቅ ተችሏል፡፡ ከዚህ ስብሰባም በኋላ ጥንቃቄ በተሞላበት እንቅስቃሴ” ማረ በላዎቹን በቁጥጥር ሥር ማዋል ተችሏል” -ይላል (ገጽ-37)፡፡ ትልቁ ቁምነገር ያለው የተሰመረበት ንዑስ ዐረፍተ ነገር ላይ ነው፡፡ በፌዴራል መንግሥቱ ዋና ከተማ የሚደረጉ ስብሰባዎችም ሆኑ ውይይቶች “ፍሬ-ከርስኪ” እንደሆኑና የመቀሌቹ ስብሰባዎችና ውይይቶች ግን “መሬት ጠብ የማይሉ” እንደሆኑ ያሳብቃል፡፡ በርግጥም ይህ ለምን ተደረገ ብሎ መመርመር ያስፈልጋል፡፡

የመቀሌዎቹ፣ በ1993 ዓ.ም በእነአቶ ስየ አብርሃም ላይ የእስር ትዕዛዙን የወሰኑት ከዚያው ከመቀሌ ነበር፡፡ አዲስ አበባ በወቅቱ ምቹ አልነበረችም፡፡ ከሚያዝያ 3-7/1993 ዓ.ም ድረስ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች አመጽና፣ አመጹንም ተከትሎ የነበረው ዝርፊያና ግድያ፤ እንዲሁም የደሕንነትና ኢምግሬሽን ዋና ሥራ አስኪያጅ የነበሩት አቶ ክንፈ ገብረ መድኅን በግንቦት 4/1993 ዓ.ም በመኮንኖች ክበብ መገደል (ወዘተርፈ) አዲስ አበባን የማትታመን ሥፍራ አድርጓት ነበር፡፡ ምርጦቹ ሕወሀቶች መቀሌ ላይ ተሰብስበው፣ “የአቦይ አብረሃ ልጆችና ግብረ-አበሮቻቸው ይታሰሩ!” ቢሉ አያስደንቅም ነበር፡፡ ምክንያቱም፣ ከአዲስ አበባ ይልቅ “መቐለይ” ለሕወሀት ምቹ የቁጥጥር ዞን ስለሆነች ነው፡፡ አዲስ አበባ ላይ ስንቱ የእህት ድርጅት አባል ስለላና ብሰሳ እንደሚያደርግባቸው ስለሚያውቁም ነው መቐለይን የመረጡት (በተለይ ብአዴን)፡፡ ታዲያ “አሁን፣ በ2005 ዓ.ም ሚያዝያ ማለቂያና በግንቦት ልደታ ዋዜማስ መቀሌ ላይ ተሰብስቦ መወሰንን ምን ይሉታል?” የምትሉ እንደማትጠፉ እርግጠኛ ነኝ፡፡ አሁንም ቢሆን፣ አዲስ አበባ ውስጥ ሕዝቡ ባለፈው የቀበሌና የወረዳ/ክፍለ ከተማ ምርጫ እንደታየው ከሆነ ለወያኔ/ኢሕአዲግ ያለውን ስሜት በግልጽ አሳይቷል፡፡” ስለዚህም፣ ከፍተኛው ያገር ገዳይ መቐለይ ላይ ሸብ-ረብ ተደረገ፡፡

ሌላም ምክንያት አለው፡፡ የፌዴራል ዋና ኦዲተርን ሪፖርት ተከትሎ “ውስጣዊ ሴራዎች/Ineternal Conspirencies) መካሄደ ላይ ነበሩ፡፡ በ116 የፌደራል መንግሥቱ ተቋማት ውስጥ በተደረገው የኦዲት ምርመራ መሠረት፣ በ84 መ/ቤቶች ከ5.2 ሚሊዮን ብር በላይ ያልተወራረደ የጥሬ ገንዘብ ውዝፍ ተገኝቷል፡፡ ይህንን ገንዘብ ደግሞ በየመሥሪያ ቤቱ የአስተዳደርና ፋይናንስ ዋና መምሪያ ኃላፊዎች ሆነው እንዳሻቸው የሚያደርጉት የሕወሀት/ወያኔ አባላት ናቸው፡፡ ሰንደቅ ጋዜጣ በሚያዝያ 23/2005 ዓ.ም እንደዘገበው ከሆነ ደግሞ ችግሩ በይብጥ የሚጎላው በመከላከያ ሚኒስቴር ውስጥ ነው፡፡ 3.2 ቢሊዮን ብሩ ደብዛው የጠፋው በዚሁ ሚኒስቴር መሥሪያ ቤት ውስጥ ነው፡፡ ምናልባትም ደግሞ ከፍተኛዎቹን የጦር መኮንኖች የሚያነካካ ነው፡፡ ብዙዎቹ፣ በማረ በላነት ይታማሉ፡፡ በአንደ በጀት አመት ግን ይኼንን ያህል ገንዘብ ተመዝብሮ አያውቅም፡፡ ምናልባትም፣ አቶ መለሰ ዜናዊ ታመሙ (ሞቱ) የሚል የተምታታ ዘገባ በነበረበት የሰኔ/2004 ማለቂያ ላይ በስልጣናቸን አንቀጥልም በሚል ተስፋ-መቁረጥ ውስጥ የነበሩ አመራሮች ካቅማቸው በላይ አሽሽተዋል፡፡ ይሄንን ደግሞ የብአዴን መሪዎች በሚገባ አውቀውታል፡፡ ማወቃችንንም ያወቅነው በ11ኛው የኢሕአዲግ ጉባኤ ወቅት የአቶ በረከት ስምኦንንና የአቶ አዲሱ ለገሠን ቀና-ቀና ማለት አብጠርጥረን ስላየነው ነው፡፡

በዋናው ኦዲተር ሪፖርት አማካኝነት የብአዴን ሰዎች ራት ለመሆን የተዘጋጁት ሕወሀቶች ከጊ ጋር ሩጫ ጀመሩ፡፡ መቀሌ ላይ መሽገው ሁለት አባላቶቻቸውን “መናጆ” አድርገው በርካታ የብአዴን አባላትን ባላቸው የደሕንነትና የፀጥታ ዕዝ ሰንሰለት ተጠቅመው በቁጥጥር ሥር አዋሉት፡፡ እራት ሊያደርጋቸው ያሰበውን ብአዴንን፣ ሀሪፍ ምሳ አደረጉት፡፡ ብዘዎቹ የብዐዴን ሰዎች ሲታሰሩ “ችግር ይፈጥሩ ይሆናል የተባሉትም የፍትሕ ሚኒስትሩ አቶ ብርሀነ ኃይሉ፣ ሐሙስ ተወካዮች ምክር ቤቱ የሕግና ፍትሕ ቋሚ ኮሚቴ ሪፖርታቸውን ከቀረቡ በኋላ ከኃላፊነታቸው መታገዳቸውን አወቁት፡፡  ይህንንም ለማድረግ መቐለይ ላይ መሽጎ የነበረው “የትግራይ ሪፐብሊካን ፓርቲ” አመራር፣ የደሕነትና የፀጥታ ኃላፊዎችን ማዘዙ ብቻ በቂው እንደነበረ አልተጠራጠረም፡፡ በዕለተ አርብ፣ ግንቦት 2/2005 ዓ.ም መጋረጃው ተገልጦ “የሙስናው ወንጀልም ጉዳይ” ለሕዝቡ በሰበር-ዜናነት ተነገረው፡፡ (ሕዝቡ ግን የሚገርም ምላሽ ነበር የሰጠው፡፡ የፕሪሜር ሊጉና የሰውለሰው ድራማ ሲያልቅባቸው ጊዜ፣ “የሙስና ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ሥር ዋሉ” የሚል ድራማ ሊያሳዩን ይፈልጋሉን? ሲል ተዘባበተባቸው፡፡ (ጎበዝ፣ ቸር እንሰንብት!)


ከተበላሸ ወተት ጥሩ እርጎ አይገኝምና ተተኪዉን ትዉልድ ሀገር ወዳድ አድርገን እናሳድጋቸው!

