ዋናው የውሸት ቀፎ የሆነው የ ‘ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ’ ድርጅት፤ በድርጅቱ ሁለተኛ ጉባኤ (1975) ያጸደቀው ውሳኔ አንዲህ ይላል “በአገራችን የሰሜን ጦርነቶች በዶጋሊ፤ጉንደት፤ጉራዕ… የተካሄዱ ጦረነቶችና ድሎች የኤርትራ ሕዝቦች እና የትግራይ ሕዝቦች ድል ነው…
ሲል በ13ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ በእነ አምደጽዮን (ከሸዋ እየገሰገሱ) እና በመሳሰሉት የድሮ ነገሥታት ከሩቅ ያገሪቱ ግዛቶች እየተወረወሩ ወደ “ሓማሴን ምድር ወይንም ወደ ባሕረ ምድር” (ኤርትራ) በመሄድ ከቱርኮች እና ከመሳሰሉ ወራሪዎች ተዋግተው ጠላት ድል የመቱትን ሁሉ በመደበቅ፤በአካባቢው የተደረጉ ጦርነቶች የትግሬ ጀግኖች ውጤት እያሉ ሚዛን ያጣ ትምክሕት በማሰራጨት አዲሱን የትግራይ ትውልድም ያንን ውሸት እየተቀበለ በዛው ትምክሕት እየተወጠረ መራመድ ጀምሯል። አሁን ወደ መረጃዬ ልሂድ።
read more http://www.ethiolion.com/Pdf/02262014yeweyanie_tegrewoch.pdf
