መድረክ በቅርቡ በ አዲስ አበባ ያካሄድው ሰልፍ የራሱ የሆነ ጠቀሜታ ሊኖረው እንደሚችል ማንም ይገነዘባል። ሰልፉ ልይ አንገብጋቢ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች ተነስተዋል፣ ይበል እሚያሰኝ ነው።ለዚህም ምስጋና ይገባዋል
ከዚህ ባሻገር ሰልፉ ከዝግጅቱ ጀምሮ የራሱ ችግሮች እንደነበሩበት መካድ አይቻልም
በተለይም የ መድረኩ ወጣት ክፍል ሃላፊው ወጣት የሰጠው ቅድመ ሰልፍ ማስጠንቀቂያ አዘል ማስታውሻ ብዙዎችን ያስገረመ ነበር።
ግለሰቡ በፌስቡክ ገጹ ላይ ባስተላለፈው መልክት መድረክ ከ ወያኔ ደህንነትና ፖሊስ ጋር እጅ እን ጓንት ሁነው እንደሚሰሩ አሳስቧል።አያይዞም መድረክ ምንም አይነት ችግር ዉስጥ መግባት እንደማይፈልግ ገልጽጿል።
ከመድረክ መግለጫ ቢያንስ ሁለት ነገሮች በግልጽ ይታያሉ።አንደኛው መድረክ ከወያኔ አኢህዴግ ጋር መሞዳሞድ እንጅ የምር ትግል ማድረግ እንደማይፈልግ ያሳብቅበታል።ለዚህም መገለጫው አገር ምድሩን በደህንነት እና ፖሊስ ያጨናነቀውን ወያኔ ኢህዴግ በወዶ ገብነት የደህንነት(ስለላ) ስራዉን አግዛለሁ ማለቱ ብዙወችን ህምምም ያሰኘ ጉዳይ ነበር።
ሌላው ከመድረክ መልክት የሚታየው ነገር ድርጅቱ ወያኔ ኢህዲግን ለማጀብ እንጅ ለለውጥ ልአስፈላጊዉን መስዋእትነት ል ለመክፈል ቁርጠኝነት የሌለዉ መሆኑን ነው።
በመጨረሻም በወጣት ክፍሉ በኩል የተለቀቀው ማስጠንቀቂያ አኢትዮጵያውያን በግልም ሆነ በቡድን ሰልፉን ለመቀላቀል ጋባዥ የሚባል አይነት ካለመሆኑ ባሻገር በተልይም ከሌሎች ሰላማዊ ታግይ ፓርቲውች ጋር ተባብሮ የመስራት ችግራቸዉንም አጉልቶ ያሳያል።
መድረክ ሆይ እባክህን ጎራህን ለይ፣ ወይ ከህዝብ አልሂያም ከ ወያኔ አኢህዴግ፤ ሶስተኝ መስመር የለም።