$
0
0
በኢሳ አብድሰመድ/by Issa Abdusemed/
22ኛ ዓመቱን ሊደፍን የተቃረበው የወያኔ ስርዓት ከቅድመ ዓያቶቻችን  የተረከብናት ሃገር አሁንም በመልካም አስተዳደር እጦትና
ብልሹነት ተውጣ የፍትህ ስርዓቷ በተረጋጋና በተደላደለ መሠረት ላይ የሚያቆሙ ተቋማት አልተዘረጉላትም፡፡
በዚህም ሀሳብን በነጻ የመግለጽ የመጻፍና የመናገር እንዲሁም በህግ ፊት እኩል የመቆም መብቶች እየተዳፈኑ ይገኛሉ
በእርግጥ ያ ከ 21 ዓመት በፊት የነበረው ትውልድ  ከዚህ ውጭ አርአያ መሆን የሚችልባቸው  በርካታ ተሰጥኦዎች እንዳሉት መካድ አይቻልም። ለምሳሌ ላመነበት አላማ እፍኝ የማትሞላ ቆሎ ቆርጥሞ ጦር ሜዳ ለመዋል አንዳች አለማመንታቱን ከትውልዳችን ጋር ብናነፃፅረው የመለኮት እንጂ የሰው ጽናት ላይመስለን ይችላል። ይሄኔም ነው ያ ትውልድ እና ይሄ ትውልድ የመንፈስ ተወራራሽነት እንደሌላቸው በግልፅ የሚገባን፡፡ ለአገር ነፃነት መልካም ምግባር፣በጎነት፣ቆራጥና ደፋር ልብን ይፈልጋል። አገር ያለነፃነት አገር አይሆንም።
ነፃነት ሕያው የሕይውት ዋስትና መሰረትና አብይ ጉዳይ፣ የአገር ፍቅርና የክብር እሴት ሃብት ነው።ነፃነት ዋጋ አለው። ይህውም ውድ የሆነ የሕይወት መሰዋዕትነት ደም ነው።ኢትዮጵያ ለብዙ ሺህ ዘመናት በነፃነት ተጠብቃ የቆየችው የኛ ቀደምት ትውልድ በከፈሉት ቆራጥነት የደም ዋጋ ኃይል የአንድነት መሳሪያነትነው።  በዚህም የኢትዮጵያ ሕዝብ ቆራጥነትና ፅናት አገርን በነፃነት መጠበቅ በዓለም ፊት ትልቅ ምሳሌነትን
ያተረፈ፣ ዛሬ ለአለነውና ለመጭውም ትውልድ የሚኰራበት ሕያው የታሪክ አለኝታ መመኪና ክብር፣ የዘላለም አገር ወራሽነት ሃብታችን በመሆኑ ጠብቀንና አስከብረን ለተተኪው ትውልድ ለማስረከብ ኃላፊነቱ ከእጅግ ብርቱ ግደታ ጋር ነው።ለዚህም ነው “አገር አትሞትም ምንጊዜም ጠባቂ ትውልድ አላት” የሚባለው። ይህን አምኖና ተቀብሎ አገርን በነፃነት የማይጠብቅ፣ወራሽ ትውልድ በኢትዮጵያ ሊኖር ከቶ
አይችልም። ከዚህ ያነሰ መስዋዕትነት ሆነ ኢትዮጵያዊነት የጐደለው ትውልድ፣ ከንቱ ትውልድ፣አገር አልባነት፣ እፍረት፣ወራዳነት የቁም ሞት ነው። ሰው መሆን ይጠበቅብሃል። አገርህ በባንዳዎች ወያኔ/ኢህአድግ  ሸፍጥና ተንኰል ተተብትቦ ከደደቢት ጀምሮ እስከ አሁኑ ወቅት ድረስ
በአሀዳዊት እናት አገር ኢትዮጵያ ላይ የማጥፋት ዘመቻ እተካሄደና እየተፈጸመባት ትገኛለች።ሉዓላዊነቷ  ክህደት ተንቆና ተደፍሮ አገር ለሁለት ተከፍላ፣ የቀረው በጎጥ ወንጀል በቋንቋ ክፍፍል ተመድቦ፣ የአገር  ሕልውና የውሃ፣የአየር፣ የየብስ ዳር ድንበር ክልሏ ተደፍሮ፣ ተጥሶና ተዋርዳ አለች።በአምባገነንነት  በጠበንጃ ኃይል፣ በሕገ_ ወጥ ሕግ፣በሃሰት ሕገ_ መንግሥት፣በማጭበርበሪያ ዴሞክራሲ፣ በውሸት ሽፍጥና   ተንኰል ሕዝብ ሰብዓዊ መብቱን ተነጥቆ፣ዜግነቱን አጥቶ፣ ብሔራዊ ሃብትና ንብረቱን እየተዘረፈ፣ የአገሩ ለም መሬት እየተሸጠ፣እየተነጠቀና እየተባረረ፣ የሽብርተኛ ሕገ ወጥ ሕግ ወጥቶለት እየታሰረ፣እየተገረፈ ፣ቶርች እየተደረገ፣እየተገደለና እየሞተ፣ እየተፈናቀለና እየተሰደደ፣እንዲሁም እየተሸጠ የአረብ አገር ባሪያእየሆነ በግፍና በጭቆና ማነቆ ተጠፍሮ በጥፋት ላይ በመሆኑ አንተ የኢትዮጵያ ወጣት ይህን በጽኑ ኅሊና   ተገንዝበህ በአስቸኳይ ልታጠፋው  የሚገባህ የባንዳ ሥርዓትን ነው። ኢትዮጵያዊ ብሔራዊ ነፃነት ያነሰውና የጐደለው፣ዜግነትና አገራዊ ስሜትህን ተነፍገህ፣ በአደባባይ ተዋርደህና ዝቅ ተደርገህ፣ ስብዕናና መብት ተነፍጐህ፣ኅብረተሰባዊ አንድነትህ፣ክብርና ኩራትህ ተንቆ  አገሪቱ ሀብት እና ንብረት  ባለቤትነትህ ተነጥቆ፣ በባንዳ ወያኔ በአጉል ጠባብ ጎጠኛ አቀንቃኝነት በቋንቋ
ልዩነት ክፍፍል ኢትዮጵያዊ አንድነትህ ከታሪክ ምዕራፍ አውጥቶ ሲያስትህ በውሸት ፕሮፓጋንዳ  ሳታውቀው እየቆሰልክ እና እየደማህ፣  እየጠፋህና እየሞትህ እንደሆነ ልብ በል ። ዳሩግን ልብ  ከአጣህ ቆየህ ።አንተ ዛሬ ወጣት በትምህርት ገበታ ላይ ነገ ደግሞ በሥራ ለአገር እድገት የምትሰለፍ  መጭው ትውልድ መሰረት የሚጣልብህ ኃላፊነቱ እጅግ የላቀ ከፍተኛ የኅብረተሰብ ክፍል ነህ ብዬ  ገምታለሁ  ይህ ከዚህ በላይ የተዘረዘሩት ግፍና ጭቆና በአገርና ሕዝብ በአንተ በዛሬው አበባ በነገው ፍሬና ዘር ላይ የተተበተበና የታሰረ ማንነትን፣ጥቅምና ደህነትን፣ አለኝታን የነጠቀና ያሳጣ በባንዳ ወያኔና  ሆዳም አድርባይ ባንዳዎች የማያባራ ፀረ_ኢትዮጵያ፣ ኢትዮጵያዊነትና ሰንደቅ ዓላማችን ላይ ያነጻጸር  የጥፋት ሴራ አጀንዳ ነው።ይህን የጠላት አመጣጥና አረማመድ በዓይነ_ኅሊና ልታይና ልትገነዘብ በተገባህ ነበር።
ነገር ግን ዘንግተሃል እያንቀላፋህ ነው።“ባለቤቱን ካልናቁ አህያውን አይጭኑም፣ወይም አይመቱም” እንደተባለው  አነጋገር ቤተሰብህ እጅ
በመስጠቱ በአንተ በታዳጊው ላይ ብዙ ጥፋትና በደል እየተሰራብህ ነው። ያኔ የአንተን አእምሮ አደንዝዞና ሰልቦ፣በማደንቆር ማንነትህን አሳጥቶ ቅል እራስ ሆነህ ወያኔ/ኢህአድግ አጠመደልህ ወጥመድ ዓይንህን ጨፍነህ፣ ጆሮህን አደንቁረህ ሰተት ብለህ በመግባት እራስህን፣ አገርና  ብረተሰብን የምትጐዳና የምትገድል ተልካሻ ትውልድ ሆነሃል። ዚህም ክስተት ማንነትህን፣ የአገር ወገን የወደፊት ትውልድ ኃላፊነትና ግደታ ዘንግተህ ወያኔን አፍቃሪ፣ አክባሪ፣ እንድሁም ፈርተህና ተሸማቀህ አጐብድደህ ከመኖር በስተቀረ ወያኔ/ኢህአድግ ጠላትና አጥፊነቱ
ገዳይህም መሆኑን በፍጹም መረዳት አልቻልክም።ተደስትህ የምትመካና የምትኰራ ትውልድ ሆነህ ወያኔዎች ሲሞቱ ታለቅሳለህ ፣ መሬት ትወግራለህ።  ይህ እጅግ ወራዳነትና የሚያሳፍር፣ ተራና ዝቅ ያለ እራስን በራስ የማጥፋት ከንቱ የኅረብተሰብ ዝቃጭነት ነው። ይህ ሰው መሆንን ዘንግቶ የነገሩትን ብቻ የሚያስተጋባ ወይም የውሻ ጩህት ነው።ዚህ ኅሊና ቢስነት ማንነትን ያላገናዘበ፣ያልተረዳና ያላወቀ ተግባር ትውልድን ሁሉ ያሳፈረ፣ ታሪክን የዘነጋና ያራከሰ እጅግ የሚያሳፍርና የሚጐዳ  ቁስል ነው።
በአገርና ሕዝብ ላይ የወያኔ አረመኔዊ ጭካኔና ክህደት ፣ጥፋት፣ሽፍጥና ተንኰል የሚደርስውና እያደረሰ ያለው
ከጣሊያን ፍሽስት ወረራ ጊዜ እጅግ የከፋና የመረረ ነው። ያኔ ፀጉረ_ልውጥ አይምሰልህ እንጂ፤ድሮም በአገር ክህደት ባንዳዎች የነበሩ እነዚህ የባንዳ ልጆች ወያኔዎች  የአገር ጠላት አገር ተደፍሮና ተዋርዶ፣ታሪክ እየተበወዘ፣ አንድነት እየተናጋ፣ሕዝብ እየታመስ፣የአንተ ዜግነትና መብት
በሕገ ወጥ ሥርዓት ታፍኖና እየተረገጥህ፣ እየታሰርህ ማንነትህ እየጠፋና እየሞትክ ሲሆን፤ የአገርህ ለም መሬት
ደግሞ ከአንተ የአገሪቱ ተወላጅ፣ዜጋና ባለታሪክ ባለቤት፣አያት፣ ቅድመ አያትህ የሞቱላትን አጽመ_ርስት ሃብትን ተነፍገህና
እየተቀማህ ለውጭ አገሮች ለቻይና፣ ለህንድ፣ለአረብና ሌሎችም በርካሽና ለረዥም ጊዜ እየተሸጠ፣ እየተቸረቸረ ወያኔዎች
እየበለጸጉ፣ የአገርን ሃብት ወራሪ አንተን የማይመስሉ አጥፊዎች ናቸው። እያወጡና እያሸሹት አንተ እየተቸገርህና እየደኽየህ በረሃብ እየተሰቃየህና ከአገር እየተባረርክ እየተሰደድክህ ትገኛለህ። ይህ ሊያስቆጣህ፣ሊያናድድህና ጥርስ ሊያስነክስ በቻለ ነበር።
የወያኔ/ኢህአድግ እድሜ ለማሳጠር የተለመደው ሕዝባዊ ድጋፍ ተጠናክሮ እንዲቀጥል መላው ነፃነት ናፋቂና ሀገር
ወዳድ ኢትዮጵያዊያን ሀገራዊ መልዕክቴን አስተላልፏለዉ።

ኢትዮዽያ ለዘላለም ትኑር


“ከሌባ ስብስብ መሃል ጎበዝ ሌባ ይወጣል እንጂ አዲስ ነገር አይኖርም”

$
0
0

ፍኖተ ነፃነት፡- ለፍኖተ ነጻነት ጋዜጣ ማተሚያ ማሽን ለመግዛት የሚደረገውን እንቅስቃሴ ከሚደግፉ ኢትዮጵያዊያን ጋር ለመገናኘት ወደ አሜሪካ አቅንተው ነበር፡፡ በአሜሪካ ቆይታዎ ከአንድነት ደጋፊዎች ጋር ያደረጉትን ቆይታ እንዴት ይመዝኑታል?…

የተከበሩ አቶ ግርማ፡- ዋሽንግተንና ሜሪላንድ የመሳሰሉን ሳይጨምር አንድ አስር ቦታዎች ከደጋፊዎች ጋር ተገናኝቻለሁ፡፡ የሄድኩበት አላማ ሁለት ነው፣የአሜሪካ መንግስት እንዴት እንደሚሰራ ለማየት እንድንችል ለተወሰኑ የአፍሪካ ሰዎች እድል በመስጠቱና እግረ መንገድም የፍኖተ ነጻነትን ማሽን የመግዛት አላማ ከሚደግፉ ኢትዮጵያዊያን ጋር ለመገናኘት ነበር፡፡ ለእኔ ያደረግኳቸው ውይይቶች በጣም ጠቃሚ ነበሩ፡፡ ከአገሩ ውጪ የሚገኙ የአገራችን ልጆች በምን ሁኔታ ላይ እንደሚገኙ ለመረዳት የሚያስችል ነው፡፡ እንደ ፖለቲካ ድርጅትም ሰዎቹ በምን ሁኔታ እንደሚገኙ ማወቅና እንዴት ሊደግፉን እንደሚችሉ መረዳት ወሳኝ በመሆኑ ውይይቱ በጣም አስፈላጊ ነበር፡ ፡ አንዳንድ ሰዎች የተገኘሁባቸውን መድረኮች ስኬታማነት በተሰበሰበው ገንዘብ ሊለኩት ይፈልጋሉ፣ ነገር ግን እኔ እንደዚያ መመልከት አልፈልግም፡፡

 

 

ፍኖተ ነፃነት፡- በየመድረኮቹ ይቀርቡልህ የነበሩ ጥያቄዎች በዋናነት በምን ላይ የሚያተኩሩ ነበሩ፣የተደረገልዎት አቀባበልስ?

