የውኃና የመብራት እጦት ቴሌን ተውት ህዝቡን ሌላ መልመጃ ውስጥ ካስገባ ሰነባበተ እናም ከከፍተኛ ልምድ በመነሳት እኛ ሀረሮች ትንሽ ምክር ቢጤ ልንሰጣችሁ አሰብን;
1,ውሃ ስለጠማህ ብቻ መጠጣት ታቆምና እንዳትታነቅ መከላከያ መሆኑን መልመድ..
2,አንዳንድ ሆቴሎች ምግብ ከበላህ በኋላ የእጅ መታጠቢያ ውሃ የለንም ልትባል ስለምትችል ,,,ምግብ አለ! ብለው ከሚለጥፋ ምግብ ቤቶች ,,,ውሃ አለ! ብለው የሚለጥፋት ጋር መግባት አማራጭ እንደሚሆን; አለበለዚያ ልክ ከሆቴል እንደወጣህ ህፃናቶች ጀሪካን ተሸክመው ጋሼ/እትዬ መታጠቢያ እኔ ጋር አንድ አንድ ብር ብቻ,,,,,,,
3, በየትኛውም ውድቅት ለሊት ውሃ ብትከሰት ተነስተህ መቅዳት እንዳለብህ አትዘንጋ አለበለዚያ የሰው ውሃ እያየህ ስትቆላምጥ ትውላለህ
4,በሄድክበት እና በገባህበት ሰፈር ሁሉ ጥያቄህ ውሃ እናንተ ጋር አለ ይሆናል? ታዲያም አዎ የሚል ምላሽ ስታገኝ ልትቀና ስለምትችል ከአሁኑ አስብበት:)
101, ውሃ ትነግስብሃለችና ታገሳት ምክንያቱም ምንም አታመጣምና መጨረሻ,,,,,, ላይ ግን እንደኛ ትለምደዋለህ ሰሚ ስታጣ ማለቴ ነው።
ድሮ ድሮ ዘመድ ከአዲስ አበባ ወደ ሐረር ሲመጣ,,, ውሃ ይዘህልን ና ነበር የምንለው አሁን እኛ በተራችን እንዳንልክ አሁንም የለንም!
በቀደም እንኳን ሲያቃጥሉን ሁሉ ማጥፊያ አተናል:(
ሕዝብን በውሃ መቅጣት አስነዋሪ ድርጊት ነው!!!
የትኛውም ጤነኛ የሆነ የአገር እድገት መሰረታዊ (necessity) የሚባሉ አቅርቦቶችን ማሟላት የቻለ ሲሆን ብቻ ነው
