ማኘክ ከሚችሉት በላይ የጎረሱ ስላሉ ጀርባቸውን በመምታት ማስወጣት ይገባል››
ለሦስት ቀናት በመላ አገሪቱ የኮንስትራክሽን ዘርፍ ላይ የተሰማሩ ከአራት ሺሕ በላይ ድርጅቶችና ባለሙያዎች በተሳተፉበት ኮንፈረንስ፣ ከተሳታፊዎች ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ምላሽ የሰጡት ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ፣ በሦስት የመንግሥት ድርጅቶች ላይ ፍተሻ እንደሚደረግ አስጠነቀቁ…
ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም በኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪው ውስጥ በሙያተኞችና በተቋራጭ ድርጅቶች ማኅበራት አማካይነት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ማብራሪያና ምላሽ የሰጡት መጋቢት 1 ቀን 2007 ዓ.ም. በሚሊኒየም አዳራሽ ሲካሄድ በነበረው ኮንፈረስ ማጠቃለያ ላይ ነው፡፡ የኮንስትራክሽን መሣሪያዎች አከራዮች ማኅበር ባቀረበው ጥያቄ መሠረት የፌደራል ውኃ ሥራዎች ኮንስትራክሽን ድርጅት፣ የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣንና የክልል ውኃ ሥራዎች ኮንስትራክሽን ድርጅቶች፣ ከአንድ ዓመት በላይ ክፍያ ሳይፈጽሙ በማዘግየት የሥራ ማስኬጃ ገንዘብ እንደማይለቁላቸውና አስተዳደራዊ በደል እየፈጸሙቸው እንደሚገኙ፣ የማኅበሩ ሰብሳቢ አቶ ሁነኛው አየለ ተናግረዋል፡፡
በርካታ ማነቆዎች አሉብን ያሉት አቶ ሁነኛው ቁልፍ ብለው ካቀረቧቸው ችግሮች ውስጥ አንዱ ለሆነውና ሦስቱን መንግሥታዊ ተቋማት በሚመለከት ላነሱት ጥያቄ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ምላሽ ሲሰጡ፣ ምንም እንኳ በሦስቱ ተቋማት ላይ ፍተሻ ይደረጋል ቢሉም፣ መሣሪያ አከራዮችና ከመንግሥት መሥሪያ ቤቶች ጋር በሚደረግ የማሽን ኪራይ ውል ሙስና ወይም ‹‹ኪራይ ሰብሳቢነት›› በመኖሩ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በግላቸው የሚያውቋቸው በርካታ ማጭበርበሮች እንደሚፈጸሙ ጠቅሰዋል፡፡ በዚህ ምክንያት አከራዮች ፍርድ ቤት ሄደው ሲከሱና ሲከራከሩ እንደማይታዩ ገልጸዋል፡፡ ቀሪውን ላማንበብ ይህን ይጫኑ