የተከበሩ አቶ ግርማ፡- የተደረገልኝ አቀባበል በእውነቱ የጠበቅኩት አይነት አልነበረም፡፡ ብዙዎቹ ቦታዎች ላይ የተደረገልኝ አቀባበል ደማቅ ነበር፡፡ በአብዛኛው ይቀርብልኝ የነበረው ጥያቄ ሰላማዊ ትግልን የሚመለከት ነበር፡፡ አሁን ባለው ተጨባጭ ሁኔታ ሰላማዊ ትግል አዋጪ አይደለም የሚሉ ሰዎች አጋጥመውኛል፡ ፡ የሰላማዊ ትግልን ሙጥኝ ማለታችንን ከፍርሃት የሚያገናኙ ሰዎችም ነበሩ፡፡ ሰላማዊ ትግል ለኢትዮጵያ ከመቼውም ግዜ በላይ አስፈላጊ እንደሆነ እናምናለን፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ የሚመጡ ሽግግሮች በህግ ስርዓት እንዲሆኑ አርአያ መሆን ይገባናል በማለት እናምናለን፡፡ ጥያቄዎቹን የሚያነሱት ሰዎች ይህ መንግስት በሰላማዊ ትግል ይወድቃል የሚል እምነት የላቸውም ታዲያ በምንድን ነው የሚወድቀው በማለት ስንጠይቃቸው ግን ምላሽ የላቸውም፡፡ብዙዎቻችን ግን ህዝቡን እያሳሳትነው ነው ነጻ እናወጣሃለን እንለዋለን፡፡ ትልቁ ነገር ግን ህዝቡ መብቱን እንዳያስነካ ማነሳሳት ነው፡፡ መብቱን ሌሎች ሳይሆኑ ራሱ ማስከበር ይኖርበታል፡፡ ነጻ ማውጣት የፖለቲካ ፓርቲዎች ስራ አለመሆኑ መታወቅ ይኖርበታል ከዚህ አንጻር ትልቅ ክፍተት እንዳለ ተረድቻለሁ፡፡ ፓርቲዎች ዋና ስራቸው አገርን የሚመሩ ሰዎችን ማፍራት መሆኑ ቀርቶ አመጽ ቀስቃሾችና አነሳሾች አድርጎ መውሰድ እየተለመደ መጥቷል፡፡ይህ የግንዛቤ ችግር ነው ብዬ እወስደዋለሁ፡፡ፓርቲዎች የጋዜጠኝነት ወይም የሲቪክ ማህበራት ስራን እንዲሰሩ መጠበቅ የለባቸውም፡፡አንዳንድ ጊዜ ድንበሮችን እያለፍን የምንሰራቸው ስራዎች አሉ፡፡ለምሳሌ ፍኖተ ነጻነት ጋዜጣን መውሰድ ይቻላል፡፡ጋዜጣውን ማሳተም የጀመርነው ሚዲያው በመታፈኑ እንጂ ጋዜጣውን ማዘጋጀት የእኛ ሃላፊነት ሆኖ አይደለም፡፡በየሳምንቱ የምናደርገው ውይይትም የእኛ ጉዳይ ሳይሆን በዋናነት ሲቪክ ማህበራት ሊሰሩት የሚገባ ነበር ነገር ግን ይህንን የሚሰሩ ሲቪክ ማህበራት ባለመኖራቸው ክፍተቱን ለመሙላት እየሰራን እንገኛለን፡፡

ፍኖተ ነፃነት፡- እንደሚያውቁት ከ1997 በፊት በተለይ በውጪ አገራት የሚኖረው ኢትዮጵያዊ ሰላማዊ ትግሉን በመደገፍ ረገድ ቀጥተኛ ተሳትፎ ያደርግ ነበር፡፡የምርጫው ውጤት መገለጹን ተከትሎ በተፈጠሩ ነገሮች የተነሳ የሰላማዊ ትግል አዋጭ አይደለም የሚሉ ቡድኖች እንዲፈጠሩ ምክንያት ሆኗል፡፡ ዜጎች እንዲህ አይነት ድምዳሜ ላይ እንዲደርሱ መንግስት አስተዋእጾ አላደረገም?

የተከበሩ አቶ ግርማ፡- ትግሉ ፍሬ እንዲያፈራ እኮ ከመነሻው መንግስት አይፈልግም፡፡ገዢው ፓርቲ ለአርባና ሰላሳ አመታት መግዛት እንደሚፈልግ ነግሮናል፡፡እኛ ከእነርሱ እንዲህ አይነት ነገር ይመጣል ብለን አንጠብቅም፡፡ከዚህ ይልቅ እኔ የማይመቸኝ በየጊዜው ቅንጅት እያልን የምንዘፍናት ዘፈን ናት፡፡በ97 የተፈጠረው ነገር መንግስት አሸንፋለሁ በሚል ትእቢት ተሞልቶ ለተቃዋሚዎች የተሻለ ሁኔታን ፈጠረ ህዝቡም እንዲህ አይነት ነገር ሲፈጠርለት በትክክል ምን እንደሚፈልግ አሳየ፡፡ነገር ግን የነበረው ነገር ሁሉ የተደራጀ አልነበረም መንገስት የተቃዋሚ አመራሮችን ጠራርጎ እስር ቤት ሲያወርድ ህዝቡ ተመልሶ ወደ ነበረበት ገባ ፡፡ይህ የሚያሳየን የተቀናጀ ነገር አለመኖሩን ነው፡፡ትግሉ የሚቆም ሳይሆን ቀጣይነት የሚኖረው መሆን አለበት፡፡ አንድ ሚልዮን ሰው የሚሳተፍበትን የሰላማዊ ትግል እንቅስቃሴ ሀምሳ ሰው በማሰር አይኮላሽም፡፡ለምሳሌ የሙስሊሞቹን አይነት እንቅስቃሴ ተቃዋሚዎች ለምን መፍጠር አልቻሉም ይባላል፡፡ሙስሊሞቹ በየሳምንቱ አርብ የሚገናኙባቸው መስጊዶች አሏቸው እኛ ይህንን ለማድረግ መገናኛ ቦታዎችን መፍጠር አለብን እንደምታውቁት አንድነት አምስት መቶ ሃምሳ የምርጫ ወረዳዎችን በመለየት በአሁኑ ሰዓት ህዝቡን የማገኝበት መድረክ ይሆነኛል በማለት እየሰራ ይገኛል፡፡ የእኛ መስጊዶች የሚሆኑት እነዚህ ናቸው ማለት ነው፡፡ እንደዚህ አይነት ቦታዎችን መፍጠር ካልቻለን አገር አቀፍ እንቅስቃሴ መፍጠር አንችልም፡ ፡ መንግስት ከ97 ምርጫ በኋላ ባወጣቸው ህጎች አማካኝነት ትልቅ ሚና የነበራቸውን ሲቪክ ማህበራትና ሚዲያዎች ከጨዋታ ውጪ እንዲሆኑ አድርጓቸዋል፡፡

ፍኖተ ነፃነት፡- በአንድ የውይይት መድረክ ማኪያቶ ወይም ቢራ እየጠጣን መታገል እንፈልጋለን በማለት መናገርዎ ጉርምርምታ ስለመፍጠሩ ተወርቷል፡፡ምን ማለትዎ ይሆን?

የተከበሩ አቶ ግርማ፡- ብዬ አላውቅም ግን ቢራና ማኪያቶ የሚከለክለኝ ነገር ግን የለም፡፡ቢራና  ማኪያቶ እንደማልለምን ካረጋገጥኩ በኋላ ነው ፖለቲካ ውስጥ ገብቼ መጫወት የጀመርኩት፡፡ ደግሞም እኮ ሱባኤ አይደለም የምገባው ነገር ግን እንዲህ አይነት ነገር ተናግሬ አላውቅም ሌሎችም እንዲህ አሉ በመባሉ ይደብረኛል

ፍኖተ ነፃነት፡- የፍኖተ ነጻነት ጋዜጣን ማተሚያ ማሽን ተሳክቶላችሁ ብትገዙ መንግስት ምን ሊያደርግ ይችላል የሚል ጥያቄ እንደቀረበልዎም ሰምተናል ምላሽዎ ምን ነበር?

የተከበሩ አቶ ግርማ፡- ይህንን እኮ መመለስ ያለባችሁ እናንተ ናችሁ እኔ እሰጥ የነበረው ምላሽ ግን እሞታለሁ ከሚል ስጋት የተነሳ ሰው ሳይተኛ እንደማይቀር ነበር፡፡ሊወርሱት ይችላሉ ወይም ያዘርፉታል የሚል ስጋት ያላቸው ሰዎች አሉ ነገር ግን ይህንን በመፍራት ማድረግ ያለብንን ነገር ከማድረግ ወደ ኋላ አንልም፡፡ ጋዜጣችንን ያትሙ የነበሩ ማተሚያ ቤቶችን በስልክ እየደወሉ አስፈራሯቸው እንጂ ማተሚያ ማሽኑን አልወሰዱባቸውም፡፡ ስለዚህ ለእኛ ደውለው ከአሁን በኋላ አንዳታትሙ ቢሉን ፈርተን አንቀመጥላቸውም፡፡ሊወርሱት ወይም ሊሰርቁን ይችላሉ እናም ይህው ሌባ መንግስት ነው ብለን አናሳያቸዋለን፡፡

ፍኖተ ነፃነት፡- በስራ አጋጣሚም ይሁን ለፖለቲካ ስራ ወደ ተለያዮ አገራት ሲያመሩ ከየአገራቱ የፓርላማ አባለት ጋር ተገናኝተው ሲወያዮ ብቸኛው የተቃዋሚ ፓርቲ ተወካይ መሆንዎን ሲሰሙ ምን ይላሉ?

