(By issa Abdusemed Kassim ) በውጭም ሆነ በሀገር ውስጥ የምትገኙ ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን በሙሉ ቀደም ሲል ለፍኖተ ነጻነት ጋዜጣ የህትመት መሳሪያ ማደራጃ ለመግዛት እንዲቻል ጥሪ መቅረቡ ይታወሳል.. በጥሪው መሰረት በርካታ ወገኖቻችን ተግባራዊ ምላሽ እየሰጡ እንደነበር ቢታወስም በወገኖቻችን እንድንኮራ አድርጎናል።
ይሁን እንጂ በርካታ ወገኖቻችን በገንዘብ አላላኩ ዙሪያም ላይ ተጨማሪም ማብራሪያ በመጠየቃችሁም ይህንን ማብራሪያ ግልፅ በሆነ መንገድ ለጥያቄአችሁም
አኩሪና አስደሳች መልስ በመስጠት ገንዘቡ የሚገባው በቀጥታ በፍኖተ ነጻነት አካውንት ነው …በሚልም ምላሽ ሰተንበታል ይኸው ዛሬ የወገን ደራሽ ወገን ነውና
የምስራች ልነግራችሁ ብቅ ብለናል የምስራች ለፍኖተ ነፃነት ታዳሚዎች በሙሉ ለኢትዮጵያ ህዝብ ልሳን የሆነችውን ጋዜጣ ስራዋን ለመጀመር ጥቂት ቀናቶች የቀራት
ቢሆንም በናፍቆት ስንጠብቀው የነበረውን ማተሚያ ማሽን ከብዙ ትግልና እንግልት በኋላ በእጃችን አስገብተናል፡፡ ከእንግዲህ ተወዳጇን ፍኖተ ነፃነት ጋዜጣን
በመላው ኢትዮጵያ ህዝብ ለማዳረስ እንችላለን ለማለት ያስችለናል ፍኖተ ነፃነት ጋዜጣ ለየት የሚያደርጋት ነገር ቢኖር ለፍትህ እና ለዲሞክራሲ መታገሉዓ ብቻ ሳይሆን
እውነትን በግልፅ ሳይጨመርም ሆነ ሳይቀነስ ለህዝብ ይፋ ማድረጉዓ ነው:: በገዢዉ ፓርቲ ኣፈናና በተፈጠረበት ተፅኖ ህትመቱ እረዘም ላለ ጊዜ ቢቓረጥም አሁን ግን
በወቅቱ ተጨባጭ ሁኔታላይ ያለዉን እዉነታ ለኢትዬጲያ ህዝብ እና ለፍኖተ ነፃነት አፍቃሪዎች ከሰሞኑ ባስገባችው አዲስ ማተሚያ ማሽን አዲስ ነገር ይዛ ብቅ ትላለች
ብለን እንገምታለን :: በአሁን ሰአት ኢትዮጲያ ዉስጥ በገዢዉ ፖርቲ ሚዲያዎች የሚነገሩ ከእዉነት የራቁ ዉቨችን ለመስማት ህዝቡ የሚገደድበት አንዱ ምክናያት የነፃ
ጋዜጦችን በሀገሪቱ እንዳያንሰራሩ አድርጎ ከምድረ ገፅ እዲጠፋ በማድረግ የኢሀዲግ መንግስት እንቅልፍ አቶ እየሰራ መሆኑ ይታወቃል ።
ኢትዮዽያ ለዘላለም ትኑር