የተከበሩ አቶ ግርማ ፡- ይህንን ብንተወው ነው የሚሻለው፡፡የሚመለከቱኝ እንደብርቅዬ ነገር ነው ፡፡ስለ እኔ ብቸኛ የተቃዋሚ ተወካይ በፓርላማ መሆኔን ሲሰሙ የምናወራበት ነገር ሳይቀር እየተለወጠ ብቸኛው መወያያ የምሆነው እኔ ነኝ፡፡ እየመጡ እየነካኩኝ ምናምን ነው የሚያወሩኝ እንደ ልዮ ነገር ነው የሚመለከቱኝ፡፡ እንዲህ በመሆኑ የምደሰት የሚመስላቸው ሰዎች ካሉ ተሳስተዋል ይህ አያስደስትም ፡፡ ምናልባት የገዢው ፓርቲ ማንነት በዚሀ ተጋልጦ ይሆናል ነገር ግን የሚጋለጠው እርሱ ብቻ አይደለም አገርም ትገመታለች፡፡ እኔ አንድ የፓርቲ ተወካይ ብቻ በመሆን ፓርላማ ከምገባ ለመንግስት የሚሻለው የአንድ ፓርቲ አመራር ሆኜ እዛ ብገባ ነበር፡፡እንዳለመታደል ሆኖ ግን እነርሱ በዚህ ሊማሩ አልፈቀዱም አሁን የተደረገውን ምርጫ በአጠቃላይ ስለ ማሸነፋቸው እየተናገሩ ነው፡፡

ፍኖተ ነፃነት፡- እርስዎ ወደ ውጪ ባመሩበት ወቅት ጠቅላይ ሚኒስትሩ የስድስት ወራት ሪፖርታቸውን አቅርበዋል፡፡ ብዙዎች እርስዎ በፓርላማው የሚያቀርቡትን አስተያየት ለመስማት ፈልገው ነበር፡፡እንዴት ነው ሪፖርቱ የሚቀርብበትን ወቅት ባለማወቅዎ ነው ወይስ ሪፖርቱ ያለ ጊዜው እንዲቀርብ በመደረጉ ነው?

የተከበሩ አቶ ግርማ ፡- ሪፖርቱ የቀረበው የጊዜ ሰሌዳውን ጠብቆ አይደለም፡፡አንድ የሚያሳምን ምክንያት ሊሆን የሚችለው ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከሁለት ወር በፊት መጥተው የነበረ መሆኑ ነው፡ ፡እኔ በግሌ እንዲያመልጠኝ ከማልፈልጋቸው የፓርላማ ስብሰባዎች አንዱ ነበር ነገር ግን መሄድ ስለነበረብኝ በወቅቱ በፓርላማው መገኘት አልቻልኩም፡፡ተመልሼ ከመጣሁ በኋላ ከገረሙኝ ነገሮች አንዱ ሪፖርቱን በማግኘት ለማንበብ ሞከርኩ ሌላ ጊዜ በጠቅላይ ሚኒስትሩ የሚቀርቡ ሪፖርቶች ከመቅረባቸው ቀደም ብሎ የፓርላማ አባላቱ አንብበው ጥያቄዎችን እንዲያነሱ እንዲደርሳቸው ይደረጋል፡፡እናም ሪፖርቱ እንደተቀመጠልኝ በማሰብ ሳጥኔን ከፈትኩ ሳጥኔ ውስጥ አልገባም፣ምናልባት አለመኖሬን ሲያውቁ ቢሮ ልከውልኝ ይሆናል ብዬ ቢሮ ሄጄ ፈለግኩ እዚያም አልመጣልኝም፤ ከዚያም ማባዣ ክፍል ሄጄ ለምን ሪፖርቱን አልላካችሁልኝም ስላቸው ሪፖርቱ እንዳልተበተነ ነገሩኝ፡፡

ፍኖተ ነፃነት፡- የፓርላማ አባላቱ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ሪፖርቱ ሳይደርሳቸው ሪፖርቱ ቀረበ እያሉን ነው?

የተከበሩ አቶ ግርማ ፡- እኔ ብኖር ኖሮ እንዲህ አይደረግም ወይም ለኢትዮጵያ ህዝብ ሪፖርቱ ሳይቀርብልኝና ሳልዘጋጅ እንድጠይቅ መደረጌን እናገር ነበር ፡፡አንድ መሆኔን ብቻ ሳይሆን መመልከት ያለብን አንድ ሆኜም የምሰራውን ነገር ነው፡፡በፓርላማ ጠቅላይ ሚኒስትሩን ይጠይቁ የነበሩ የፓርላማ አባላት ጥያቄዎቹን ለዚያውም የተጻፈ እያነበቡ መጠየቃቸው እንድገረም አድርጎኛል፡፡እነዚህ ሰዎች ጥያቄውን የጠየቁት እዚያው ነው እንዳይባል ከመጀመሪያው ስማቸው እየተጠራ ነው እንዲጠይቁት የሚደረጉት፣ሪፖርቱ ደርሷቸዋል ከተባለም እንዳልተበተነ ማባዣ ክፍሉ ተናግሯል፡፡በአጭሩ ለፓርላማ አባላቱ ጥያቄ እያዘጋጀ የሚበትን አካል አለ ማለት ነው፡፡

ፍኖተ ነፃነት፡- የአሜሪካ መንግስት እነ አንዷለም አራጌና እስክንደር ነጋ ለፈርድ ቤት ያቀረቡት ይግባኝ ውድቅ ተደርጎ እስሩ እንዲፈጸምባቸው መደረጉን በመቃወም ጠንከር ያለ መግለጫ አውጥቷል መግለጫው በቀጣይ በአሜሪካና በገዢው ፓርቲ መካከል በሚኖረው ግኑኝነት ላይ ተጽእኖ ያሳርፍ ይሆን?

የተከበሩ አቶ ግርማ ፡- በእርግጥ የአሁኑ ጉዞዬ አላማ የአሜሪካ መንግስት እንዴት እንደሚሰራ ማየትን የሚጨምር ነበር፡፡ ከዲፕሎማቶች ጋር በተገናኘሁበት ወቅትም ያወራነው ስለዚህ ጉዳይ ነው፡፡በተረፈ እንዲህ አይነት ነገሮች በመደበኛነት ባይሆንም መነሳታቸው አይቀርም፡ ፡በግል ባነሳናቸው ውይይቶች የኢትዮጵያ መንገስት ፖለቲከኞችና ጋዜጠኞች ላይ እየወሰደ የሚገኘው ነገር እያሳሰባቸው እንደመጣ ይነግሩኛል፡፡መሰመር ያለበት ጉዳይ ግን አሜሪካኖች ተጫኑም አልተጫኑም ትልቁ ትግል መደረግ የሚኖርበት በእኛው ነው፡፡ መንግሰትን ሌሎች እንዲያንበረክኩት መጠበቅ የለብንም፡፡ መጫን ያለብን እኛው መሆን አለብን፡፡ በደርግ ዘመን አባቴ ‹‹አንድ ልጅ ከዚህ ቤት በወታደሮች በሃይል አይወሰድም ልጆቼን የሚወስዱት እኔን ገድለው ነው››ይል ነበር፡፡በዚያ ወቅት እኮ ቤተሶዎች ልጆቻቸውን በብሄራዊ ውትድርና ሰበብ ይነጠቁ ነበር፡፡ እንዲህ አይነት እምቢ የሚል ሰላማዊ ታጋይ ማፍራት ይኖርብናል፡፡ ፊሪዎች ከሆንን አንድ ነገር ማድረግ አንችልም፡ ፡እናንተ ፈሪዎች ስለ መሆናችሁ አላውቅም ብትሆኑ ኖሮ እዚያ ግቤ አትገቡም በእንዲህ አይነት እሳትም አትጫወቱም፡፡

ፍኖተ ነፃነት፡- በቅርቡ እንግዲህ መንግስት ከፍተኛ ሃላፊዎቹ ላይ ከስራ የማንሳትና የእሰር እርምጃ ወስዷል፡፡ ጸረ ሙስናም በፓርላማ በኮሚሽነሩ አማካኝነት ባቀረበው ሪፖርት ከፍተኛ ምዝበራ ስለ መፈጸሙ ተናግሯል፡፡ ሰሞነኛው እርምጃ መንግስት በሙስና ላይ ቆርጦ ስለመነሳቱ የሚያሳይ ነው ወይስ የተለመደው የፖለቲካ ጨዋታ ነው?

የተከበሩ አቶ ግርማ ፡- እኔ በአዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር ተስፋ ከሚያደርጉ ሰዎች አንዱ መሆኔን ከዚህ ቀደም ተናግሬያለሁ፡፡ የፖሊሲ ለውጥ እንኳን ባይኖር የሹፌር ለውጥ የተወሰነ ለውጥ እንደሚፈጥር ተስፋ አደርጋለሁ፡፡ ከዚህ በተቃራኒው የሚያስቡ ደግሞ አሉ፡፡ ሹፌሩ ለውጥ ያመጣባቸዋል ብዬ ከማምንባቸው ነገሮች አንዱ ተቋማትን በህግ በተሰጣቸው መብት መሰረት እንዲሰሩ ያደርጋሉ በማለት ነው፡፡ ፍርድ ቤቶች፣እንባ ጠባቂ፣ጸረ ሙስና፣የፌደራል ኦዲተርና ሌሎችም በነጻነት መስራት ከቻሉ በትክክል የጠቅላይ ሚኒስትሩን ስልጣን ማየት እንችላለን፡፡ የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር እነዚህ ነገሮች አያስፈልጓቸውም የሚፈልጉትን ነገር በስልክ መጨረስ ይችሉ ነበር፡፡ የአሁኑ ጠቅላይ ሚኒስትር ከዚህ መቆጠብ አለባቸው፡፡ ጸረ ሙስና ያደረገውን ነገር ማበረታታት አለብን ይህንን የምናደርገው ሰዎቹን ስለምንጠላቸው አይደለም፡፡ የግድ መደረግ ስላለበት ነው፡፡ የፖለቲካ ጉዳይ መሆኑም መዘንጋት የለበትም ፡፡ በሚኒስትር ደረጃ የሚገኝ ሰው በሙስና ተዘፍቆ መገኘቱ ለምንግሰት ጥሩ ነገር አይደለም፡፡ በዚህ ኢህአዴግ መጠየቅ አለበት፡፡ ሌባ የሾመው እኮ እርሱ ነው፡፡

ፍኖተ ነፃነት ፡- እነ መላኩ ፈንታ ከመታሰራቸው ቀደም ብሎ መቀሌ ላይ ህወሃት ስብሰባ ማድረጉንና እንዲታሰሩ ስለ መወሰኑ ተነግሯል ከዚህ በመነሳትም የባለስልጣናቱ መታሰር ከሙስና ባሻገር ሌላ መልእክት እንዳለው ብዙዎች ሲናገሩ ይደመጣሉ፣በዚህ ላይ የወሳኝነቱን ሚና ከሀይለማርያም ይልቅ ለህወሃት የሚሰጡ ቀላል ቁጥር የላቸውም በዚህ ይስማማሉ?

የተከበሩ አቶ ግርማ ፡- ባህርዳር ላይ ስብሰባ እንደሚደረገው መቀሌ ላይ ሊደረግ ይችላል፡፡ ሌላው እኔ ህወሃቶች ሌሎችን ማሽከርከር የሚችሉበት ቁመና ላይ ናቸው ብዬ ለማመን እቸገራለሁ፡፡ እንደውም እነርሱ ራሳቸውን ከሌሉቹ እኩል ለማድረግ እየሰሩ የሚገኙ ይመስለኛል፡፡

ፍኖተ ነፃነት፡- ራሳቸውን እኩል ለማድረግ ሲሉ በተለይ የብአዴኖችን እየጎሉ መምጣት ለመምታት እንዲህ አይነት እርምጃ እንዲወሰድ ያደርጋሉ የሚባለው?

የተከበሩ አቶ ግርማ ፡- ብአዴን ከጎላ እኮ ከእርሱ እኩል ያልሆነው ጫና ሊፈጥርበት አይችልም፡ ፡ሙስና የሚባለውን ነገር ኢህአዴግ ለመታገል ከተነሳ ተቃዋሚዎች ብንሆን እንኳን መደገፍ ይኖርብናል፡፡ ሚዲያዎችም ትልቅ ሃላፊነት አለባቸው፡፡ በሙስና የታሰሩትን ሰዎች ሳይ ወደ አእምሮዬ የሚመጣው የመጣው የመጀመሪያ ነገር ሌሉችን በተለይም ነጋዴዎችን ሌቦችና ሙሰኞች እያሉ ሲዘልፉ መቆየታቸው ነው፡፡

ፍኖተ ነፃነት፡- በእስሩ ላይ ጥርጣሬ ያላቸው ሰዎች ሌላ የሚያነሱት መከራከሪያ ጸረ ሙስና ትልልቆቹን አሳዎች ሳያጠምድ ትንንሾቹ ላይ ሲያተኩር መቆየቱንና ከዚህ ቀደምም በእነ ስዬ ላይ የተወሰደው እርምጃ የበቀል አይነት መሆኑን ነው፡፡

የተከበሩ አቶ ግርማ ፡- ጸረ ሙስና እስከ ዛሬ በነበረው ስራው ከፓርቲ መገልገያነት ነጻ ነው ብዬ አላምንም፡፡ ነገር ግን የአሁኑን ጉዳይ ከእነ ስዬ ጋር ማገናኘት አይገባንም፡፡ እነዚህ ሰዎች በአብዩታዊ ዴሞክራሲ ፍቅር ወድቀው ሌሎችን ሲያስጨንቁ የነበሩ ናቸው፡፡የፖለቲካ ልዩነት እንዳላቸው እኛ እስካሁን ድረስ ምንም አልሰማንም፡፡ጥፋት አጥፍተው አይ እንዲህ ስላልን ነው ማለት ተቀባይነት ሊኖረው አይገባም፡፡መውጣት የነበረባቸው መጀመሪያ ነው፡፡

ፍኖተ ነፃነት፡- ገዢው ፓርቲ ኢህአዴግ ባህር ዳር ላይ አድርጎት በነበረው ዘጠነኛ ጉባኤ ሙስናን እንደሚዋጋ መናገሩ አይዘነጋም ነገር ግን ተቺዎች ኢህአዴግ ሙስናን የሚዋጋ ከሆነ ራሱን ያጠፋል ይላሉ፣ለዚህ የሚያነሱት ነጥብ ድርጅቱ አባላቱን የሚሰበስብበት መንገድ ከጥቅም ጋር የተቆራኘ መሆኑን ነው፡፡ ከዚህ በመነሳት ጸረ ሙስና ኢህዴግንም መመልከት አይገባውም ይላሉ?

የተከበሩ አቶ ግርማ ፡- አለበት እንጂ ከሌባ ስብስብ መሃል ጎበዝ ሌባ ይወጣል እንጂ አዲስ ነገር አይኖርም፡፡ እያንዳንዱ ሰው ለምን በኢህአዴግ ወስጥ እንደሚቆይ ብናጣራ ለፓርቲው ብለው የምናገኛቸው ሰዎች በጣም ጥቂት ይሆናሉ ፡፡ በመሰረቱ አብዮታዊ ዲሞክራሲ በፍቅር እንድትወድቅለት የሚያደርግህ አይደለም፡፡ አሁን ኢህአዴግ በመሆናቸው ብቻ ስራ ያገኙ ሰዎች ቁጥር ቀላል አይደለም፡፡ ኢህአዴግ ባይሆኑ ኖሮ ይህንን ስራ አያገኙትም ስለዚህ ከድርጅቱ ጋር እንዲጣበቁ ያደረጋቸው ጥቅም መሆኑን ለመገንዘብ አያስቸግርም ይህ ደግሞ ትልቅ ሙስና ነው፡፡


ታላቅ የሰላማዊ ሰልፍ ጥሪ በመላው አውሮፓ ለምትገኙ ሃገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን በሙሉ

$
0
0

Ethiopian United task force for Justices and Human Rights in Europe

በኢትዮጵያ ውስጥ እየተፈጸመ ያለውን የስብዓዊ መብቶች ጥስት፣ የዘር ….Ethiopians rally in Europe, Jun 19, 2013ማጥራት፣ከቤት ንብረት ማፈናቀል፣ በሙስሊሙም፣ በክርስቲያኑም እየተደረገ ያለውን የሃይማኖት ጣልቃገብነትና ግረፋት፣ እስራት፣ ዛቻና ግድያ አንዲሁም በልማት ስም አየተፈጸመ ያለውን ገደብ ያጣ የመሪት ሽያጭና ስጦታ፣ እየፈጸመ ያለውን ህዝባዊና ሃገራዊ ክህደት ለመቃወምና ለማጋለጥ፣ ታላቅ የተቃውሞ ሰላማዊ ስልፍ ጁን 19/2013 ከ13:00 ስዓት ጀምሮ በቤልጄም ብራስልስ ሹማን ቁርጥ ቀጠሮ ይዘናል።

እየተፈጸመ ያለውን የዜጎችን መብት ረገጣ፣ የዘር መድሎ እንዲሁም ወያኔያዊ የሃገር ማጥፋት ውል ፍልስፍና በመቃወም! ለሃገረዎ ለወገኖዎ ያለዎትን ክብርና ሃገራዊ ስሜት በዚህ ደማቅ ሰልፍ ላይ በመገኘት ስሜትዎን በግንባር እንዲገልጹ ጥሪያችንን እናቀርባለን!

ከተለያዩ አውሮፓ ሀገራት ለምትመጡ በሃገር ኣቋራጭ አውቶብስ ለመጓጓዝ በድህረ-ገጹ ወይም ማስታወቂያው ላይ ያለውን ስልክ በመደወል ድምጽዎትን በፊት ለፊት ለማሰማት በአካባቢዎ ይደራጁ።

ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!

ለበለጠ መረጃ:-

Geneva፡

41223454206, 0041799483736

Belgium፡

0032493499619, 0032493284107, 0032493567554, 0032477327090,

German፡

004917647598748 004915211790603 00492217901605

Sweden፡

004673759578

Italy፡

0039690230273

Norway፡

004745206390



፨፨ አደጋ እና ግብረመልሶቻችን ፨፨

$
0
0
 ኢትዮጵያ ውስጥ የሚደርሱት አደጋዎች አብዛኛዎቹ ሰው ሰራሽ አደጋዎች ናቸው ፈጣሪ ሲጠብቀን ከድርቅ በስተቀር(ችግሩ በአብዛኛው ሰው ሰራሽነው)ለመከላከል እጅግ የሚከብዱት ተፈጥሯዊ አደጋዎች ብዙም አልደረሱብንም…. የአደጉት ሀገሮች እጅግ ከባድ የሆኑትን የተፈጥሮ አደጋዎች ለመከላከል በሚተጉበት በዚህ ዘመን እኛ ኢትዮጵያውያን መከላከል በምንችላቸው ሰው ሰራሽ አደጋዎች ሕዝብ እያለቀነው።ከሁለት ወይንም ከሶስት አመት በፊት ይመስለኛል በባህርዳር ከተማ በሳትኮን ኮንስትራክሽን ለሚሰራ ህንፃ የሚሆን ደረጃውን ያልጠበቀ ከእንጨት የተሰራ መወጣጫ(scaffolding)ተደርምሶ 18 ምስኪን ለፍቶ አዳሪዎች በአሰቃቂ ሁኔታ ህይወታቸው አልፏል።ይህ አደጋ የደረሰው በስራ ተቋራጩ በሳትኮን እንዝላልነትና በመንግስት የቁጥጥር ማነስ ነው። ችግሩ ከደረሰ በኋላ ሕዝቡ ለምን ብሎ መንግስትን አስጨንቆ ስላልያዘ በመንግስትም በኩል በሳትኮን ላይ አሰታማሪ የሆነ ከባድ ቅጣት ስላልተጣለ ይህ ተመሳሳይ አደጋ በዚህ አመት ባምቢስ አጠገብ ከሚሰራ ህንፃ የ4 ንፁሀን ዜጎችን ህይወት ቀጥፏል።   ከባህርዳር የሰሞኑ “አደጋዎች” ሳንወጣ ከፌደራሉ ግድያ ብንጀምር፦ =>አንድ ፌደራል እስካሁን ምክንያቱ ጥርት ብሎ ባልታወቀ ሁኔታ 16 ሰዎች በላይ ሲቀጥፍ ሕዝቡ አደባባይ ወጥቶ  እንዴት? ለምን? ተከሰተ ብሎ የመንግስት አካሎችን ማስጨነቅ አለበት? አንድ ግለሰብ አንድን አካባቢ አንድ ሰዓት ሙሉ አካባቢው ተቆጣጥሮ ይኸን ያህል ሰው ከገደለ በአካባቢው መንግስት የለም ማለት ነው።ይህ ክስተት ነገ በባ/ዳርም ሆነ ከባ/ዳር ውጭ ላለመድረሱ ዋስትና የለም። =>ከፌደራሉ ግድያ በኋላ አንድ ሚኒባስ ከእንጅባራ ወደ ባ/ዳር ሲጓ…ዝ ተጋጭቶ አብዛኛዎቹ ተሳፋሪዎች ሲያልቁ ይኸን አይነት አደጋ እንዳይደርስ ስለተደረገው ጥንቃቄ ያወራ የለም። ኢትዮጵያውያን በየቦታው በየአቅጣጫው በመኪና አደጋ እየረገፉ ነው እየተወሰደ ያለው ቅድመ ጥንቃቄ ከተወሰነ ጊዜ የሚዲያ ፍጆታነት ሲያልፍ አይታይም። => ሌላ አሳዛኝ አደጋ ከባ/ዳር የመንግስት ንብረት የሆነ ጀልባ ከ160 በላይ ሰዎችን ይዞ በጣና ሀይቅ ሲጓዝ በደረሰ አደጋ እስከአሁን ከ10 በላይ ሰዎች ህይወታቸው አልፏል የደረሱበት ያልታወቀው በርካቶች ናቸው።ጀልባው እጅግ ያረጀ እንደነበር እየተሰማ ነው ይኸኔ ነው በውኑ ኢትዮጵያ ለዜጎቹ የሚጨነቅ መንግስት አላት ብሎ መጠየቅ! የሚያሳዝነው የወያኔ አገዛዝ አሁንም የቁጥር ጨዋታ እየተጫዎተ ይገኛል። አደጋው እንዴት ደረሰ ብሎ የሚመረምር አካል በቦታው በማሰማራት ፈንታ ፌደራል አሰማርቶ መረጃ እንዳይወጣ ያፍናል።   ከላይ ለአብነት የባህርዳርን ብቻ አደጋ ያነሳሁት ወቅታዊነት ስላላቸው ነው ችግሩ ግን ሀገር አቀፍ ነው።ኢትዮጵያ ውስጥ ብዙ መከላከል የምንችላቸው ሰውሰራሽ አደጋዎች እየደረሱ የዜጎችን ህይወት እየቀጠፉ ነው እነዚህ ክስተቶች የደረሱት በሕዝባቸው ተጣያቂነት ባለባቸው የዴሞክራሲያዊ ሀገሮች ቢሆን ኖሮ ለዜጎቹ ግድ የሚሰጠው መንግስት ከሆነ በመጀመሪያ አደጋው እንዴት እንደደረሰ ይመረመራል ከዛ ስለወደፊቱ እንዴት ጥንቃቄ መወሰድ እንዳለበት ጥናት ይደረጋል ሕዝቡም መንግስትን አስጨንቆ ይይዛል። እኛ ሀገር ግን መንግስት ጉዳዩን ያድበሰብሳል ሕዝቡ ከንፈር ይመጣል አለቀ! ቆም ለምን!? እንዴት!? ብለን ካላሰብንና ተጠያቂ አካሎችን ወጥረን ካልያዝን መቸም በአደጋ ማለቃችን አይቆምም!
13/09/05 ሀና መታሰቢያ / posted by Issa Abdusemed/

ከኢህአዴግ ተፈጥሮ የሚመነጨውን ሙስና ሥርዓቱን በመለወጥ እንጂ ዓመታትን ጠብቆ ከፍተኛ ባለስልጣናትን በማሰር መግታት አይቻልም!!!

$
0
0
Unknownከ33ቱ ፓርቲዎች የተሰጠ መግለጫ

 የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተጠሪ የሆኑት የፌደራል ዋናው ኦዲተርና የፌዴራል የሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን ሚያዚያ 22 እና ግንቦት 6 ቀን 2ዐዐ5 ዓ.ም በቅደም ተከተል ሪፖርቶቻቸውን ለምክር ቤቱ አቅርበዋል..

በዋናው ኦዲተር የቀረበው የ2ዐዐ4 ዓ.ም በጀት ዓመት ኦዲት ሪፖርት በፌዴራል መንግሥት መሥሪያ ቤቶች ከፍተኛ ከሕግ ውጭ የተፈፀሙ ጉድለቶችን ሲዘረዝር ወደ 1.4 ቢሊዮን ብር አለመወራረዱን፣ 353.6 ሚሊዮን ብር ደንብና መመሪያ ያልተከተለ ግዥ መፈፀሙን 3.5 ቢሊዮን ብር ባልተሟላ ሰነድ ወጪ መሆኑንና ከዚህም ውስጥ መከላከያ ባልተሟላ ሰነድ 3.2 ቢሊዮን ብር ወጪ ማድረጉን ይገልፃል፡፡ የመንግሥት መስሪያ ቤቶች ከተፈቀደላቸው በጀት በላይ ብር 212.5 ሚሊዮን መጠቀማቸውንም ያሳያል፡፡

የሥነ-ምግባርና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን በበኩሉ በመንግሥት ባለስልጣናት የተፈፀመውን የመሬት ወረራ፣ በግብርና ታክስ አሰባሰብ ረገድ የሚፈፀመውን ሙስናና በኮሚሽኑ ስለተወሰደው ርምጃ ወዘተ የሚገልጽ ሪፖርት አቅርቧል፡፡ የኮሚሽኑ ሪፖርት ሌላው ክፍል ያተኮረው የገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን ሁለት ከፍተኛ የመንግሥት ባለስልጣናት ፈጽመውታል ባለው የሙስና ድርጊት ነው፡፡ አቶ መላኩ ፋንታ (በሚኒስትር ማዕረግ) የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተርና ምክትላቸው፣ አቶ ገብረዋሕድ ወልደጊዮርጊስና ሌሎች በፈፀሙት ሙስና በፖሊስ ቁጥጥር ሥር ውለው ክስ ለመመስረት መዘጋጀቱን ኮሚሸኑ ገልጿል፡፡

የሁለቱም ተቋማት ሪፖርቶች በዝርዝር ጉዳዮች ካልሆነ በስተቀር በይዘት አዲስ አይደሉም፡፡ የዋናው ኦዲተር (መስሪያ ቤት) ላለፉት በርካታ የበጀት አመታት ቁጥራቸው እጅግ በበዛ የፌዴራል መንግሥት መስሪያ ቤቶች የመንግሥት በጀት ከታለመለት ዓላማ ውጭ በከፍተኛ መጠን እየባከነ መሆኑን ፓርላማው ጉዳዬ ባይለውም ያላመላከተበት ዓመት የለም ለማለት ያስደፍራል፡፡ ይህን ይዘት ያለው ሪፖርት ለዓመታት ከመደጋገሙ የተነሳም የዋናው ኦዲተር በመንግሥት መስሪያ ቤቶች የመንግሥት በጀት እየተመዘበረ ነው የሚለው ሪፖርት የተለመደ ሆኗል፡፡ የሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽንም ከተቋቋመበት ከ1993 ዓ.ም ጀምሮ (በሪፖርቶቹም ሆነ በጋዜጣዊ መግለጫዎቹ) የመንግሥት ባለስልጣናትን (በአብዛኛው ትንንሾቹ አሳዎች የተባሉትን) በጥቂቱም ቢሆን በሙስና ሲከስና ሲያስቀጣ መቆየቱ የተለመደ ሆኗል፡፡ ሙስናው ግን ተባበሰ እንጂ አልቀነሰም፡፡

በሐገሪቱ የመንግሥት ባለስልጣናት በሙስና የመዘፈቃቸው እውነታ መባባሱን በብዙ ረገድ ማመልከት ይቻላል፡፡ የመንግሥት ጆሮና ሕጋዊ ርምጃ የተነፈጉ የፌዴራሉ ዋና ኦዲተር መ/ቤት ከዓመት ዓመት የሚሰሙ የበጀት ብክነትን የሚያመለክቱ ሪፖርቶችና የሥነ-ምግባርና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን በትንንሾቹ አሶች ላይ የሚመሰርታቸው ክሶች ሙስና መባባሱን የሚያረጋግጡ ናቸው፡፡ ገዢው ፓርቲና መንግሥት ቁርጠኛ ርምጃ መውሰዱ ቀርቶ ይፋ መግለጫ ለመስጠት የተቸገሩበትና የተባበሩት መንግሥታት አካላትን ጨምሮ አለም አቀፍ ተቋማት ባለፉት አስር ዓመታት ከ12 ቢሊዮን ዶላር (24ዐ ቢሊዮን ብር) የሚበልጥ ገንዘብ በሕገ-ወጥ መንገድ ከኢትዮጵያ መውጣቱን የሚገልፁ ሪፖርቶች ስለሙስና መባባስ ተጠቃሽ አስረጅዎች ናቸው፡፡ መንግሥትም በአደባባይ የኛ (የመንግሥት) ሌቦች ብሎ መናገሩ ይህንኑ ያረጋግጣል፡፡ በንግድና ኢንቨስትመንት ዓለም ከሚታሰበው (ከሚገመተው) ውጭ በአንድ ጀምበር ከምንም ተነስተው ራሳቸውን ቤተሰቦቻቸውንና ዘመዶቻቸውን በሀብት ማማ ላይ ያወጡትን ጥቂት ሚሊየነሮች እና ቢሊዮነሮች የመንግሥት ባለስልጣናትን መከረኛውና ጎስቋላው ሕዝብ ለይቶ ያውቃቸዋል፡፡ ‹‹የሙስና ሠፈር›› ሕንፃዎችን፣ የንግድ ድርጅቶችንና ቪላዎችን የማን እንደሆኑ ሕዝቡ አንድ በአንድ ያውቃል፡፡ በአዲስ አበባና በክልል ከተሞች ‹‹የሙስና ሰፈሮች›› መብዛታቸውን ማን ከሕዝቡ ሊደብቅ ይችላል?

ይህ እየሆነ ኢህአዴግ ‹‹ዛሬም ሙስናን እየተዋጋሁ ነው›› ቢልም ውጤቱ ግን የተገላቢጦሽ ሆኖበታል፡፡ ኢህአዴግ የከበደው ራሱ የፈጠረውን የሙስና ምንጭ ራሱ ማድረቅ የማይችል በመሆኑ ነው፡፡ ዜጎች በብቃትና በነፃ ውድድር ለኃላፊነት የሚበቁበትን ሥርዓት ከመዘርጋት ይልቅ የፖለቲካ ታማኝነታቸውን ብቻ ዋና መመዘኛ ማድረግ የሙስና ምንጭ መፍጠር ነው፡፡ ነፃ የዳኝነት ሥርዓት አለመዘርጋት ለሙስና በር መክፈት ነው፡፡ የፕሬስና የሚዲያ ነፃነትን ማፈን፣ የመንግሥታዊ ተቋማትን ነፃነት መንፈግ፣ የሙስና ምንጭ መፍጠር ነው፡፡ ምክንያቱም ያለ እነዚህ ተቋማት ተሳትፎ ሙስናን መከላከልም ሆነ መግታት አይታሰብምና ነው፡፡

ከዚህም በመነሳት ኢህአዴግ ሙስናን በቁርጠኝነት ለመዋጋት ተፈጥሮው አይፈቅድለትም ለማለት ይቻላል፡፡ ኢህአዴግ የሚተማመነው በነፃ የዳኝነት ሥርዓትና በነፃ ሚዲያ አይደለም፡፡ በነፃ መንግሥታዊ ተቋማትና በነፃ ሲቪል ማህበራት አይደለም፡፡ በነፃና ፍትሓዊ ምርጫም አይደለም፡፡ ኢህአዴግ የሚተማመነው ከእሱ ጋር ሆነው ምርጫ በሚያጭበረብሩ መካከለኛና ከፍተኛ ካድሬዎቹ ነው፡፡ ምርጫ ሲጭበረበር ‹‹ምርጫው ነፃና ፍትሓዊ ነው›› ብለው በሚመሰክሩ ‹‹ልማታዊ›› ባለሀብቶቹና ይህንኑ በሚያስተጋቡት ‹‹ልማታዊ›› ጋዜጠኞቹ (የፕሮፓጋንዳ ሰዎቹ) ነው፡፡ ዛሬ በእነዚህ ላይ ጨክኖ በቁርጠኝነት ፀረ-ሙስና እንቅስቃሴ በተለይ በከፍተኞቹ ላይ ቢያፋፍም በቀጣይ ምርጫ ለማጭበርበር አጋር ከየት ይገኛል? ሙሰኛ ካድሬዎችና ‹‹ልማታዊ›› ባለሀብቶች ኢህአዴግን ይፈልጉታል፡፡ ኢህአዴግም እንዲሁ ይፈልጋቸዋል፡፡ ሕዝብንና አለም አቀፉን ማህበረሰብ ለማሳሳት የፖለቲካ ቁማር ለመጫወት ሲል ግን ከመንጋ ሙሰኞች መካከል በጣት የሚቆጠሩትን የመስዋዕት በግ ያደርጋቸዋል፡፡ በዚህ ዘዴ በዙፋኑ ላይ ለመቆየት ይሻል፡፡ ለኢህአዴግ ፖለቲካና ሙስና መጣመሩ ተፈጥሮአዊ ነው፡፡

ኢህአዴግ የሁል ጊዜ ጭንቀቱ በሆነው የዙፋኑ አጀንዳ በተጠመደበት ሁኔታ ከላይ እስከታች የተዘረጋው የሙስና ሰንሰለት ሀገሪቱን ክፉኛ እየጎዳት ነው፡፡ ሀገሪቱ ማግኘት የሚገባትን የውጭ ምንዛሪ ሙሰኞቹ ባለስልጣናትና ተባባሪዎቻቸው ወደ ውጭ ባንኮች እያሸጋገሩ ነው፡፡ የሕዝቡን ማህበራዊ ሕይወት ለማሻሻል (ለምግብ ምርት፣ ለጤና አገልግሎት፣ ለንፁሕ ውሃ፣ ለመኖሪያ ቤት፣ ጥራት ላለው ትምህርት. . . ) መዋል የነበረበት ገንዘብ እየተዘረፈ የሕዝብ ጉስቁልና እየጨመረ ነው፡፡ በሙስና የተገኘ ሀብት ፍትሕን ለማዛባት እየዋለ ዜጎች ሰብአዊ መብቶቻቸው እየተጣሱ ነው፡፡ ሀገሪቱ 12 ሚሊዮን ዜጎችዋን በቋሚ ረሀብተኛነት (በምግብ እጥረት ተጠቂነት በሚባለው) ለለጋሽ አገሮች በረሀብተኘነት አስመዝግባ፣ ለሴፍቲኔት ምጽዋት ከስራቸው ወድቃለች፡፡ በራሳቸው አቅምና በነፃነት ለመሻሻል የሚጥሩ ነጋዴዎችና በለሀብቶች የእድሉ በር ተዘግቶባቸዋል፡፡ ዜጎች በሐገራቸው መንግሥታዊ አስተዳደርና የፍትሕ ሥርዓት ተስፋ ቆርጠዋል፡፡ ሙስና ለፍትሓዊ የሀብት ክፍፍል ጠንቅ በመሆኑ ዜጎች በአደገኛ ሁኔታ አንደኛ ደረጃና ሁለተኛ ደረጃና ሦስተኛ ደረጃ ወዘተ ዜጎች ሆነው ተከፍለዋል፡፡ ይህም ከሙስና ለሚመነጩ ወንጀሎች ሀገሪቱን አጋልጧል፡፡

ከዚህ አጠቃላይ ቀውስ ለመወጣት የሚቻለው ኢህአዴግ ‹‹ሙስናን እየተዋጋሁ ነው፡፡›› በሚለው የማስመሰያ ፕሮፓጋንዳ ሳይታለሉና ሙስናው የሥርዓቱ ብልሹ አስተዳደር ውጤት መሆኑን በመረዳት በኢትዮጵያ ውስጥ የተሻለ ሥርዓት እንዲገንባ የሚደረገውን ሕዝባዊ ትግል በሙሉ ልብ በመቀጠልና በማስፋት ነው፡፡

ከ33ቱ ፓርቲዎች የተሰጠ መግለጫ

ግንቦት 13 ቀን 2ዐዐ5 ዓ.ም

አዲስ አበባ


አንዲት ፀሎት፤ ጥቁር ለባሾችን ከነጭ ለባሾች ይጠብቅልን!

$
0
0
ግንቦት 17 የአፍሪካ መሪዎች በአዲስ አበባየአፍሪካ ህብረትን 50ኛ አመት በዓል ትንሽ ሰብሰብ ብለው ሊያከብሩ እና ትንሽ ሰብሰብ ብለው ሊያሸልቡ ተቀጣጥረዋል…

ብዙ ጊዜ የውጪ ሀገር እንግዶች ወደ ኢትዮጵያ ለስብሰባ መጥተው ሲወጡም ሆነ ሲገቡ መንገዱ ታጥሮ የሰው ዘር ዝር ብሎ አይተው ስለማያውቁ ሀገራቸው ሲሄዱ አዲሳባ የፌደራል ፖሊሶች እና የቤተመንግስቱ ጠባቂዎች መኖሪያ ብቻ ሳትመስላቸው አትቀርም፡፡

945335_581602011857560_385163152_n

የሰማያዊ ፓርቲ ልጆች  እንዳሰቡት ከተሳካላቸው፤ ለአፍሪካ መሪዎች እና ለሌሎቹም እንግዶች በሀገሪቷ ውስጥ ከፌደራል ፖሊስ እና ከቤተመንግስቱ ጠባቂዎች ሌላም ሰው መኖሩን እናሳያለን ብለዋል፡፡ ሰው ብቻም ሳይሆን በመንግስቱ ላይ ያዘነ ማቅ የለበሰ ሰው አለ የሚለውን ለማሳየት ጥቁር እንለብሳለን ሲሉም ጨምረዋል፡፡

በአንፃሩ ደግሞ የመንግስት ሰዎች ቢቻል ቢቻል በዕለቱ ጥቁር የለበሰ ሰው በአዲሳባ ከተማ እንዳይኖር፤ ይሄ ፈፅሞ የማይቻል ከሆነ ደግሞ ህዝቡ ጥቁር የለበሰው ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ሀዘን እንደሆነ ለእንግዶቹ ገለፃ ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡

ሰሞኑን በውጪ ሀገር የሚገኝ አንድ ወዳጄ የፌስ ቡክ ስዕልህን ጥቁር በማድረግ ለጥሪው ያለህን ድጋፍ አሳይ ብሎ በውስጥ መስመር ነግሮኝ ነበር፡፡ እኔ ግን እንዲህ ያለውን እንቅስቃሴ በውጪ ያለ ሰው በሚደግፍ ጊዜ የሚባለውን ነገር ሳላደርገውም ብዙ ጊዜ ተብያለሁና ውጡም ሳልል ግቡም ሳልል ልበሱም ሳልል አውልቁም ሳልል በጥቅሉ ድጋፌ በቅስቀሳ ሳይሆን በፀሎት ቢሆን ይሻላል አልኩ፡፡

…እናንተ ውጪ ሆናችሁ ሀገር ውስጥ ያለውን ሰው ልታስጨርሱ… የሚሉ ብዙ ሰዎች አሉ፤ እርግጥ ነው እነዚህ ሰዎች “እናንተ ውጪ ሆናችሁ ሀገር ውስጥ ያለውን ሰው ታስጨርሳላችሁ…” ሲሉ ቢደመጡም እነርሱም ሲፋቁ… ሀገር ውስጥ ቁጭ ብለው ሀገር ውስጥ ያለውን ሰው የሚያስጨርሱ መሆናቸው ተደርሶበታል፡፡

የሆነው ሆኖ ግን እነርሱ የሚሉትን ለማሳጣት በሚል ስትራቴጂ እኔ እና ሌሎች በውጪ የምንገኝ ወዳጆቼ ሰማያዊ ፓርቲ የጠራውን ጥቁር ለብሶ የመዋል ቀን የምንደግፈው በፀሎት እንዲሆን ተስማምተናል… (በቅንፍም ከሁለት ወዳጆቼ ጋር ብቻ እኮ ነው የተስማማሁት… ሃሃ…)

ለማንኛውም ሰማያዊ ፓርቲ ከግንቦት 15 እስከ ግንቦት 17 ድረስ ሁሉም በያለበት ጥቁር ለብሶ በመንግስት ላይ ማዘኑን እንዲያመለክት ጥሪ አቅርቧል፡፡ እኛም  የሆነ ቀን ግር ብለን መጥተን ራሳችን ተሳታፊ የምንሆንበት ቀን እስኪመጣ ድረስ፤ ጥቁር ለባሾች በነጭ ለባሾች ጥቃት እንዳይደርስባቸው በፀሎት እንተጋለን…


የባህር ዳር እጣን መጋዘን ተቃጠለ!

$
0
0

በባህር ዳር የሚገኘው የጅንአድ የእጣን ማከማቻ መጋዘን ተቃጠለ፡፡ እሳቱን ለማጥፋት ከአየር ሀይል፤ ከአድማ ብተናና ከከተማ አስተዳደሩ የተውጣጡ የእሳት አደጋ ሰራተኞች እየነደደ ያለውን መጋዘን ለማዳን እየተረባረቡ ቢሆንም… የእጣኑ መጋዘን ነዲድ እየጨመረ ከአቅም በላይ ሆኗል፡፡

 

Fire in bahrdar;  May 21,13 የተቀጣጠለው መጋዘን በውስጥ በኩል እየነደደ በመሆኑ ለመቆጣጠር አስቸጋሪ ከመሆኑም በላይ ወደ ትልቁና ወደ ዘይት ማከማቻው ሊዛመት ይችላል በሚል ተሰግቷል፡፡ የከተማዋ ነዋሪ ርብርብ በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡ የቃጠሎውን ምክንያት ለማጣራት የተደረገው ሙከራ አልተሳካም፡፡ የባህር ዳር ጅንአድ በአገሪቱ ካሉ ጅንአዶች ከ10 ትልልቆች አንዱ ነው፡፡ በሌላ በኩል፤ ባለፈው ሳምንት የፌዴራል ፖሊስ ሰላማዊ ህዝብ መጨረሱ፤ ከዚያም ተከትሎ ከአስር ሰው በላይ የጫነች ጀልባ ጣና ሃይቅ ላይ ሰጥማ በውስጡ የነበሩት ሰዎች ማለቃቸው የቅርብ ጊዜ ዜናዎች ነበሩ። ይህ ሃዘን የከተማውን ድባብ አጨልሞት እያለ፤ አሁን ደግሞ የእጣን ማከማቸው መቃጠል ብዙዎችን የከተማው ነዋሪ እያነጋገረ ይገኛል።


የኢሕአዴግ የአ.አ ወጣቶች ማህበር 15 አመራሩን አገደ

$
0
0

የአዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር በጉባኤው

ዋዜማ ላይ እየተወዛገበ ነው ‘‘የማህበሩ አመራር በኪራይ ሰብሳቢነት ተዘፍቋል’’ ከማህበሩ የታገዱ የም/ቤት አባላት ‘‘በኪራይ ሰብሳቢነት የተዘፈቁት የታገዱት አመራሮች ናቸው’’…. የማህበሩ አመራር በዘሪሁን ሙሉጌታ የአዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር ከግንቦት 25 ቀን 2005 ዓ.ም ጀምሮ ጠቅላላ ጉባኤውን በማካሄድ የአመራር ምርጫ ያካሂዳል። ማህበሩ ጉባኤ ከማካሄዱ በፊት ወደ 15 የማህበሩ ም/ቤት አመራር አባላትን ማገዱን ተከትሎ ከታገዱት አባላት ጋር ውዝግብ ውስጥ ገብቷል። 70 አባላት ካሉት የማህበሩ ም/ቤት መካከል ወደ 23 የሚሆኑ አባላት አለአግባብ ‘‘ተባረናል’’ ሲሉ ለሰንደቅ ጋዜጣ ገልፀዋል። በአሁኑ ወቅት ማህበሩን እየመራ ያለው የአመራር አካል በኪራይ ሰብሳቢነት መዘፈቁንም አመልክተዋል። በቅርቡ ለሚካሄደው ጠቅላላ ጉባኤም 1 ነጥብ 3 ሚሊዮን የተጋነነ ገንዘብ መመደቡንም ገልፀዋል። የተመደበውም ገንዘብ በአብዛኛው ‘‘ለተሃድሶ’’ ወይም ለመዝናናት የሚውል ከመሆኑም በላይ የገንዘብ አሰባሰብ ሂደቱም ግልፅነት የጎደለው እንደሆነም ተናግረዋል። ማህበሩ ጉባኤውን ለማካሄድ የጠየቀውን 1 ነጥብ 3 ሚሊዮን ብር ከአዲስ አበባ አስሩም ክፍለ ከተሞች፣ ከአዲስ አበባ ገቢዎችና መንገዶች ባለስልጣን እና ከሌሎች መንግስታዊ ተቋማት የሚሰበሰብ እንደሆነም አመልክተዋል። በማህበሩ አመራር አለአግባብ ታግደናል የሚሉት እነዚሁ ወጣት አመራሮች በተጨማሪ እንደገለፁት የጉባኤው መሪ ቃል (ሞቶ) ‘‘የወጣቶችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የመለስን ራዕይ እናሳካለን’’ የሚል መሆኑ ማህበሩ ነፃነት የሌለውና በኢህአዴግ ካድሬዎች የሚሽከረከር መሆኑን ማረጋገጫ ነው ብለዋል። ‘‘አለአግባብ ተባረናል’’ የሚሉት ወጣት አመራሮች የተባረሩበት ምክንያት በማህበሩ አካባቢ ኪራይ ሰብሳቢነት መስፈኑን በማጋለጣቸው፣ አንዳንዶቹ ደግሞ በሕገ-መንግስታዊ መብታቸው መሠረት በሌላ ነፃ ማህበር ውስጥ አባል በመሆናቸው ምክንያት መሆኑን ገልፀዋል። ማህበሩ ለስሙ 80 ሺህ አባላት እንዳሉት ቢነገርም በትክክል የማህበሩን ስራ የሚያከናውኑ ከሁለት ሺህ እንደማይበልጡ ነው ቅሬታ አቅራቢዎቹ የገለፁት። የማህበሩ ፕሬዝዳንት ወጣት ዮሐንስ ጣሰው ማህበሩን ውጤታማ ለማድረግ ከፍተኛ ጥረት ቢያደርግም በኢህአዴግ ካድሬዎች ተፅዕኖ እንደሚደረግበትም ቅሬታ አቅራቢዎቹ አያይዘው ገልፀዋል። በማህበሩ አመራር ላይ በተነሱ ቅሬታዎች ላይ የማህበሩ ፕሬዝዳንት ወጣት ዮሃንስን ለማነጋገር ተደጋጋሚ ሙከራ ያደረግን ቢሆንም ከስራ መብዛት ጋር በተያያዘ ልናገኘው አልቻልንም። ሆኖም የማህበሩ ምክትል ፕሬዝዳንት ወጣት መድሃኔ መለሰ ለሰንደቅ ጋዜጣ እንደገለፀው ከአንድ ሳምንት በፊት ስብሰባ ተካሂዶ እንደነበር እና 15 የማህበሩ የም/ቤት አባላት ለጊዜው መታገዳቸውን አምኗል። በማህበሩ ሕገ-ደንብ መሠረት የአመራር አባላት የሚባረሩት በጠቅላላ ጉባኤው መሠረት እንደሆነ አስታውቋል። 15ቱ የአመራር አባላት የታገዱት ከክፍለ ከተማ በመጣ ግምገማ መሠረት እየሰሩ አለመሆኑ በተጨባጭ ማስረጃ በመረጋገጡ ከክፍለ ከተሞች ለአስፈፃሚው በመጣ የግምገማ ሪፖርት መሆኑን አመልክቷል። ሦስቱ የአመራር አባላት ደግሞ በገዛ ፈቃዳቸው ከምክር ቤቱ እራሳቸውን በማግለል ሲሆን፤ የቀሩት አምስቱ ደግሞ ከሀገር በመውጣታቸው እንደሆነም ገልጿል። ለጉባኤው የወጣው የገንዘብ መጠን በተመለከተ ወጣት መድሃኔ ተጠይቆ ትክክለኛው የገንዘብ መጠን 1 ሚሊዮን ሦስት መቶ ሺህ ሳይሆን አንድ ሚሊዮን ሦስት መቶ ብር መሆኑን፤ ከዝግጅት ጋር በተያያዘም ጠቅላላ ጉባኤው መካሄድ ከነበረበት ጊዜ መዘግየቱን በመጪው ግንቦት 25 ቀን 2005 ዓ.ም ጀምሮ የወረዳ ም/ቤት ጉባኤዎች ከተካሄዱ በኋላ በሳምንቱ ደግሞ በከተማ ደረጃ የማህበሩ ጠቅላላ ጉባኤ እንደሚካሄም አመልክቷል። ለጉባኤው ወጪ የተደረገው የገንዘብ መጠን በ116 ወረዳዎች ውስጥ ለሚካሄድ ጉባኤ በመሆኑ ከፍተኛ ወጪ የሚጠይቅ መሆኑን የጠቀሰው ወጣት መድሃኔ በ116 ወረዳዎች ጠቅላላ ጉባኤ ለማካሄድ የተጠቀሰው ገንዘብ ቢያንስ እንጂ አይበዛም ብሏል። ማህበሩ በመተዳደሪያ ደንቡ የገንዘብ ምንጩ በመንግስትና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች የሚደገፉ በመሆኑ ከመንግስታዊ አካላት በአይነት መደገፉ ወይም ስፖንሰር መደረጉ ችግር የለውም፤ የሚለው ወጣት መድሃኔ ገንዘቡ ለተሃድሶ (ለመዝናናት) ይውላል መባሉ በተጨባጭ እቅድ ላይ የሌለ ነገር ነው ሲል አስተባብሏል። ከመንግስት አካላት በገንዘብ ከሚሰጠው ድጋፍ በበለጠ በቲሸርት፣ በኮፍያና በአዳራሽ መልክ የሚደረጉ ድጋፎች እንጂ በካሽ አለመሆኑን አያይዞ ገልጿል። የማህበሩ የአባላት ብዛት በተመለከተ ቀደም ሲል 80 ሺህ አባላት አሉት ይባል እንደነበር የጠቀሰው ወጣት መድሃኔ፤ ነገር ግን በተደረገው የማጥራት ስራ በአሁኑ ወቅት በማህበሩ እንቅስቃሴ ውስጥ በንቃት የሚሳተፉ የአባላት ቁጥር 32ሺህ መሆኑንም አስረድቷል። የጉባኤው መሪ ቃል በተመለከተ ‘‘በመለስ ሌጋሲ የወጣቱን ተጠቃሚነት እናረጋግጣለን’’ መባሉ ከማህበሩ ነፃነት አንፃር ስላለው ፋይዳም ተጠይቆ፤ በቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ አስተዳደር ወቅት ወጣቶችን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ፓኬጆች በመቀረፃቸው፣ በህገ-መንግስቱ ወጣቱ በነፃ በመደራጀቱና ወጣቱ በአነስተኛና ጥቃቅን ተደራጅተው ተጠቃሚ መሆናቸውን መነሻ በማድረግ የተወሰነ ነው ሲል መልሷል። በማህበሩ ስም ከሚከራዩ ተቋማት ገቢ ጋር በተያያዘ ምዝበራ ስለመኖሩም ወጣት መድሃኔ ተጠይቆ ከአመራሩ ይልቅ በም/ቤቱ ከታገዱ ወጣቶች ላይ ይሄ ችግር መኖሩን ከታገዱበት ሦስት ምክንያቶች መካከል የኪራይ ሰብሳቢነት ችግር አንዱ እንደሆነ በመግለፅ በአንፃሩ ማህበሩ አመራሩን የሚቆጣጠርበት ስርዓት መቀየሱን፤ በአሁኑ ሰዓት ሦስት የአመራር አባላት ከኪራይ ሰብሳቢነት ችግር ጋር በተያያዘ በፍርድ ቤት ተከሰው ጉዳያቸው በሕግ መያዙን በመጥቀስ አመራሩ ኪራይ ሰብሳቢነት እየተዋጋ መሆኑን አመልክቷል። የአዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር በ1990 ዓ.ም የተቋቋመ ማህበር መሆኑ ይታወቃል።n (ምንጭ ሰንደቅ ጋዜጣ የዛሬ ሜይ 22 ዕትም)


Viewing all 931 articles
Browse latest View live


<script src="https://jsc.adskeeper.com/r/s/rssing.com.1596347.js" async> </script>